2016 ማርች 19, ቅዳሜ

መጻሕፍት



ጤና ይስጥልኝ፣
በደብረብርሃን ከተማ የጀመርነው መጻሕፍትን ባሉበት የማድረስ ተግባራችን በይፋ ተጀምሯል፡፡ የሚፈልጉትን መጻሕፍት ይዘዙን፡፡ የምንሰጣቸው አገልግሎቶች፡-
1. የራስዎ አነስተኛ የመጻሕፍት ስብስብ እንዲኖርዎት እናግዛለን (የመጻሕፍት መደርደሪያ ሞዴሎችን እናቀርባለን)
2. ምን እንደሚያነቡ እናማክራለን
3. የንባብ ችግር ካለብዎት እናግዛለን
4. በኢንተርኔት፣ በስልክ፣ በሶፍት ኮፒ ሱስ ከተጠመዱ ወደ መጽሐፍ እንዲመጡ እናደርጋለን፡፡ (እንደ እኔ)
4. የፍጥነት ንባብ (speed reading with a better comprehension) እናለማምዳለን
5. ያገለገሉ መጻሕፍትን እንገዛለን፡፡ ገዝተውት ሳያነቡት የተቀመጠ መጽሐፍ ካለ ለምን ሸጠውልን ሌሎች አያነቡትም? መጻሕፍትን ከእስር ነጻ እናውጣቸው!
6. እናከራያለን (የሚከራዩት ገንዘብ አስይዘው ሲሆን፤ ክፍያው በቀን ሁለት ብር ነው፡፡)
7. ከእኛ የገዙትን መጽሐፍ አንብበው ከአንድ ሳምንት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ንጽሕናውን እንደጠበቀ ከመለሱልን ከዋጋው በ60 ፐርሰንት እንገዛለን፡፡
8. ከእኛ የገዙትን መጽሐፍ ማንበብዎን በስልክና በኢንተርኔት እንከታተላለን
9. መጽሐፍ ለሚያሳትሙ ደራሲያን የምክር አገልግሎት እንሰጣለን
10. የመጻሕፍት ውይይት እናካሂዳለን
11. የመጻሕፍት ዕቁብ እናስጀምራለን፤ መጻሕፍቱን እናቀርባለን፤ በቡድኑ ምን ይነበብ በሚለው ላይ እናማክራለን
12. በሌሎች ከተሞችም የመጻሕፍት ሽያጭና እኛ ከምንሰራው ጋር የሚመሳሰል ስራ ለመጀመር ለሚያስቡ የምክር አገልግሎት እንሰጣለን፡፡
ሌላ ምን አገልግሎት ብንጨምር ጥሩ ነው ትላላችሁ? ለተጨማሪ መረጃ በ 0913 6588 39 ወይንም 0970 38 10 70 ይደውሉ፡፡ ጊዜያዊ ማዕከላችን ጓሳ ቡና ሲሆን መገኛውም ደብረብርሃን፣ ጠባሴ፣ ከእርሻ ሰብል ፊት ለፊት ነው፡፡

2016 ማርች 10, ሐሙስ

አንድን ትምህርት በሁለት ቋንቋ የምታስተምሩ ሆይ!




በቅርቡ ወደ አንድ የግል ትምህርት ቤት ሄጄ ከመምህራን ጋር በምነጋገርበት ወቅት አንድን ትምህርት በሁለት ቋንቋ እንደሚያስተምሩ ነገሩኝ፡፡ ይህም ማለት ሂሳብንና ሳይንስን የመሳሰሉትን ትምህርቶች በአማርኛም በእንግሊዝኛም ያስተምራሉ፡፡ ነገሩ የወላጆችንም የመንግስትንም ፍላጎት ለማሟላት መሆኑ ነው፡፡ በአንድ በኩል ወላጅ ልጁ በእንግሊዝኛ እንዲማርለት ይሻል፤ በሌላ በኩል ደግሞ መንግስት በአፍ መፍቻ ቋንቋ አስተምሩ ይላል፡፡ በመሃል ቤት ተማሪው ጫና ያርፍበትና አሥራ ምናምን ትምህርት እንዲማር ይገደዳል፡፡ አሥራ ምናምን የሚገባው ኮምፒውተሩ፣ የእንግሊዝኛ ንግግሩ ሲጨማመር ነው፡፡ በግል ትምህርት ቤቶች የተሻለ የትምህርት አሰጣጥ መኖሩ ባይካድም ተማሪው ግን ይህ ጫና ሊወገድለት ይገባል - በአንዱ ቋንቋ ብቻ ሊማር ይገባዋል፡፡ ይህን ጉዳይ የሚከታተሉት የትምህርት ሹማምንት ትምህርት ቤት ድረስ ሄደው ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ሰምቻለሁ፡፡ ተማሪዎቹ በሁለት ቋንቋ አይማሩም የሚል አቋም አላቸው፡፡ አንድ ቅር የሚያስብለው ነገር ግን ግብረገብንና ግዕዝና የመሳሰሉት ትምህርቶችም ሊሰጡ አይገባም መባሉ ነው፡፡ የትምህርቱ ጠቀሜታ እየታየ ተማሪዎች እንዲማሩት ቢደረግ ክፋቱ አይታየኝም፡፡ እርስዎ ስለዚህ ጉዳይ የተሻለ የሚያውቁ ከሆነ ሃሳብዎን ያጋሩኝ፡፡

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...