2017 ሴፕቴምበር 2, ቅዳሜ

ደጋ…ግሞ ማዳመጥ  የታከተው መምህር




ከትምህርት ተመልሶ ተገናኘን፡፡ ከኔ ጋር ያወራነው በመሃላችን ብዙም የተለመደ ወሬ አይደለም፡፡ ስለ ፍጥነት ንባብ ነበር፡፡ በዚህ ጉደይ ላይ ከዚህ ውይይታችን በኋላ አስፈላጊውን ዶሴ በአድራሻው ልኬለት አመስግኖኛል፡፡

‹‹የጥበብ ሰዎች ሳይቀሩ በቴሌቪዥን ላይ ተመሳሳይ የዱሮ ወሬ ማውራት ልማዳቸው ነው፤ ምክንያቱም ሌላውም ጓደኛቸው ሲደጋግመው ስለሚውልና ስለማይሳታቸው ነው›› አለኝ፡፡ የወሬ መደጋገም አሰልችቶታል፡፡ ከመገናኛ ብዙሃን እስከ መስሪያቤት፣ ከቤተሰብ እስከ ጓደኛ ሁሉም አዲስ ነገር አልባ ሆነውበታል፡፡

‹‹ጓደኛህን አግኝተኸው ባለፈው ያወራህን ተመሳሳይ ወሬ ያወራሃል፡፡ ‹እሱን እኮ ባለፈው ነግረኸኛል››› ስትለው አይሰማህም፡፡ ‹‹ለምንድነው ግን ሰዎች አዲስ ወሬ ያጡት›› ሲል አማረረ፡፡  

ይህን የወሬ መጠንዛት የታዘቡ ታዝበዋል፤ የተማረሩ ተማረውበታል፤ የሰለቻቸውና ድፍረቱን ያገኙ አልፈው ተናግረዋል፡፡ አዲስ ወሬ ከየት ሊገኝ እንደሚችል ነጋሪና መካሪ ያሻቸው ይሆን? ሳይሆን አይቀርም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን ደጋግመወው ቢያወሩ የማሰለቹ አሉ፡፡ የመንግስቱ ለማን ፍጡር አለቃ መክፈልትን አስታወስኩ በግሌ፡፡

‹‹ስለችግርህ ማውራት ስትችል ለምን ከዱሮ ጋር ትንገታገታለህ፤ ከራስህ ጋር ስታወራ ነው መፍትሔ የሚመጣው፡፡ ለራሳችን የማሰቢያ ጊዜ ሲኖረን ነው መፍትሔና ለውጥን የምናመጣቸው፡፡ እስኪ የቅድመ ምረቃ ትውስታ ማውራት ለኛ ምን ይጠቅመናል?››

‹‹ወሬኛ ሰው ደግሞ ያለ ምንም ዳራ ያወራሃል፡፡ ሲፈልገው ቤቱ ሊበላኝ ነው ይልሃል፡፡ አሁን ነገሩ ያው ወጣቱንም ያየህ እንደሆነ Noshall ሆኗል፡፡ – without social life የሚኖር ነው - በቅርቡ የሳማሁት ጥሩ አገላለጽ ነው፡፡ ምናልባት ያለ የሌለ ወሬ ማዳመጥ ሲሰለቸው ሊሆን ይችላል፡፡ ስለችግርህ ለበርካታ ቀናት ቤት ዘግተህ ተቀምጠህ መነጋገር ትችላለህ፡፡ ቤት ካልዘጋህ እኮ ማንበብ አትችልም፡፡ ገለባ ነው የምትሆነው፡፡ ዘፈኖች ራሱ ይገርሙኛል፡፡ ጨፍር ተዝናና ይሉሃል፡፡ አዲስ ነገር አይታይባቸውም፡፡››

ወንድሜ ጽናቱን ይስጥህ፤ አዲስ ወሬም አይንሳህ፤ የድርሻህን ለመወጣትም ሞክር እላለሁ!

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...