2017 ኦክቶበር 25, ረቡዕ

ብድር ማስመለስ ተሳነን፤ ወይ ማስያዣ አልያዝን!





‹‹አበዳሪው ምን ያርግ ብሩ እንዲወልድለት
ተበዳሪው ምን ያርግ ልጆቹ እንዲያድጉለት
እኔስ የገረመኝ የዋሱ ሞኝነት››
ለአሁኑ ችግራችን የሚሆን የህዝብ ግጥም ስላጣን ይህን ተያያዥ ግጥም በመጋበዝ ጀመርን፡፡
1. በክፍል ጓደኛ መጭበርበር
2003 በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኤፍ ካምፓስ የሚማርና በአንድ የምስራቅ ኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ የሚያስተምር ቆንጆ ልጅ ነበር፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በድባብ መናፈሻ ሁሉም ጓደኞቹ ፀሐይ እየሞቁ ክፍለጊዜ እስኪደርስ ያሙታል፡፡ ከነዚህ ጓደኞቹ አንዱ ጓደኛዬ ስለነበር አጠገባቸው ሆኜ አዳምጣለሁ፡፡ አንዱ ልጅ ይህ ጓደኛቸው ስልክ አስደውለኝ እንዳለውና እንዳስደወለው፤ ካስደወለው በኋላ ሲያይ ግን ጓደኛቸው በስልኩ ውስጥ ገንዘብ እንደነበረው ይረዳል፡፡ ቁጭቱን በሆዱ ያዝ አድርጎ ዝም! ሁሉም የተነጠቁትን ገንዘብ እየተናገሩ ተደመረ፡፡ ብ ….. ዙ ብር ሆነ፡፡ ልክ የአገራችን ብሔራዊ ዕዳ በአሁኑ ሠዓት እንደበዛው ካቅሙ በላይ ሆነ፡፡ ይህ ልጅ ለመበደሩ ምክንያቱ ምን ይሆን? አመል ሳይሆን አይቀርም፡፡ ትምህርታቸው ስለገንዘብ ነገሮች በመሆኑ አንድ ቀን መምህራቸው ስለብድር አመላለስ ሲያስተምሩ እያቃለዱ ጠየቁ አሉ፡፡ እንዲህ በማለት "ከዚህ ክፍል ተበድሮ የማይመልስ አለ?" በማለት፡፡ ተማሪው ሁሉ ወደዚያ ዞረ አሉ፡፡ "ያልመለሳችሁ ቶሎ መልሱ ብድራችሁን" ብለው ትምህርቱን ቀጠሉ መምህሩ፡፡ ተማሪው በሳቅ!
2. በሰፈር ሰዎች መታለል
ዛሬ ከዚህ ያልተናነሰ ዚቅ ደብረብርሃን ተከሰተ - በሰባት ዓመቱ፡፡ ጓደኛሞች ተሰብስበን አንዱ ደወለልኝ፡፡ "ይህን ስልክ አላነሳም፤ 1000 ብር ነጥቆኛል" ብዬ ተናገርኩ፡፡ ከዚያም በቅደም ተከተል ገንዘብ የቀሙኝን በምሬት ዘረዘርኩ፡፡ ‹‹ጥሬ ገንዘብ ቆጥሬ ሰጥቼ!›› ተጀመረ ምክንያታዊ ቡጨቃ! "እኔንም ይሄን ያህል አስቀርቶብኛል! ከኔም ስንትና ስንት ብር ነጥቃኛለች! ደሞ ክህደቷ፡፡ እኔማ በኔ ሞኝነት እንዳልወሰደችው ነግሬያታለሁ፡፡ ሰጥቼሻለሁ የምትለው ደሞ!" መባባል ተጀመረ፡፡ የተበደሩባቸው የውሸት ግን ለጊዜው አሣማኝና አሣዛኝ ምክንያቶች ተነሱ፡፡ የጋራ ንግድ እንጀምር በማለት፣ የእቁብ ገንዘብ ሳይከፍሉ ከፍያለሁ በማለት፣ እቃ ወስዶ ባለመክፈል፣ የማትፈልገው ብር ካለህ ነገ እመልስላሃለሁ በማለት …. ፈልጌህ ነበር ብሎ ረፍት ነስቶ አገር የተሸበረ አስመስሎና ስትመጣ ጉዳዩን እነግርሃለሁ ብሎ ከስራ ቦታ ድረስ አሯሩጦ በማስመጣት፣ በቁልምጫ በመጥራትና የገሬ ልጅ እያሉ በማባበል፣ በርካታ ፈጠራ የተሞላባቸው ምክንያቶችን በመደርደር፡፡ ምን ነበር ጓደኝነትን ለሚያጠናክርና ለመልካም ነገር ፈጠራ ቢፈልጉ?
ለማስመለስ የተደረጉ ጥረቶች ተወሱ፡፡ በሞባይል ሜሴጅ ምላሽ የሚሰጡ አሉ፡፡ ‹‹አንቺ ጥሩ ልጅ አልነበርሽም ወይ? ለዚች ብር ምን እንደዚህ ያደርግሻል! ካገር አልጠፋ! አክስታችን ሞታ አገር ቤት ሄጄ ነው፡፡ (ሦስት ደርዘን አክስት ያላ ይመስል በየቀኑ አንድ ትገድላለች!)›› የትዳር አጋሮቻቸው አማላጅነት እንኳን አለመስራቱ ተወሣ፡፡ ባልና ሚስት ካንድ ‹አጭበርባሪ› ባህር ይቀዳሉ እንዲሉ፡፡ ያላበደሩት ሰዎች ምን አለባቸው! ዛሬም መልካም ጓደኝነታቸውን አስቀጥለዋል፡፡ ወጥመዱን እንዴት እንዳለፉት ያወሳሉ! ያበደርን ግን ወይ ምስጋና የለ፣ ምን የለ! ተበድረው ቤታቸውን ያደራጁ እንዳሉ ሁሉ በብሩ የተዝናኑበትም አይጠፉም፡፡ ነገ ብዙ ጓደኞቻችን ሲመጡና የአውጫጭኙን መጀመር ሲረዱ የየራሶቻቸውን ታሪኮች በቁጭት ያወጋሉ፡፡ ለማሸማቀቅ ብፈልግ እነዚህን ተበዳሪዎች ታግ አደርጋቸው ነበር፡፡ ገጠመኝ ካላችሁ ተጨማሪ የማጭበርበሪያ መንገዶቻቸውን ንገሩን፡፡ እስከዚያው የናንተን ገጠመኝ ፃፉልኝ፡፡ ወስደው ያስቀሩባችሁንም ኮሜንት ላይ ስማቸውን ጽፋችሁ መልሱልኝ በሉ፡፡
3. አጥማጅ የስራ ባልደረቦች
እስከ 2005 ድረስ ለበርካታ የስራ ባልደረቦቼ አበዳሪ ነበርኩ፡፡ ደሞዝ እስኪመጣ ድረስ ማን ጋ ስንት ብር እንዳለኝ ሳስብ እከርማለሁ፡፡ እንትና ጋ 65፣ እንትና ጋ 1200፣ እንትና ጋ 2000፣ እንትና ጋ 34 ወዘተ፡፡ ወይ አልጽፈው! ወይ ባንክ አይደለሁ! ወይ ባይመልሱ ማስያዣ አልያዝኩ! ደሞዝ ሲመጣ የሚመልሱ አሉ፡፡ የማይመልሱም አሉ፡፡ ስድስት ወር አቆይተው የሚያመጡም አሉ፡፡ ባገኙኝ ቁጥር ‹‹ብርህን ሳልመልስ፤ ቆይ ደሞዝ ሲመጣ›› የሚሉኝ አሉ፡፡ ከተበዳሪው በላይ ስሳቀቅ ቆየሁ፡፡ ዓይናቸውን አየት ሳደርግ ብሬን አምጣ የሚል አስተያየት እንዳይመስልብኝ ስሰጋ እቆያለሁ፡፡ ‹‹ከባለፈዋ ጋር የሚመለስ 200 ብር ጨምልኝ›› እባላለሁ፡፡ ከባንክ አውጥቼ ሰጥቼ ሲመልሱልኝ ባንክ አላስገባውም፡፡ አባክነዋለሁ፡፡ ቢመልሱም የቆብኩትን አስጠፉኝ ማለት ነው፡፡ ቆይቶ ተበዳሪዎቼን ማራቅ ጀመርኩ፡፡ አንዱ ገንዘብ ቸገረው፡፡ መሄጃ አጣ፡፡ በየወሩ የማበድረው እኔ ነበርኩ፡፡ አትምጣብኝ ብዬዋለሁ፡፡ ከነጓደኛው ‹‹ክፉ ሰው›› የሚል ስም አውጥተውልኛል፡፡ ታዲያ ክፉ ሰውን እንዴት አበድረኝ ይበል፡፡ ምላሼንም ይገምታል፡፡ ሌላ ጓደኛውን ጠይቆት ኖሯል፡፡ ያ ጓዳኛው ደግሞ ምንም ሱስ የሌለበትና ተበድሮኝ የማያውቅ ነው፡፡ ‹‹ኤቲኤም አልሰራ አለኝ፤ ነገ ሰኞ የምሰጥህ 300 ብር ስጠኝ›› ሲል ጠየቀኝ፡፡ ሰጠሁት፡፡ ወዲያውኑ አብሮን ለነበረው ለዚያ ጓደኛችን ሰጠው፡፡ እሱም ‹‹እኔ ከሱ አልፈልግም፤ ይቅርብኝ›› አለ፡፡ በልምምጥ ተቀበለው፡፡ ገንዘብ ቆጥብ ስለው የማይሰማኝ ሰው ለምን ገንዘብ ይጠይቀኛል ብዬ ስለማምን ነበር በሱ ላይ ያን ውሳኔ የወሰንኩት፡፡ ወስዶም ለሱስ ነው፡፡ ተበድሮኝ አያውቅም፡፡ ጓደኛ ራሱን እንዳያሻሽል መንስኤ መሆንም ይመስለኛል ማበደር፡፡ አሁን የስራ ባልደረቦቼን የአበድረኝ ጥያቄ ፈጽሞ አስቀርቻለሁ፡፡
ለመሰናበቻ፡፡ ምን ጊዜም ስንጽፍ የልጅነታን ነገር ትዝ ይለናል - ያለፈው፡፡ ሳሲት ከተማ ላይ አንድ ደግ ሰው አለ፡፡ ባም ጋባዥ ነው፡፡ ሰዎች ስለሱ ሲያወሩ የሰማሁት ነገር ይገርማል፡፡ ‹‹ጋሼ እኮ ከተበደረም አይመልስም፤ ካበደረም አይጠይቅም›› ያሉት ነገር ገርሞኛል፡፡ የማይመልሰው እየረሳው ሳይሆን አይቀርም፡፡

2017 ኦክቶበር 5, ሐሙስ

የቱ ግቢ?


ግቢ የሚለው ቃል ሲነሳ በእርስዎ አእምሮ ምን ይመጣል?
ጽሑፉን ከማንበብዎ በፊት አስተያየት መስጫው ላይ ይጻፉልኝ፡፡
ሁለት ዲያቆናት ግቢ ሲሉ የቤተክርስቲያኑን ቅጥር ግቢ ለማለት ይሆናል፡፡
ሁለት ሸኮች የመስጊዱን
ሁለት እስረኞች የእስር ቤቱን
ሁለት ኮማሪቶች የሆቴሉን
ሁለት ዳኞች የፍርድ ቤቱን….
በዕድሜ መስመር ወደ ኋላ ሄጄ ሳስብ ‹ግቢ› አንድ ትርጉሙ ይታየኛል፡፡ ይኸውም የብረታብረትና የሸክላ ስራ የሚሰራባቸው ስፍራዎች ግቢ ይባሉ ነበር፡፡ አንድ ሰው ‹‹እስቲ ግቢ ልሂድና ማጭድ ላሰራ፣ አያ ታችበሌ›› ሊል ይችላል፡፡ እነዚህ የዕደጥበብ ሰራተኞች ተገልለውና የራሳቸውን ሰፈር መስርተው የሚኖሩበት ቦታ ግቢ እንደሚባልና ልጆች እንደማይሄዱበት እናውቃለን፡፡ ተከብሮና ተፈርቶ የሚኖር አካባቢ ነው፡፡ ለመንደሩ ምስረታ መነሻ የሚሆነው ግን ሰዎቹ በማህበረሰቡ መገለላቸው ነው፡፡ እነሱም ወደ ሌላ ሰፈር እንዲሄዱ አይፈለጉም፡፡ ማህበር፣ እድር፣ ጋብቻም ውስጥ አይካተቱም፡፡ ዉበት አላቸው ቢባልም አይቀርቧቸውም፡፡ ሰውን አተኩረው ካዩ ‹ቡዳ› ተብለው ይሰደባሉ፡፡ ሲደነግጡ ‹አይበሉም› ስለሚባል - መብላት ብሎ ጣጣ! አሁንም ይህኛው የግቢ ትርጉሙ ነው በአእምሮዬ የሚመጣው፡፡ ‹‹ማጭድ ላላሰራ ወይ ቢላዋ፤ ግቢ አልሄድም›› ዓይነት ሃሳብ በውሳጤ ይመላለሳል ግቢ በተነሣ ቁጥር፡፡
ጊዜ ያነሣቸው ቃላት
ግቢ የሚለውን ቃል አሁን አሁን በተደጋጋሚ መስማቴ በፊት የነበሩ አንዳንድ ዘመን - አመጣሽ ቃላትን እንዳስታውስ ያደርገኛል - በሰፈርም ሆነ በፖለቲካው ዘንድ ሰው ሙጭጭ የሚልባቸው ቃላት ነበሩ፡፡ አሁንም ወደፊትም ይኖራሉ፡፡ ‹‹እንደ ወረዳ፣ ከዚህ ጋር ተያይዞ፣ ቀላል፣ አደል…›› የመሳሰሉትን አስታወስኩ፡፡ ‹‹እንደ ወረዳ›› ሲሉ ‹‹እነዚህ ሰዎች ይህ ወረዳ ለአቅመ-ወረዳ አልደረሰም ማለታቸው ነው፤ ወይስ ወረዳ ተብዬ ማለታቸው ይሆን እላለሁ›› ጥሬ ቃሉን ብቻ እያሰብኩ፡፡ ድንገት ቦግ ያለች አጠቃቀም ነች፡፡ ቃሉ ሳይበረዝ በፊት ‹‹እንደ እህት ሆና አስታመመችኝ›› የመሳሰሉትን አባባሎች አስታውሳለሁ፡፡
‹‹ተው አትሽጥ ሲሉት በሬውን ሸጠና
ተው አትግዛ ሲሉት ምንሽር ገዛና
ደሞ እንደ ወንዶቹ ቆላ ወረደና
ሲነፋጠጥ መጣ ነጠቁኝ አለና››
በሚለው የቃል ግጥም ውስጥ ‹እንደ ወንዶቹ› ከሚለው አንጻር እዩልኝ እንደ ወረዳን - አስፋልት-የለሽ ወረዳ - ማለታቸው ይመስለኛል፡፡
የዩኒቨርሲቲ መምህራንስ?
በዚህ ጉዳይ ላይ ውይይት እንዲነሳ አድርጌ ነበር፡፡ ለማ ሚደቅሳ ‹ግቢ› ከበፊትም የነበረ እንደሆነና የሱ ታላላቆች ሳይቀር ይጠቀሙት እንደነበር ትዝ ይለዋል፡፡
አማን ቃዲሮ ግን ‹‹ግቢ ዩኒቨርሲቲን አይወክልም፡፡ የምን ግቢ ነው የሚወራው? ግቢ ኮምፓውንድ ነው እኮ፡፡ ስለ ካምፓስ ስለሆነ የምናወራው አንድ በሉኝ›› ይለናል፡፡
ለማ በበኩሉ ‹‹‹ግቢ እንገናኝ› ይባላል፤ ማለትም - ካምፓስ - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ - 6 ኪሎ - 5 ኪሎ መሆኑ ነው›› ሲል ይቀጥላል፡፡ ሁለት ከምፓስ ሲኖር ዋናው ግቢምሚባ ነገር አለ፡፡ አአዩ ለዚህ አንድ ምሳሌ ነው፡፡ ‹‹በሌላ በኩል ሰፈራችን ውስጥ የያንዳንዱ ሰው ቤት ግቢ ነው››፡፡
አሁን ግቢ በጣም ዝነኛ ከመሆኑ የተነሣ አንድ ግቢ በሚል ቃል የሚጀምር አደረጃጀት አለ - ግቢ ጉባኤ ይባላል፡፡ ሰለግቢ ጉባኤ የሰማሁት ከዐሥር ዓመት በፊት ስለነበር ይህ ቃል እውነትም የቆየ ይሆን እንዴ አሰኝቶኛል፡፡ በተያያዘ ዜና ‹ግቢ› ቤተመንግስትንም ያመለክታል፡፡ ግቢ ገብርኤል የተባለው ለዚያ ይመስለኛል፡፡
እኔ ስማርም አልፎ አልፎ ቃሉ - ግቢ - ጥቅም ላይ ይውል የነበረ ይመስለኛል፡፡ ኦሮሞ ጓደኞቼም በቋንቋቸው ሲያወሩ ‹ሞራ› የሚለውን ቃል ይጠቀሙ ነበር፡፡ የግቢ ትርጉሙ መሆኑ ነው፡፡
አጋጣሚዎችም አሉኝ ግቢን አስመልክቶ፡፡ ራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻህፍት በዚህ በክረምት ስሰራ ተጠቃሚዎች መታወቂያ አስይዘው መጽሐፍ ስለሚዋሱ መጽሐፉን ሲመልሱ ምን ዓይነት ቀለም ነው መታወቂያው ስላቸው ‹‹የግቢ ነው›› ይሉኛል፡፡ ተማሪዎቹ በየዩኒቨርሲቲው የሚማሩ የደብረብርሃን ልጆች በመሆናቸው የተለያዩ ዓይነት መታወቂያዎች በየዩኒቨርሲቲው አሉ፡፡ ስለዚህ በኔና ነሱ መሃል ግቢ የሚለው ቃል ሊያግባባ አይችልም፡፡
በሌላ አጋጣሚዬ የመኪና ረዳት የሆነ ልጅ ባለፈው ከአዲስ አበባ ስንመጣ አንዲቱን ተማሪ ተዋውቋት ወሬ ጀመሩ፡፡ ከወሬው የሰማሁት ‹‹የት ነሽ ግቢ?›› የሚለው ጥያቄው አሰቆኛል፡፡ ግቢ ለሱ ምኑ ነው፡፡ ምናባት ለሱ ግቢ ተብሎ መጠራት የሚችለው መናኸሪያው መሆን ነበረበት፡፡ ከዩኒቨርሲቲ ውጪ ላለው ግቢ ምኑ ነው? ተማሪዎች ‹‹ግቢ እንደዚህ አድርገን›› ሲሉ ሲሰማ ‹‹እኔም ከናንተው ቡድን ነኝ›› ለማለት የሚጠቀምበት ይሆናል፡፡ ስለ ትምህርት ቤታችሁ አውቃለሁ ማለቱ ይሆናል፡፡ እንደሷ ግቢን እንደሚያውቅ በማሳየት በመካከላቸው ያለውን ርቀት ለማጥበብ የተጠቀመበት ዘዴ ይመስለኛል፡፡
ዩኒቨርሲቲ የሚለውን መጥራት ካለመቻል?
ለኔ ከዋነኛ የግቢ ዝነኝነት ምንጮች ውስጥ አንዱ ይህ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲን አስተካክሎ መጥራት የሚችለው ሰው ከቀን ወደ ቀን እየቀነሰ መሄዱን ታዝቤያለሁ፡፡ ስለዚህ ግቢ ጥሩ መደበቂያ ነች፡፡ በር ላይ በጉልህ የተጻፈልንን ማንበብ ካልቻልን ለሌላ ዕውቀት ምን ዓይነት በር እንከፍታለን? ተመልካችነታችን የታለ?
ከዩኒቨርሲቲው ዉጪ ሆነው ስለ ዶርም፣ ካፌ፣ ክላስ፣ ላብ፣ ሳይሆን ባጠቃላይ ስለ ግቢ ነው የሚያወሩት፡፡ አፍ ላይ ደስ ይላል ልበል? አዎ፣ በእርግጥ ቅለትም አላት፡፡ ሁለት ፊደላት ናቸው፡፡

2017 ኦክቶበር 1, እሑድ

The African Storybook Initiative in Ethiopia

The initiative has been undergoing a phenomenal literacy work in the continent. Recently, Ethiopia has been selected as one of the countries to benefit from African Storybook’s (ASb) activities. The purpose of this blog is to assess what is going on.
Partnerships:
ASb partnered with governmental, non-governmental and private institutions to achieve the goals set in promoting early childhood literacy. As far as I know, due to these endeavors, mobile applications have been developed for Amharic and Afaan Oromo, students have been invited to assist in translation, writing and promoting, and story development workshops have been held. Such synergistic coalitions shall improve the quality and quantity of what is being done in Ethiopian languages.
Visits:
Lisa, Dorcas and Fatima visited Ethiopia and facilitated the activities held. The frequent visitor is Dorcas, who is from Kenya, a neighbor of Ethiopia. The explanations these visitors give, the friendly atmosphere they create during meetings and throughout their encounters with people here, has made ASb popular, at least among people who heard of it. I was also invited to a workshop in South Africa to learn about the new and updated website. This eye-opening visit made me appreciate the efforts everyone at ASb exerts! As young people, I and my friends should learn from the persistence of everyone at ASb.
Published:
Stories written by participants of workshops and story writing competitions in Ethiopia have been published on the website (africanstorybook.org). This hopefully encourages both the writers and others who take them as role models. There are many more writers, stories, ideas and concepts to use in the country. It is the amount of the trainings, reading and practice that should be focused up on to tap our potentials.  
Translations:
As stories should cross borders of various kinds, translation is of a paramount importance. Unquestionably, though, these translations should be thoroughly evaluated before they reach the children. Let me mention my own encounter. Last summer, I gave the librarian at Ras Abebe Aregay Library, Debre Birhan, my translation of ‘Greedy Kiundu’. I changed the names of people and places to local ones to familiarize the story with the children who read in the target language. When the librarian, a young girl of 21, was done with reading, she asked me if I mean the residents of the village I mentioned were as gluttonous as Mr. Kiundu. I explained the reason why I used the name of that place and she calmed down. Since books cannot answer all readers’ questions once they fly out of our hands, care should be taken. The collection of translated stories mainly in the three major Ethiopian languages is growing. This will have a huge impact on the children who read them.
Original Ethiopian Stories:
Ten Tigrigna stories are being processed for publication. In addition to this, their English translations are also available. This is a fruit of a workshop held at Adwa and supervised by the ASb delegation mentioned above. I hope stories from the other languages will also be made available in the future. I say this because stories are best appreciated in their original forms than in translation. Some stories written in English were also published. ‘Petros and his dog’ is one of them. This encourages the writers who have to grapple with the medium, a foreign language, and the content suitability of the stories. We may see these children among the writers of their country in the time to come. Guess what I say to them when I hand them copies of their stories! “You are just like Achebe or Ngugi – you are a published African writer!”
Accessibility:
I wish I wrote this in gold. As to me, it is an issue of urgency. Obviously, I am happy that the stories are published, translated and assessed by a number of volunteers, commissioned people and ASb staff. But the question that everyone of us should worry about is whether our ultimate objective is met. I know I shouldn’t give up just here because it may improve in the future. Should we wait until it improves or should we take proactive measures? Let me make this point clear. The stories for which everyone of us strived to get published are not reaching the target children! The children do not have mobile phones, tablets or computers. They cannot access these fancy apparatuses. The laptop and projector donated to our library, for example, are doing a great job. If many of them are distributed among schools, the scenario would change for the good. Can anyone afford to buy these? We may not. What about distributing hard copies? I think this is feasible. So, we should find a means like this to achieve our goal and reach the children. I tried to distribute CD copies of the stories to schools in Debre Birhan town by going there. On the other hand, my effort to get the stories printed at the Debre Birhan Uuniversity, with whom we signed an MOU, is still awaiting some officials’ willingness. I have some working plans which I may mention in my next blog.

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...