2016 ኤፕሪል 20, ረቡዕ

ራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት




ጤና ይስጥልን፣
በደብረብርሃን ከተማ የጀመርነው መጻሕፍትን ባሉበት የማድረስ ተግባራችን በይፋ ተጀምሯል፡፡ የሚፈልጉትን መጻሕፍት ይዘዙን፡፡ የምንሰጣቸው አገልግሎቶች፡-
1.
የራስዎ አነስተኛ የመጻሕፍት ስብስብ እንዲኖርዎት እናግዛለን (የመጻሕፍት መደርደሪያ ሞዴሎችን እናቀርባለን)
2.
ምን እንደሚያነቡ እናማክራለን
3.
የንባብ ችግር ካለብዎት እናግዛለን
4.
በኢንተርኔት፣ በስልክ፣ በሶፍት ኮፒ ሱስ ከተጠመዱ ወደ መጽሐፍ እንዲመጡ እናደርጋለን፡፡
4.
የፍጥነት ንባብ (speed reading with a better comprehension) እናለማምዳለን
5.
ያገለገሉ መጻሕፍትን እንገዛለን፡፡ ገዝተውት ሳያነቡት የተቀመጠ መጽሐፍ ካለ ለምን ሸጠውልን ሌሎች አያነቡትም? መጻሕፍትን ከእስር ነጻ እናውጣቸው!
6.
ያገለገሉ መጻሕፍትን እንገዛለን፣ እናከራያለን፡፡ በነጻ እናስነብባለን፡፡ መጻሕፍትን እንሸጣለን፡፡
7.
ከእኛ የገዙትን መጽሐፍ አንብበው ንጽሕናውን እንደጠበቀ ከመለሱልን ከዋጋው 50 ፐርሰንት እንገዛለን፡፡
8.
ከእኛ የገዙትን መጽሐፍ ማንበብዎን በስልክና በኢንተርኔት እንከታተላለን
9.
መጽሐፍ ለሚያሳትሙ ደራሲያን የምክር አገልግሎት እንሰጣለን
10.
የመጻሕፍት ውይይትና የስነጽሑፍ ምሽት ዘወትር ሐሙስ ማታ ከ12፡00 ጀምሮ እናካሂዳለን
11.
የመጻሕፍት ዕቁብ እናስጀምራለን፤ መጻሕፍቱን እናቀርባለን፤ በቡድኑ ምን ይነበብ በሚለው ላይ እናማክራለን
12.
በሌሎች ከተሞችም የመጻሕፍት ሽያጭና እኛ ከምንሰራው ጋር የሚመሳሰል ስራ ለመጀመር ለሚያስቡ የምክር አገልግሎት እንሰጣለን፡፡
ለተጨማሪ መረጃ 0913 6588 39 ወይንም 0970 38 10 70 ይደውሉ፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል!
መገኛችን ጠባሴ፣ ደብረብርሃን፣ ከእቴነሽ ሆቴል አጠገብ ነው፡፡ ስልክ 0970381070

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...