2020 ዲሴምበር 24, ሐሙስ

ለታዳጊ ሃገራት የተመረጡ የሥራ ፈጠራ ሃሳቦች

 


አሰናጅ - መዘምር ግርማ

 

መግቢያ

በታዳጊ አገር እንደመገኘታችን ያለንበት ሁለንተናዊ ሁኔታ ከሌላው ዓለም የተለየ ነው፡፡ አዳዲስ ነገር የምንሞክር ሰዎች ለአካባቢያችን ተመራጭ የሆነ የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ያስፈልገን ይሆናል፡፡ ስለሆነም ላለንበት ዘመንና አካባቢያዊ ሁኔታ የሚስማሙ የሥራ ፈጠራ ሃሳቦችን ማወቅ ይኖርብናል፡፡ በዚህም መሠረት ከድረገጽ ያገኘነውን ጽሑፍ በአጭሩ ወደ አማርኛ መልሰነዋል፡፡ በየሥራ ዘርፉ ያለውን ዕድልና ዝርዝር ሁኔታ ለማወቅ ድረገጹን እንድታነቡት እንጋብዛለን፡፡ ምናልባትም እንግሊዝኛ ቋንቋ የሚቸግራችሁ አንባቢያን ከድረገጹ ጽሑፉን ገልብጠችሁ በመውሰድ በጉግል ትራንስሌት ተርጉማችሁ በአማርኛ ማንበብ የምትችሉ መሆኑን ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

 

ዝርዝር የሥራ ዓይቶቹን እነሆ፡-

1.     ደረቅ ቆሻሻ መሰብሰብ

2.     የሕጻናት ማዋያ

3.     ግብርና

4.     የቁጠባ ቤቶች አቅርቦት

5.     የውበት ሳሎን

6.     በድረገጽ ሙያን መሸጥ

7.     ብሎግ መጀመር

8.     የፀሐይ ኃይል ላይ የተመሰረተ ሥራ

9.     የስማርት ስልክ ሽያጭ

10.  ማስጠኛ ማዕከል

11.  ጭማቂ ቤት

12.  ልብስ ስፌት

13.  ሥዕልና ቅርጻቅርጽ

14.  አፕሊኬሽንና የኦንላይን ስራዎች

15.  ዘመናዊ የክፍያ መንገዶች

16.  አነስተኛ ብድርና ቁጠባ

17.  የጉዞ ወኪል

18.  የሞባይል ካርድ መሸጥ

19.  የዩቱብ ቻነል መጀመር

20.  ዕደ ጥበብ ማስተማር

21.  የሙዚቃ መምህርነት

22.  የስፖርት አሰልጣኝነት

23.  አስጎብኚነት

24.  የበይነመረብ የምግብ አሰራር ትምህርት

25.  ቁርስ ቤት

26.  አማራጭ የኃይል ምንጭ

27.  ነዳጅ ቆጣቢ ፈጠራ

28.  አስመጪና ላኪ

29.  ያገለገሉ ዕቃዎች ሱቅ

30.  ሥጋ ቤት

31.  ጥበቃና ደህንነት

32.  የሰራተኛ አገናኝ

33.  የኤሌክትሮኒክ ንግድ

34.  የዳሰሳ ጥናትና መረጃ ስብሰባ

35.  አማራጭ የኃይል ምንጭ

36.  የዕቃ ግዢ አገልግሎት

37.  የማጓጓዝ ሥራ

38.  የኮምፒውር ነክ መረጃ ጥበቃ

39.  የትምህርት ማማከር

40.  የእጥበት አገልግሎት

41.  ጥገና

42.  የጤና አገልግሎት

43.  የኮምፒውተር አገልግሎት ማዕከል

44.  የሂሳብ ሥራ

45.  የቢዝነስ ዕቅድ ሥራ

46.  የመኪና እጥበት

47.  የኮምፒውተር አሰልጣኝነት

48.  የግል የአካልብቃት አሰልጣኝነት

49.  የትርጉም አገልግሎት

50.  ቤት ለሚለቁ ዕቃ ማጓጓዝ

ማጠቃለያ

እስኪ ከእነዚህ ከላይ ከተጠቀሱት የምርትና አገልግሎት ዓይነቶች የትኞቹን ለመሞከር አሰቡ? የትኞቹስ በአካባቢዎ ተጀምረዋል? የትኞቹስ አዳዲስ ናቸው? ለመጀመር የሚያስፈልጉዎትን ነገሮች ያስቡባቸው፡፡ መሬት ወይም ቦታ፣ ገንዘብ፣ ሥልጠና፣ የሠለጠነ ሠራተኛ ወይስ ሌላ? ለእነዚህና ሌሎች ጥያቄዎች የሚመጡልዎትን መልሶች በመጻፍ ያቅዱ፡፡ ሌላ የማንክደው ነገር ከላይ የተገለጹት የሥራ ዘርፎች ላይ አልፎ አልፎ ተመሳሳይነትና ብዥታ ሊኖር ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ እያንዳንዳቸው የየራሳቸው ልዩ ባህርያት አሏቸው፡፡ ከኛ አገር ሁኔታም ጋር አጣጥሞ በማሻሻል በግልም ሆነ በቡድን መስራት ይቻላል፡፡ በቀጣይ ተከታታይ ዕትሞቻችን ሥራ ፈጠራን አስመልክቶ ተከታታይ ጽሑፎችን እንደምናወጣ እየገለጽን ለማናከውም ጥያቄዎ እንዲጽፉልን እንጋብዛለን፡፡

      በሸዋጸሐይ ዝግጅት ክፍል አድራሻ ወይም በ mezemirgirma@gmail.com    

ውድ አንባቢያችን፡- እርስዎም በጉዳዩ ላይ በደንብ አስበውበት በኛ ሁኔታ ሊሰሩ የሚችሉ አስር የሥራ ፈጠራ ሃሳቦችን ከላኩልን ጥሩ የምንላቸውን በቀጣይ ዕትሞች የምናወጣ ይሆናል፡፡

2020 ሴፕቴምበር 2, ረቡዕ

ዘጠና ቀናት በአዲስ አበባ፣ ተጻፈ በመዘምር ግርማ

 ዘጠና ቀናት በአዲስ አበባ

ተጻፈ በመዘምር ግርማ

ከሰኔ 1፣  2012 እስከ ነሐሴ 30፣ 2012 በአዲስ አበባ ስላደረኩት ቆይታ አንዳንድ ነገሮች

ሀ. ሰኔ 1፣ 2012 ዓ.ም. ከደብረ ብርሃን ከሞቀ ቤቴ ወደ አዲስ አበባ መጥቼ አነስተኛ የመኖሪያ ቤት ተከራይቼ ሁቱትሲን አሳትሜ ማከፋፈል ጀመርኩ።

ለ. ሁቱትሲ የሩዋንዳዊቷ የኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ የዘር ማጥፋት ወቅት ማስታወሻ የ Left to Tell የአማርኛ ትርጉም ነች። 

ሐ. በ2008 ዓ.ም. የመጀመሪያ ዕትሟን ሳወጣ 62,000 ብር ለማተሚያ ቤት ከፍዬ ነበር። መጽሐፉ ተከፋፍሎ ገንዘቡ በወቅቱ ስላልተሰበሰበ ደግሜ ለማሳተም የሚሆን ገንዘብ ለማግኘት አራት ዓመታት ፈጅቶብኛል።

መ. ይህም የሆነው ከመጽሐፉ ሕትመት በኋላ በደብረብርሃን የከፈትኩት ራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት ወጪ ስለሚያስወጣኝ ነው።

ሠ. እንደ መምህርነቴ ከመጋቢት መጀመሪያ እስከ ግንቦት መጨረሻ በኮቪድ ምክንያት እረፍት ላይ ስለነበርኩ በራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት በአስነባቢነት ሰርቻለሁ። ይህም የሆነው አስነባቢዎቹ በበሽታው ምክንያት ከስራቸው ስለለቀቁና ገጠር ስለገቡ ነው። ከሰኔ እስከአሁን አዲስ አስነባቢ ስላገኘሁ በሷ መኖር ምክንያት ነው አዲስ አበባ ልቀመጥ መቻሌ።

ረ. በጥቅሉ መጽሐፏ ከሁለተኛ እስከ አራተኛ ዕትም 20,000 ኮፒ የተሸጠች ሲሆን፤ ይህም በቀን በአማካይ 222 መጽሐፍ እንደተሸጠ ያሳያል።

ሰ. መጀመሪያውኑ በክረምትና በኮቪድን መምጣት ምክንያት አንባቢያን መጽሐፏን ይፈልጋሉ የሚል ሐሳብ ስለመጣልኝ ወደ ህትመቱ ሥራ ገብቻለሁ። 

ሸ. ሥራው ብዙ ውጣውረድ ያለው ሲሆን ወደ ተስፋ ማስቆረጥ ደጅም አድርሶ ይመልሳል። ቢሆንም የመጻሕፍት ማሳተምና ማከፋፈልን ሥራ ከታች በመጀመር ላውቅበት ችያለሁ። በአሁኑ ወቅት ሁለት የሌሎች ደራሲያንን ሥራዎች በአሳታሚነት ወደ ማተሚያ ቤት አስገብቻለሁ። ይህም እነዚህ ሦስት ወራት የሥራ ፈጠራ ሕይወቴን እንዴት እንደቀየሩት ለማየት ይቻላል።

ቀ. ማህበራዊ ሚዲያ፣ ዋናው ሚዲያና ብዙ ወዳጆቼ ለመጽሐፏ መሰራጨት ትልቅ ሚና ተጫውተዋል። ከነዚህም ውስጥ አማራ ቴሌቪዥን፣ ሠይፉ በኢቢኤስ፣ አልዐይን አማርኛ፣ ፀደይ ኤፍኤም 102.9፣ የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ፣ Meet EBC (ተፈራ ገዳሙ) እና ሌሎችም ተጠቃሾች ናቸው።

በ. አሁን የሚቀረን በመጽሐፉ ላይ መወያየትና ለሃገራችን የዘር ተኮር ችግሮች የጋራ መፍትሔ ለመፈለግ መሞከር ነው።

ተ. ከመጽሐፉ ሽያጭ ከተገኘው ትርፍ ባለፈው ወር ለሦስት የሰኔ 2012 የዘርና የኃይማኖት ጥቃት ሰለባዎች 30,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል። ከሰሞኑም ለአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ትምህርት ቢሮዎች በስራቸው ለሚገኙ አብያተ መጻሕፍት የ60,000 ብር የሁቱትሲ መጻሕፍት ድጋፍ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል። 

ቸ. ከሚያዝያ 27፣ 2012 ዓ.ም. ጀምሮ በቀን አንድ ጊዜ (ጠዋት ብቻ) ተመጋቢ በመሆኔ በረሃብ አንጀቴ እንደምሰራ ሊታሰብም ይችላል። ክብደቴ አስር ኪሎግራም ያህል ቀንሷል። 

እስኪ የጋራ ጉዟችንን እንወያይበት።

ሁላችሁንም አመሠግናለሁ።

አንዲት ነገር ይፈቀድልኝ።

ደብረብርሃንን በጣም እንደምወዳት ስርቃት ገባኝ። እናም ከመስከረም 2013 ጀምሮ ወደ ደብረብርሃኑ ቤቴ በመመለስ የማሳተምና የማከፋፈል ሥራውን ከዚያ እየተመላለስኩ ወይም ሥራ አስኪያጅ ቀጥሬ እሠራለሁ/አሰራለሁ።

ሌላ ዋና ነገር

ሞትን ንቄው እንደከረምኩ ይሰማኛል። አዲስ አበባን ሲዞር የዋለ ብር ከየመጻሕፍት አዟሪውና መደብሩ እኔ ጋ ቢመጣም ለኮቪድ የነበረኝ ጥንቃቄ ዜሮ ነበር። ሰኔ አንድ የገዛሁት ሳኒታይዘር አሁንም አለ። ይህ ከኔ የሚጠበቅ ነገር ባይሆንም መጠንቀቁ ስለሰለቸኝ ነው።  በማናቸውም ደቂቃ ልወድቅና በዚያው ልቀር እንደምንችል ወይም በተኛሁበት ላሸልብ እንደምችል እየተሰማኝ ሦስት ወር ቆየሁ። ዘጠና ቀናት በሩዋንዳ የነገሰው ሞት በአዲስ አበባም በኮሮና ወረርሽኝ መልክ ማንዣበቡን እሰማለሁ። ይሁን እንጂ ሳይነካኝ ወደ ደብረብርሃን ልመለስ እንደሆነ ይመስለኛል።

አምስተኛው ዕትምስ?

አይ ቆይ፣ ለማተሚያ ቤት ልጆችም እናስብ! ዓመት በዓሉን አረፍ ይበሉና ከበዓል በኋላ ያትሙታል። እስከዚያው መጽሐፉን የገዛን ሰዎች እየተዋዋስን እናንብብ።

2020 ጁላይ 15, ረቡዕ

My Eyewitness Account of the Riot in Addis Ababa

Mezemir Girma, translator of "Left to Tell, Discovering God Amidst the Rwandan Holocaust" to Amharic

June 30 - July 15 2020
Email: mezemirgirma@gmail.com

"Kan nama nyaatu nu keessa jiraa. = The cannibal is among us." Hachalu Hundessa

"Oh, genocide! In Rwanda they were just two ethnic groups. If it comes to Ethiopia? Who knows who kills us? May God save us!" Professor Merera Gudina answering a question I asked him in 2017 on whether he thinks a genocide erupts in our country. I was one of the lecturers who visited him in his party's headquarters in Addis to console him about his expulsion from his teaching position at Addis Ababa University.

An ethnic Amhara mourner who gave an interview to the VoA a week after the current wave of attacks in Oromia Region
said that he suspects that there is a hidden government going operational in this country so as to orchestrate these systematic and selective attacks on his relatives who have been the targets of brutal killings.
This one is an extraordinary observation and awakening unlike some of the Tutsis of Rwanda who believed that the state and everyone in power was doing everything possible to curb genocidal plots.

My esteemed readers,
Instead of this bad news, I wish I announced a certain development program useful for the country. However, today is destined to be the day I sadly scribble what I observed in Addis Ababa.

Tuesday (June 30 - the day after the
assassination of Hachalu Hundesa):
I learned about the death of Afaan Oromo Artiste Hachalu Hundessa from Facebook at 4:00 AM on Tuesday morning. As usual, early in the morning, I walked to my place of work in Biherawi. A few shops and offices opened here and there at that time of the day. I went to the Post Office to mail a dozen copies of my translation of the memoir of a Rwandan woman to Ethiopians in the diaspora. A Post Office worker told me that they don't send to Dubai and Qatar at this time of the COVID 19 pandemic. I carried the books back and placed them at a nearby coffee shop. Customary as it has been during riots in the country, a little after 8:00 AM the internet connection was completely shut down. I couldn't surf the net nor take photos of the fearsome situations. At Biherawi, the financial hub of the nation where almost all bank headquarters are being built, rioters set up roadblocks, and jogged carrying sticks. Broken glass doors and window panes are also seen everywhere. The people who were working, buying and moving in the area were threatened and had to seek refuge in hideouts nearby. I went to the coffee shop and spent the time the raging rioters reigned at. The people hiding speculated that the rioters were heading to Emperor Minelik's statue, located near St. George's Church. This statue, a symbol of the unification of modern Ethiopia, remained a point of contention in the recent Ethiopian political strife. The youth who demonstrated filled the area from the Headquarters of the Ethiopian Broadcasting Corporation to the Black Lion High School, about a hundred metres long. They were encircled by armed security personnel. As the situation escalated, I went back to a place near my home in Lideta. I sat at the veranda of a cafe, on a second floor of a building opposite Lideta Park. In a motorway about a hundred metres from where I was the youth from the neighborhood were fighting with the rioting youth who were carrying sticks. Hurling stones at the stick-carrying youth, these boys who were not more than twenty in number, were receiving flying sticks in return. Police intercepted and the fighting stopped. While all this was unfolding, people at the cafe, some of whom old enough to be grandparents, were complaining about the time and situation God let them live to see. They reprimanded the boys from Addis to stop throwing rocks. They warned the defenseless people living outside of Addis Ababa would be victims of retaliatory measures the rioters may take when they go back home.

Wednesday (July 1):
On this day, I headed to my work place only to find all businesses closed. There were few cars on the road. One of the very busy traffic-light stops at Lagare had only one car from each of the four directions. Security got tighter. Armoured personnel carriers (APCs) were seen here and there. The military also went out of their barracks to calm the nation down. Ethnic-based attacks, the burning down of properties and other forms of violence in parts of Addis Ababa and its outskirts were said to take place. Towns within the Oromia Regional State were also said to have entertained similar incidents. Top government officials gave briefings and press releases. Opposition politicians, journalists and people suspected of plotting to create havoc were reported to have been imprisoned. At a cafe, I saw Aljazeera's news coverage on the incident. They concluded the report by reminding their viewers that the Oromo were the largest ethnic group deprived of political and economic rights in the country.

Thursday: (July 2)
Artiste Hachalu Hundesa's remains have been buried in the morning. I heard the program live from Ambo Stadium and the funeral site from the radio on my phone. My cute memories of a week I spent in the beautiful Ambo town started to recollect. I had no radio receiver or TV set in the week the riot took place to comfortably check from foreign media. I sat at Wabe Shebele Hotel in the afternoon when I learned with difficulty from the low sound of the TV an Aljazeera broadcast. They reported about the burial of the artiste. On this very day, local FM stations reported that certain political parties and their agents were held responsible by authorities for the incidents in the metropolis. The government gave briefings and releases through the Public Prosecutor, the PM, his deputy, the Mayor of Addis, and Oromia's President among others.
Many of my friends and relatives called to check my well-being and I also did the same to those living in Addis in return. People I met on this day asked me if the rioters came to our house at night and I told them that they didn't. Rain played key roles in preventing demonstrators from accessing the in and outs of the city. As far as I am concerned, nothing is heard in the compound I live in or nearby. The people who asked me, on the contrary, told me that there were such tough cases.

Friday (July 3):
As the Mayor of Addis Ababa Engineer Takele Uma had ordered the day before, normal business resumed. Those who lost their loved ones, who were enjured and those who lost their properties need a long time to recover. Internet connection is not yet back. The net surely helps businesses, but its negative sides of serving as a means of disseminating hateful messages to masses surely continues. It took me more than 15 days to air this observation due to the internet shutdown.

My take:
The assassination of celebrities is a major initial action that planners of attacks take. Even the First World War had the assassination of a member of a royal family as an immediate cause. Immediate causes could help ignite, however, in most cases bloodshed, civil wars, genocides or any other forms of public unrest happen as a result of carefully-planned plots. Strict proactive measures must be taken to prevent bloodshed and the massacre of innocent civilians of whatever background. The incidence of the assassination of Juvenile Habyarimana, the president who ruled Rwanda before the genocide, was planned to take place on March 23, 1994. Nonetheless, for their convenience the plotters of the genocide decided to execute it at midnight on the 6th of April 1994. Innocent Tutsis and moderate Hutus were wiped out afterwards. The then exiled Rwandan Patriotic Front, which had no means to  fire rockets from near the airport in Kigali, was held responsible for the shooting down of the plane carrying Habyarimana and his Brundian counterpart. This fabricated pretext was used to resume the genocide the world watched indifferently.
I was in Addis Ababa last October when a more or less similar riot to the current one broke out. At that time, it happened mostly in the outskirts. More than eighty people were reportedly killed in Oromia. By sheer coincidence, I followed the inception and immediate cause of the October violence from social media at night. The current one also started at night. I really feel deeply worried when by coincidence I happen to learn about such protests that are waged at night because the starting of the Rwandan genocide by midnight reverberates in my mind. As the October incidence began, I disclosed on Facebook that I was leaving for a week-long wokshop in Ghana. A friend messaged, "Are you leaving us for death?" The current one has grown quite intense and threatened everyone. It reminds one of the fable about the frog that thought her hideout of a pond was safe when a wildfire set a nearby jungle ablaze. The scope and scale of this week's youthful outrage was larger as it battered even downtown Addis Ababa. On the other hand, in October, security was loose, yet this week authorities are seen making it tighter than before! Who can tell where our country is heading? Leave alone the defenseless mass like me, celebrities, rich people and Ethiopian holders of other passports cannnot escape such sudden situations. Travel restrictions the COVID 19 pandemic caused made every Ethiopian national staying currently in their home country more vulnerable. We are all locked in to seek together workable solutions to the most pressing of problems this country of 3000 (or as some politicians claim, 100) years  is facing - ethnically-motivated plots, riots and attacks. Who knows how intense the next rage or riot may be?
I should take this opportunity to express my heartfelt grievances for all those Ethiopians of all backgrounds who lost their precious lives due to the well planned and ethnically motivated assaults. Not only this, I also really feel very sad for the plotters and their accomplices for going very cruel in as far as setting this trap for their country in an attempt to quench their lust for power and money!
Whether Ethiopians will open their hearts to the unifiers or cessationists in the upcoming elections remains the million dollar question!
P.S. The detailed reports that I heard on the days after the hateful and tragic occurrences from the informants of the Voice of America and Deutsche Welle from the butchering sites were really heartbreaking! People were singled out and attacked because of their ethnic and religious backgrounds. Lists of targets were made ready before the attacks. The attacks systematically orchestrated and made innocent civilians their victims! Meanwhile in Addis Ababa people organized themselves to defend their neighborhoods irrespective of their ethnic backgrounds.

2020 ጁን 25, ሐሙስ

መጽሐፍ ግምገማ

መጽሐፍ ግምገማ

በደራሲ ጥላሁን ጣሰው 

መዘምር ግርማ “ሁቱትሲ” በሚል ርዕስ የተረጎመውን የኢማኪዩሌ ኢሊባጊዜ መጽሐፍ አንብቤዋለሁ። ስለተርጓሚው የቋንቋ ጥራትና ምጥቀት ዶ/ር ያዕቆብ ለመጽሐፉ ከሰጡት ቀዳሜ ቃል በላይ የምለው የለኝም። በዚህ ግምገማ የማተኩረው በመጽሐፉ ውስጥ ከምንተዋወቃቸው ሰዎች ሦስቱን በመውሰድ ከወግ፣ ሃይማኖትና ባህል በመነሳት ንጽጽር በማድረግ ቀደም ብለው መጽሐፉን ያነበቡት በጥልቀት እንዲያስተውሉት፣ ያላነበቡትና ወደፊት የሚያነቡት ትኩረት እንዲያደርጉበት አጽንዖት ለመስጠት ነው።
ኢማኪዩሌ ሐጢያትና ክፋት ሳይኖራት እንደ እዮብ በፈተና ውስጥ የምታልፍ ናት። ትምህርት ቤት ውስጥ ዘረኛው መምህር ሁቱዎች ቁሙ፣ ቱትሲዎች ቁሙ፣ቱዋዎች ቁሙ እያለ ሲጠይቅ የምን ዘር (በመዘምር አማርኛ ዘውግ) እንደሆነች ስለማታውቅ ከመቀመጫዋ ሳትነሳ የቀረች ልጅ ነበረች። ወላጅ አባቷ ይህን ሲሰማ መምህሩን በማነጋገር ይህን አወጋገን እንደተቃወመ ይሰማናል። መምህሩ ግን ኢማኪዩሌን በክፍል ውስ ጠርቶ ቱትሲ ስል ትቆሚያለሽ ብሎ ይነግራታል። ይህች የዋህ፣ ቅን ሰው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደምናገኘው እግዚአብሔርን የሚፈራ ግን የሚፈተን ሰው እሷም በእግዚአብሔር ቸርነት በወላዲት አምላክ አማላጅነት ለወሬ ነጋሪ የተረፈች እንደሆነች ትነግረናለች።
በወቅቱ የሩዋንዳ ሕብረተሰብ በአደገኛ የሥነልቦና ቀውስ ውስጥ መሆኑን ለማሳዬት በመጽሐፉ ውስጥ የምናገኛቸው ቄሱን ነው። ቄሱ ከፍራትና ከጥቅም አንጻር ነገሮችን በማዬት እንደ ጲላጦስ ለመሆን እንኳን የማይደፍሩ ናቸው። “እኔ ከደሙ ንጹህ ነኝ  በነዚህ ሰዎች ላይ አልፈርድም” ለማለት እንኳ ድፍረቱ የላቸውም። እንደ አንድ ሃይማኖት አባት “ሁላችሁም የአንድ ቤተክርስቲያን ልጆች ናችሁ። ማንም በወንድሙ ላይ ቆንጨራ ቢመዝ ሃጢያተኛ ነው። ይህን ተላልፎ ወንድሙ ላይ እጁን ለመሰንዘር የሚፈልግ በኔ እሬሳ ላይ ይራመድ።” ብለው ለማውገዝ ጥንካሬ የሌላቸው ናቸው። በቅርቡ ክርስቲያንና ሙስሊም ተጓዦች ላይ ኬንያ ውስጥ አልሸባብ ነጣጥሎ ለመግደል ሲሞክር እስላሞቹ ክርስቲያኖቹን ከገደላችሁ እኛንም ግደሉን ያሉበትን ያህል መንፈሳዊ ጥንካሬ ለመንፈስ ልጆቻቸው ሞት አላሳዩም። ሴቶቹን ደብቀው የሚያስቀምጡበት ዓላማም ከወደፊት ጥቅም አንጻር የተሰላ መሆኑ የሚታወቀው ምስኪን ተደባቂዎቹን የተደባቂዎቹ ዘር በደል ይፈጽም ነበር ብለው በማውራት ሲያሸማቅቋቸው ነው። እንደ አንድ መንፈሳዊ አባት “እናንተን እግዚአብሔር የሚፈትናችሁ ስለሚወዳችሁ ነው። ብጸዕ ናችሁ ። ፈተናውን ታልፉታላችሁ። በናንተ ላይ የሚፈጸመው ሁሉ ትክክል አይደለም።” ብለው አያጽናኑም። ራሳቸው ተስፋ አጥተው ተደባቂዎቹንም ተስፋ ቢስ ያደርጋሉ። ይልቁንስ ቄሱ በፍራት ተውጠው የሁቱ ጽንፈኞችን ሃሳብ እንደሚደግፉ ለጽንፈኞቹ ዘረኞች በመናገር ቀውሱን ያባብሱታል። እንደ አንድ መንፈሳዊ አባት ሁላችሁም ልጆቼ ናችሁ። አንዳችሁን ከአንዳችሁ አላበላልጥም። ምህረትና ትህትና እናገራለሁ።” ለማለት አልቻሉም። አንዲቷን ቤተክርስቲያ በዘር ከፋፈሏት ማለት ነው። ሁቱዎች ብቻ የሚያመሰግኑባትና የሚቀድሱባት ዓይነት። በዘመኑ ሩዋንዳ በመንፈስም ደረጃ የደረሰችበትን ዝቅጠት አመላካች ገጸ ባሕሪ ናቸው።
የኢማኪዩሌ አባት በመንግሥት ከአድልዎ ነጻ የሆነ ሥርዓትና ሕጋዊነት የሚያምን ነው። ስለዚህ በትምህርት ቤቶች በዘር የሚከፋፍለውን አስተማሪ ለማስተካከል በከንቱ እንደሞከረው ሁሉ ጭፍጨፋው በጀመረበት ወቅት የዘር ጭፍጨፋውን አቃጅና አስፈጻሚ ለሆኑት የመንግሥት ሹማምንት እየተሠራ ያለው ሥራ ትክክል ስላልሆነ የመንግሥት ሹማምንት ጣልቃ ገብተው በሃላፊነት ጭፍጨፋውን እንዲያስቆሙ ሲወተውት በዚያው የመንግሥት መሥሪያ ቤት የሚገደል ነው። ወንድ ልጁ ፍጅቱን ለማቆም ወይም ካልተቻለ ለመሰደድ የሚያቀርብለትን ሃሳብ በመንግሥትና በሕግ በመተማመን በእንቢታ የቆመ አባት ነው። የመንግሥት መዋቅሮች የዘር ሴራ ማውጠንጠኛ በሆኑበት ሁኔታ በመንግሥትና በሕግ ላይ እንደዚህ የጸና እምነት ያለው ሰው በሃይማኖትና ዓለማዊ መጽሐፎች ውስጥ ማነጻጻሪያ ሊሆን የሚችል ለጊዜው ትዝ አይለኝም። መኖሩንም እጠራጠራለሁ። የኢማኪዩሌ መጽሐፍ የዚህ ዓይነት ተምሳሌት ፈጥሯል።
በኢማኪዩሌ መጽሐፍ ውስጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የምናውቀውን ጳውሎስን የሚስተካከል ሁቱ ተወላጅ አናይም። ቅዱስ ጳውሎስ ክርስቲያኖችን አሳዳጅ የነበረ ሲሆን በኋላ ተመልሶ ለክርስትና መስዋዕት የሆነ ነው። በሩዋንዳ አማጽያን ካምፕ ሁቱዎችን ብናይም በአደባባይ የቱትሲ መግደያ መሣሪያውን ጥሎ “ከእንግዲህ በቃኝ። በቱትሲዎቸ ላይ እጄን አላነሳም። ብትፈልጉ እኔንም ግደሉኝ፣’’ ብሎ ነውጠኞቹን የሚጋፈጥ ሰው በመጽሐፉ አይታይም። እንዲህ ዓይነት ሁቱዎችን ለምፍጠር ምናልባት በመሸሽ ፈንታ ተፋጥጦ በመቆም ብትፈልጉ ግደሉኝ ሃሳባችሁ ትክክል አይደለም የሚሉ ቱትሲዎች በብዛት ባለመኖራቸው ጥቂት የጳውሎስ ዓይነት ሁቱዎች አልወጡ ይሆናል። ይህ ከሆነ ደግሞ የሩዋንዳ ሕብረተሰብ በዚያን ወቅት የመጣበትን መዓት ለመቋቋም የማይችል ነበር ማለት ነው። 
በኢማኪዩሌ መጽሐፍ ውስጥ ቀሳውስቱ በመንፈስ ልጆቻቸው መሃከል በፍራትና በጥቅም ታውረው ቤተክርስቲያኒቱ የዘር ቅርጽ ስትይዝ ሳይከላከሉ፣ የመንግሥት ተቋማት የዘር አድማና ሴራ መጠንሰሻ ማዕከልነት ተቀይረው በሌላ በኩል ደግሞ ሕዝቡ ይሆናል ብሎ ከመጠንቀቅ አይሆንም በሚል ተስፋ ጸጥ ብሎ ቆሞ እናገኘዋለን። ሩዋንዳ ወደ ፈተና ገባች። ክፉው ሁሉ ተፈጸመባት።በቸርነቱ የተረፉት ቂምን ሳይሆን ምህረትን አደረጉ። የኢማኪዩሌ ታሪክ ይህ ነው።
መዘምር ተርጉሞ ስለቀረበልን ምስጋና ይግባው። ልብ ያለው አንባቢ ልብ ይበል።

2020 ሜይ 31, እሑድ

ሁቱትሲ


ሁቱትሲን ላላነበባችሁ ወዳጆቼ ለቅምሻ ያህል እነሆ፤
ሁለተኛው ዕትም እስኪወጣ።

መግቢያ
ኢማኪዩሌ እባላለሁ
ገዳዮቹ ስሜን ሲጠሩ ሰማኋቸው፡፡
እኔ በግንቡ በአንደኛው በኩል ስሆን እነሱ ደግሞ በሌላኛው አቅጣጫ ናቸው፤ አንድ ጋት የማይሞላ ውፍረት ያለው ጭቃና ዕንጨት ብቻ ይለያየናል፡፡ ንግግራቸው ጭካኔ የሚንጸባረቅበትና ቆርጠው መነሳታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
‹‹እዚህ ነችእዚህ የሆነ ስፍራ እንዳለች እናውቃለን፡፡ …. ፈልጓት - ፈልጓት ኢማኪዩሌን፡፡››
አካባቢው በሁካታ ተሞላ፡፡ ብዙ ገዳዮች መጥተዋል፡፡ በአእምሮዬ ይታዩኛል - ሁልጊዜ በፍቅርና በደግነት ሰላምታ ይሰጡኝ የነበሩ የቀድሞ ወዳጆቼና ጎረቤቶቼ በቤቱ ውስጥ ጦርና ገጀራ ይዘው ስሜን እየጠሩ ይዘዋወራሉ፡፡
‹‹399 በረሮዎችን ገድያለሁ›› ይላል አንደኛው ገዳይ፡፡ ‹‹ኢማኪዩሌ 400 ታደርግልኛለች፡፡ ይህን ያህል ከገደልኩ ምን እፈልጋለሁ!››
በትንሿ ምስጢራዊ መታጠቢያ ቤታችን ጥጋት አንድስ እንኳን የሰውነቴን ክፍል ሳላላውስ ተሸሽጌያለሁ፡፡ እንደኔው ሕይወታቸውን ለማትረፍ እንደተደበቁት ሌሎች ሰባት ሴቶች ሁሉ ገዳዮቹ ስተነፍስ እንዳይሰሙኝ ትንፋሼን ውጫለሁ፡፡
ድምጻቸው የሠራ አከላቴን ገማመሰው፡፡ በከሰል ፍም ላይ እንደተኛሁ፣ እሳትም ላይ እንደተጣልኩ ተሰማኝ፡፡ መላ ሰውነቴ የሕመም ውርጅብኝ ወረደበት፡፡ ሺህ የማይታዩ መርፌዎች ተቸከቸኩብኝ፡፡ ፍርሃት እንደዚህ የሚያርበደብድ ስጋዊ ሥቃይ ያስከትላል ብዬ አስቤ አላውቅም፡፡
ለመዋጥ ሞከርኩ፤ ጉሮሮዬ ግን ተዘግቷል፡፡ ምራቅ አልነበረኝም፤ አፌም እንደ ኩበት ደርቋል፡፡ ዓይኖቼን ጨፈንኳቸው፤ ራሴንም ለመደበቅ ሞከርኩ፤ ንግግራቸው ግን እየጎላ መጣ፡፡ ምንም ዓይነት ምኅረት እንደማያደርጉልኝ አውቃለሁ፤ በአእምሮዬም አንድ ሐሳብ ያስተጋባ ጀመር - ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ ይገድሉኛል
ገዳዮቹ በራፉ ላይ አሉ፤ በማንኛዋም አፍታ እንደሚያገኙኝ አውቃለሁ፡፡ ገጀራው ቆዳዬን አልፎ ሲገባና አጥንቴ ድረስ ሲቆራርጠኝ የሚሰማኝ ስሜት ምን እንደሚመስል አሰብኩት፡፡ ወንድሞቼና ወላጆቼም ትዝ አሉኝ፤ ሞተው ወይንም በሕይወት እየኖሩ እንደሆነ፣ በገነት ከአፍታ በኋላ እንገናኝም እንደሆነ አለምኩ፡፡
እጆቼን እርስ በርሳቸው አጣመርኳቸው፤ የአባቴን መቁጠሪያም ጥብቅ አድርጌ ያዝኩ፤ በለሆሳስም መጸለይ ጀመርኩ - እባክህ እግዚአብሔር ሆይ፣ እባክህ እርዳኝ፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ እንድሞት አታድርገኝ፣ እንደዚህ አይሁን፡፡ እነዚህ ገዳዮች እንዲያገኙኝ አታድርግ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስህ ከጠየቅን እንደሚሰጠን ትነግረናለህእንግዲህ ጌታዬ እየጠየኩህ ነው፡፡ ወይ በለኝ፡፡ እባክህን እነዚህን ገዳዮች ወዲያ እንዲሄዱ አድርጋቸው፡፡ ኧረ በዚህ መታጠቢያ ቤት እንድሞት አታድርገኝ፡፡ እባክህ፣ እግዚአብሔር፣ እባክህ፣ እባክህ፣ እባክህ አድነኝ፡፡
ገዳዮቹ ከቤቱ ወጥተው ሄዱ፡፡ እኛም እንደገና መተንፈስ ጀመርን፡፡ ሄደዋል፤ ሆኖም ግን በቀጣዮቹ ሦስት ወራት ውስጥ ብዙ ጊዜ ይመላለሳሉ፡፡ ሕይወቴን እግዚአብሔር እንዳተረፋት አምናለሁ፤ ሆኖም ቁምሣጥን በምታክል መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ከሰባት ሌሎች ሰዎች ጋር በፍርሃት እየተርበደበድኩ ባሳለፍኳቸው 91 ቀናት መትረፍ ከመዳን በጣም የተለየ አንደሆነ እማራለሁይህ ትምህርትም ለዘለቄታው ለውጦኛል፡፡ ይህ ትምህርት በጅምላ ጭፍጨፋ ውስጥ የሚጠሉና የሚያሳድዱኝን እንዴት መውደድ እንዳለብኝ - ቤተሰቤን ያረዱትንም ሁሉ እንዴት እንደምምር ዕውቀት የቀሰምኩበት ነው፡፡
ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡ ይህ በታሪክ ብዙ ሕዝብ ካለቀባቸው ጭፍጨፋዎች በአንዱ እግዚአብሔር እንዴት እንደተገለጠልኝ የሚያሳይ ታሪክ ነው፡፡

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...