2021 ፌብሩዋሪ 28, እሑድ

የመጽሐፍ ዳሰሳ

 የመጽሐፍ ዳሰሳ

(በዚህ ገጽ የተከፈለበት)



የመጽሐፉ ርዕስ - Marcus GARVEY፣ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አፍሪካ

 ደራሲ - ማርከስ ጋርቪ

 የመጽሐፉ ተርጓሚ - አሊሹ ሙሜ

 ዘውግ - ግጥሞች 

 የገጽ ብዛት - 142

ዋጋ - 69

የታተመበት ጊዜ - 2007 ዓ.ም.

ዳሰሳ ጸሃፊ - ሃይማኖት ክንፈ

የተከበራችሁ ውድ የመጽሐፍ አፍቃሪያን እንደምን ሰንብታችኋል?ሰላም እና ጤና እንዲሁም  ፍቅር ከሁላችሁ ጋር እንዲሆን እየተመኘሁ! ወደ መጸሐፍ ዳሰሳዉ ስገባ:-

ማርከስ ጋርቪ ይባላል የመጽሐፉ ደራሲ ሲሆን በትውልድ የጃማይካዊ ነው። ጋርቪ የጥቁር ዘር መሪ፣ጋዜጠኛ፣ተነግሮ አሳማኝ እንዲሁም ርእዮተ አለማዊ ሰው ነበር። ከዚህም በተጨማሪ ማርከስ ጋርቪ ገጣሚ ሲሆን የደቡብ እና የመካከለኛውን አሜሪካ ግዛቶች ተንቀሳቅሶ ከጎበኘ በኹዋላ በ1912 ወደ እንግሊዝ ሀገር ተጓዘ።በእንግሊዝ ሎንደን ከተማ ሳለ ለአፍሪካ ታሪክ እና ባህል ልዩ ትኩረትን ሰጥቶ የግል ጥናቱን አከናወነ።

 አንደበተ ርቱእ የሆነው ማርከስ ጋርቪ በአሜሪካ የሚኖሩ ጥቁሮችን "በዝርያችሁ ኩሩ፤"ብሎም "ወደ አያት ቅድመ አያቶቻችሁ ምድር ወደ ቅድስት አፍሪካ ተመልከቱ!"እያለ መስበኩን ቀጠለ።

በፓን አፍሪካኒዝም እንዲሁም በፈረንሳይ ሀገር የአፍሪካውያን "ኔግሪቱድ"ንቅናቄና የለንደኑ የምእራብ አፍሪካ ተማሪዎች ህብረት እና ሌሎችም የጥቁር ነፃነት ትግሎች በተነሱ ቁጥር ከነ ኤድዋርድ ዊልመንት፣ክዋሜ ንክሩማ፣ጁሙ ኬንያታ፣ማልኮም ኤክስ እና ሌሎችም ስሞች ጋር ማርከስ ጋርቪ መወሳቱ አይቀሬ ነው።

 ማርከስ ጋርቪ ገና የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ አገዛዝ ቀንበር ባልተላቀቁበት ጊዜ እንኳን "ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አፍሪካ "የሚለውን መሪ ህልም ከአእምሮው አመንጭቶ ታግሎ ያታገለ ጀግና ነው። ጋርቪ የአፍሪካ ዝርያዎችን ወደ አፍሪካ እንዲመለሱ ሆኖ የበለፀገች በራሷ ህዝብ የምትተዳደር ጠንካራና ነፃ የሆነች አንዲት አዲስ አፍሪካን መፍጠር ነበር አላማው።

 በጥሞናዊ የስነግጥም ስራዎቹ ውስጥ የመጀመሪያውን የኢንፔሪያሊስቶች ሽንፈት ከዋኝ የሆኑትን የአድዋ መሪ የሆኑትን አጤ ሚኒሊክ፣ከዚህ ሽንፈት በኹላም በኦጋዴን በኩል የጣሊያን ወረራ ያርበደበዱትን ራስ ነሲቡ ዛማኔልን እና ለኢትዮጵያ የተዋጋው ቱርካዊ ውሂብ ፓሻ አንዲሁም የደቡብ ክንፍ ተዋጊ የነበሩትና ቡታጅራ የተሰውትን ራስ ደስታ ዳምጠዉ የመሳሰሉትን የነፃነት ታጋዮች በስም ለመጥቀስ የመታሰቢያ ግጥሞችን አበርክቶላቸዋል።



 በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን በዘመናዊው ባርነት እየተገዛን ላለነው አፍሪካውያን ራሳችንን እንድንመለከት ያደርገናል። እንዴት? ብትሉ ዛሬም በዲቪ ሰበብ እነሱ የናቁትን የስራ አይነት ወይም ምርጫ በማጣት ሳቢያ ዛሬም በአውሮፕላን ተሳፍሮ፣በመኪና ተሽከርክሮ፣በመርከብ፣በታንኳ፣በጀልባ፣በበቅሎ፣በግመል እንዲያም ሲል በእግሩ ኳትኖ እዚያዉ ስፍራው ድረስ በመሄድ የሁነቱ ሰለባ መሆን እጅግ የሚያሳዝን እውነታ ነው።ይህ መጸሐፍ አይናችንን ገልጠን እውነታውን እንድናይ አመላካች ሲሆን እንደ እንደ አፍሪካዊ ምን ማድረግ አለብን የሚለውን በግጥሞቹ እያነሳሳ ፣እየመከረ እና እየኮረኮመም ያስተምረናል።

 ይህን መፅሃፍ ማን ሊያነበው ይገባል? ይህ የማርከሰ ጋርቪ ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አፍሪካ መፅሐፍ በታሪክም ሆነ በምርምር ተግባር ለተሰማሩ የኢትዮጵያ ወጣቶች ለሀገራቸውና ለህዝባቸው ተቆርቋሪና ታጋይ ዜጋ እንዲሆኑ ከማገዝም ባሻገር ለአንባብያን የንባብ ፍጆ ወይም የዚያን ዘመን ከዚህኛው ጋር በማጣቀስ ምርምር ማድረግ ለሚሹ ሁሉ የጠብታንም ያህል አስተዋፅኦ ያደርጋል።


በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...