2020 ፌብሩዋሪ 23, እሑድ

የእሁዱ ግብር በደብረ ሆላንድ (The Sunday Banquet at Debre Holland)


የእሁዱ ግብር በደብረ ሆላንድ
(The Sunday Banquet at Debre Holland)
በመዘምር ግርማ (mezemirgirma@gmail.com)
14. 06.2012


ይህን ጽሑፍ ሳዘጋጅ በዕለቱ ያደረኩትን ምልከታ፣ የጠየኳቸውን ሰዎች አስተያየት እንዲሁም ethiopiapoultry.com የተባለውን የድርጅቱን ድረገጽ ተጠቅሜያለሁ፡፡

መንደርደሪያ
ከመጓዛችን በፊት ባሉት ቀናት የሆነውን በመጻፍ ልጀምር፡፡ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሜካኒካል ምሕንድስና መምህሩ ሕንዳዊው ዶክተር ጀሚር ከረጅም ጊዜ ቀጠሮ በኋላ የደብረ ሆላንድን ኃላፊ አርኖልድን ወደ ራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት አመጣው፡፡ አርኖልድም ቤተመጻሕፍቱን ጎበኘ፡፡ እሱ እየሰራ ስላለውም ስራ አስረዳኝ፡፡ የድርጅቱን ስኬት አስመልክቶ እሁድ ለሚደረገውም ግብር እንደተጋበዝኩ ነገረኝ፡፡ እኔም ስለምጎበኘው ነገር እንደምጽፍና በብሎጌ እንደምለቅ ነገርኩት፡፡ ‹‹ስንት ነው የምታስከፍለው››  በማለት ጠየቀኝ፡፡ እኔም እንደማላስከፍል ነገርኩት፡፡
ስለ ዶሮ እርባታው በዩኒቨርሲቲው ከሚገኙ ድርጅቱን ከሚያውቁ ሰዎች ጋር ተነጋገርኩ፡፡ በዚህም ውይይት የድርጅቱ አሰራር እስካሁን ከምናውቀው ለየት እንደሚል ተረዳሁ፡፡ ጫጩቶቹ ከሆላንድ እንደሚመጡ፣ በፋብሪካው ውስጥ ላለችው ለእያንዳንዷ ስራ አንድ የሆላንድ ድርጅት በቅርበት እንደሚያማክር፣ አንዲትን ዶሮ በሁለት ቀን ሦስት እንቁላል እንደሚያስጥሏት  ወዘተ ለማወቅ ቻልኩ፡፡
ዕለቱ ከመድረሱ በፊት ልሂድ አልሂድ በደንብ አልወሰንኩም ነበር፡፡ ዶክተር ጀሚር እሁድ ከሰዓት በኋላ ጦስኝ አምባ ሆቴል እንድጠብቀው ሲነግረኝ ለመሄድ ወሰንኩ፡፡ እኔ ብቻ ሳልሆን አብረውኝ የነበሩት ሁለት ጓደኞቼም ለመሄድ ስለተስማሙ ሄድን፡፡ ከዩኒቨርሲቲው የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች፣ መምህራንና ሰራተኞች በአራት መኪኖች ሄድን፡፡ እኔ የነበርኩባት የዶክተር ጀሚር መኪና ከሹፌሩ በተጨማሪ አንድ ሰው ብቻ የምትይዝ ኖራ ሁለታችን ተሳፈርንባት፡፡

መንገዱና አካሄዳችን
እንደሚታወቀው ደብረ ብርሃን ብዙ ኢንቬስትመንት እየጋበዘች ነው፡፡ የጅሩ መንገድ ግን አልተሻሻለም፡፡ እኛም እየሄድን ያለው በዚሁ መንገድ ነው፡፡ መንገዱ በቅርቡ የፍጥነት መቀነሻ በትራክተር እየተከመረ ተሰርቶለታል፡፡ በሱ ላይ እየነጠርን በጅሩ መንገድ የተወሰነ (ቢበዛ አንድ ኪሎሜትር) ከሄድን በኋላ ወደ ቀኝ ወደ ጎሼ ባዶ መንገድ ታጠፍን፡፡ የደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክን ወደ ግራ ትተን መሆኑ ነው፡፡ ጎሼ ባዶን በአድህኖ የገጠር ልማት ማህበር በኩል በአስተርጓሚነት ስራ ብዙ ጊዜ ጎብኝቻለታለሁ፡፡  በዚያ መንገድ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ሄደን ወደ ግራ ወደ ቢርቢርሳ ቀበሌ ታጠፍን፡፡ ይህ 1.1 ኪሎሜትር መንገድ በደብረ ሆላንድ ዶሮ እርባታ ኃ/የተ/የግ/ማ በ2.4 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ ነው፡፡
ቀኑ የተወሰኑ ነጫጭ ደመናዎች እዚህም እዚያም የተበታተኑበት የጠራ ሰማይ የሚታይበት፣ ከአቧራው በቀር አገር ፍቅርና የመዝናናት ስሜት የሚያመጣ ነገር ያለበት ነው፡፡ ከከተማ ጫጫታ እፎይ ያስባለን የገጠር ትዕይንት እውነት ለመናገር አስደሳች ነበር፡፡ ዶክተር ጀሚር የእንግሊዝኛ ዘፈን ከፍቶ እየኮመኮመ ትኩረቱን በመኪና መንዳቱ ላይ አድርጓል፡፡ ስለሃገራችን አየር ንብረት ስጠይቀው በአመዛኙ ጥሩ ሆኖ ትንሽ አለመስማማት እንዳለውና በተለይ ለቆዳው የፀሐይ መከላከያ እንደሚቀባ ነገረኝ፡፡ እኛ ጥቁሮች ያለን ሜላኒን እዚህ ለመኖር እንደተፈጠርን ምስክር ነው፡፡ ለነጮቹም ግን ረጅም የበረዶ ወቅት በሃገራችን አለመኖሩ የኛን አየር ተመራጭ እንደሚያደርገው አያጠራጥርም፡፡

የቢርቢርሳ ቆይታችን
በስፍራው ደረስን፡፡ የሰማይን ሁሉንም ጫፎች ምንም ነገር ሳይካልላችሁ የምታዩበት ነው፡፡ ደብረ ብርሃን ውስጥ በኃይለማርያም ማሞ ግቢ ብቻ ያየሁት ትዕይንት መሆኑ ነው፡፡ አድማሱን እያየሁ የህይወት ግቦቼን መከለሴ አልቀረም፡፡ አርኖልድ ከነባለቤቱና ቤተሰቡ ተቀበለን፡፡ ሴቶቹ በሙሉ የሐበሻ ቀሚስ ለብሰዋል፡፡ አውላላ ሜዳ ላይ የተገነባው ፋብሪካ ጅማሮ እንጂ መጨረሻ እንዳልሆነ እወቁ፡፡ የወደፊቱን የማስፋፊያ ፕሮጀክት ፎቶ ከታች ተመልከቱ፡፡
 ወደ ግብር አዳራሹም ገባን፡፡ በክብ በክብ ተጋባዥ እንግዶችና በአበሻ ቀሚስ ያሸበረቁት የፋብሪካው ሰራተኞች ተቀምጠዋል፡፡ በነገራችን ላይ ለበዓሉ ልዩ ድምቀት ለመስጠት ድርጅቱ ነው የሐበሻ ቀሚስ ስጦታውን ያቀረበላቸው፡፡ የከተማው የሐበሻ ቀሚስ ሳይሆን የገጠሩ ቢሆን እንዴት እንደሚያምር አትጠይቁኝ፡፡
ደብረ ሆላንድ የራሱ ሶላር ሲስተም ከ5 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ አሰርቷል፡፡ የከርሰ ምድር ውኃ 1.6 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ አስቆፍሯል፡፡ የሚሉና ሌሎችን መረጃዎች በመጥቀስ ‹‹ለሌሎች ኢንቬስትመንቶች ትምህርት የሚሰጥ ነው›› ብሎታል ባሶ ኮሚኒኬሽን በኖቬምበር 29፣ 2019 የፌስቡከ ዕትሙ፡፡  
የኔ ምልከታ ጠለቅ ያለ ትንታኔ እንዳይሆን የሚያደርገወው ነገር በዘርፉ ያለኝ ግንዛቤ ጠለቅ ያለ አለመሆኑ ነው፡፡ ለዚህም ነው ጽሑፌ በዓይን በሚታየውና በሚወራው ነገር ላይ ብቻ ማተኮሩ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ዕለቱ ለግብዣ የተያዘና የጉብኝት መርሃግብርም ያለመኖሩ እይታዬን ገድቦታል፡፡ በእርግጥ ለጋዜጠኞችና ለጸሐፊያን የተወሰነ ጉብኝት ተፈቅዶልን አድርገናል፡፡ ያስቀረነውንም በፎቶው ላይ ልታዩት ትችላላችሁ፡፡
ፋብሪካው ከከተማ ወጣ ያለበት ምክንያት የዶሮ እርባታ ንክኪ የማይፈልግ በመሆኑ ነው፡፡ ለአካባቢው የሚቆረቆር እንደሆነና ለእኛም ትምህርት እንደሚሰጥ ተገንዝቤያለሁ፡፡
ሰዎቹ ነቅለው ገብተዋል፡፡ ልጆቻቸውም የሚማሩት እዚሁ ነው፡፡ በርቀት በኢንተርኔት ይማራሉ፡፡ ለትንሹ ልጅ መምህርት ከሆላንድ ቀጥረውለት መጥታ እዚሁ እየኖረች ታስስምረዋለች፡፡ በዕለቱ ብዙ ፈረንጆች አይተናል፡፡

ዝግጅቱና የተሰጡ አስተያየቶች
እስኪ አሁን ደግሞ በቦታው ከተገኙት እንግዶች የቃረምነውን እነሆ፡-  
‹‹ተመሳሳይ ሥራ ለመሥራት ተነሳስቻለሁ፡፡ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡›› መምህር ሠውነት ተስፋዬ
‹‹የመጣሁት ከጓደኞቼ ጋር ነው፡፡ ጓደኞቼ እንሂድ ብለውኝ ነው፡፡ በሰዎች ግፊት መልካም ነገር ይመጣል፡፡ መግቢያ እንዳልጠየቅ ፈርቼ ነበር፡፡ ይህን ሁሉ አየን፡፡ ልምድ መቀመር አለብን ሁላችንም፡፡›› መምህር ሃብታሙ መኮነን

ዝግጅቱ አንድ አንድ እያለ እየተሟሟቀ፣ ተጋባዦቹም እየተሟሉ ሄዱ፡፡ የመግቢያ ንግግር በአርኖልድ ተደረገ፡፡
የኢቨንት ኦርጋናይዘርና ድግስ አቅራቢ ድርጅቶች የተጠበቡበት ዝግጅቱ የድምጽ ማጉያ ካለመኖሩ በቀር ምንም አይወጣለት፡፡  
‹‹ከብቶቻችንና እኛ ንጹህ ውሃ አግኝተናል፡፡ ችግራችንን ይረዱልናል፡፡ እየመጡ ይጠይቁናል፡፡›› አንድ የአካባቢው አርሶአደር ካቀረቡት ንግግር፡፡
የወረዳው አስተዳደር ‹‹ደብረ ሆላንድ ከወረዳው ኢንቬስትመንቶች አንዱና ውጤታማ የሆነ ነው፡፡ 80 000 ዶሮዎች አሏቸው፡፡ ጠንካራ ድርጅት ነው፡፡ የሚጎድሉም ነገሮች አሉ፡፡ እየተነጋገርን እናስተካክላቸዋለን፡፡ በመንግሥት በህግ የተፈቀዱ ድጋፎችን እናደርጋለን፡፡ የምሳ ፕሮግራም ተብሎ ግብዣው በመዘግየቱ መጀመሩን አበስራለሁ፤ እንዲጀመርም አሳስባለሁ፡፡›› የሚል አስተያየት ሰጥተው ተሳታፊውን ፈገግ አስብለውታል፡፡  
የድርጅቱ ተቀጣተሪ የነበረን ሰው ድርጅቱ ዋስ ሆኖ የእንቁላል አከፋፋይ አድርጓል፡፡ ይህ ለሌሎችም ሊለመድ የሚገባ ጥሩ አሰራር ነው፡፡ ደብረ ሆላንድ በደብረ ብርሃን ከተማ ቀበሌ 09 ለሚገኙ የጤና መድህን ለሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች 18000 ብር ከፍሎ መድናቸውን ሸፍኖላቸዋል፡፡ የቼክ ርክክቡም በዝግጅቱ ላይ ተካሂዷል፡፡
ደረጃውን የጠበቀ ግብር የጾም መያዣውን አስመልክተው አድርገዋል፡፡ በሁሉም ነገር ደስተኞች ነን፡፡ ለወደፊቱ ደግሞ የቡድን ፎቶ ቢኖር ለድርጅቱም ለፋይል ይሆነዋል ብዬ አስባለሁ፡፡ ሌላ ቀንም ጠርተው የፋብሪካውን አሰራር ያስጎበኙን ይሆናል፡፡ የእንቁላል ሽያጩ በጥሩ ሁኔታ እየሄደላቸው እንደሆነ ተገንዝቤያለሁ፡፡

ድረገጻቸውስ ምን ይላል?
የድርጅቱን ድረገጽ ለመቃኘት ባደረግነው ሙከራ የሚከተለውን ቃርመናል፡፡ በኢትዮጵያ ለ10 ዓመት ሰርተዋል፡፡
ድርጅቱ ሌሎችን የውጪ ድርጅቶች በቴክኖሎጂው በዶሮና ስሕይወታዊው ኢንዱስትሪ ለማገዝ መዘጋጀቱን ያሳየ፤ ድርጅቱ ከሥራ ፈጣሪዎችና ከኢንቬስተሮች ጋር አብሮ ለመስራትም እንደሚፈልግ የገለጸ ነው፡፡
ለአካባቢው ህብረተሰብ የስራ ዕድልና የስልጠና ዕድሎችን ፈጥሯል፡፡ ለህብረተሰቡ በሚሰጡት ሥልጠና ስለ ዶሮ በሽታ መከላከል፣ አመጋገብ፣ ስለሚጠጡት ውሃና የክትባት ህግ ያስገነዝባሉ፡፡
በኔዘርላንድና ኢትዮጵያ ልምድ ያለው ድርጅቱ በኢትዮጵያ ፍቃድ ስላለውና የህጉን ሁኔታ ስለሚያውቅ መምጣት የሚፈልጉትን እንደሚያግዝና አብሮም እንደሚሰራ ገልጧል፡፡ 
ደብረዘይት በቀን 90 000 እንቁላል የሚያመርተው በ60 ትጉህ ሰራተኞች ብቻ ነው፡፡ በሰዎችና በእንስሳት ላይ ኢንቬስት እያደረገ ያለው ድርጅቱ በደብረብርሃኑ ፋብሪካ የህብረተሰቡ የእንቁላልና የስጋ ፍጆታ እንዲሟላ ሌት ተቀን ይተጋል፡፡
በቀን 33 000 እንቁላል በቢርቢርሳ ይመረታል፡፡ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ጫጩቶች አሉ፡፡ የሥጋ ዶሮዎች ያቀርበል፡፡ ቴክኖሎጂው ዘመናዊ ነው፡፡
ከአካባቢ ጋር የተስማማ እርሻ፣ የኃይል መቆራረጥ እንዳያሳስበው ዘመናዊ የነፋስና የፀሐይ የኃይል ማመንጫዎች ያስገጠመ ነው፡፡   
ለዚህ ጽሑፍ ዝግጅት ድረገጻቸውን ሳይ በደችና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች ብቻ መሆኑን ታዝቤያለሁ፡፡ ወደ አማርኛ እንድተረጉመው ስራ አስኪያጁን አማክሬው ፈቅዶልኛል፡፡
የኛም ባለሐብቶች ከዚህ ተምረው ለሃገር የሚጠቅም ስራ እንዲሰሩ አሳስባለሁ፡፡

2020 ፌብሩዋሪ 21, ዓርብ

Freedom to Read 2020 in Ethiopia


Freedom to Read 2020 in Ethiopia
By Mezemir Girma
Founder and owner, Ras Abebe Aregay Library


Ras Abebe Aregay Library envisions creating a generation of readers in Ethiopia.  We engage with the community in Debre Birhan town, Amhara National Regional State through our library. Our involvement in making learning materials and knowledge accessible online to the wider Ethiopian community indicates that we serve much more Ethiopians. 
The lack of easy access to resources in mother tongue languages for Ethiopian students perpetuates the vicious circle of illiteracy and poverty. We would love to let you know that in Ethiopia there is a shortage of not only storybooks, but also textbooks.
Our library took part in an African Library and Information Associations and Institutions (AfLIA) meeting in Accra in October 2019. At that event we gave the participants explanation about the African Storybook Initiative. A representative of Uganda asked if that was like StoryWeaver.  That was our first time to learn about StoryWeaver. Afterwards we visited the website of StoryWeaver and followed them on social media. Then, on Twitter we learned about the Freedom to Read campaign. We applied to translate storybooks to Amharic. After the selection process, our library was in the list of the six organizations chosen globally to take part in the translation project.
As we are working on reading and literacy we understand how storybooks are helpful to children in our communities. When one gets the opportunity to translate quality picture storybooks into one’s mother tongue, one should not miss the opportunity. As we wish to help this generation get better opportunities than ours, we seized this opportunity and took StoryWeaver‘s online training via Skype.
Local digital storybooks in Amharic are helpful as there is a shortage of storybooks in the country. As a lecturer in English Literature at one of the public universities in Ethiopia, I (Mezemir Girma), was not aware of storybooks until 2014 when an American Peace Corps Volunteer, Benjamin Rearick introduced me to the African Storybook Initiative (ASb) and their wonderful translation system. If we, teacher educators, do not know about storybooks, who knows? By the way, I really felt happy when I found the storybooks I translated for ASb on the StoryWeaver website. Therefore, in a country where children have little access to storybooks, the role that the translation project may have in beyond words.
The translation process was a bit challenging. At first, our plan was to engage library readers and volunteers in the activity. However, they found it hard to get time to involve in the translation project. Therefore, the activity relied on the manager of the library, Mezemir Girma, alone. The translation was a bit difficult because I was not familiar with the website. It took me a while to get used to it. The online training helped me. The number of holidays that Ethiopia celebrated in the last few weeks kept me away from the university where I could get internet connection. As much as possible I used the time I had to translate.  After I went half way, I learned that I could use google translate. Earlier I didn’t rely on Google’s Amharic translation system as I heard people say it was inaccurate. Now I am using it even if their Amharic translation requires more editing work.
Once the translation is over, distribution is another challenge. As I know from experience, the community lacks access to the internet. At our library, we will display the storybooks to children using our projector and laptop. We will also download and disseminate to nearby schools. Other areas of the country could be reached with social media and regional education bureaus.
The logo of our library was designed by our IT volunteer Mr Tesfamicael Hailu and we would love to thank him as he filled that gap and helped our library appear at the back of the storybooks we translate. Thank you everyone at StoryWeaver for the opportunity you gave us!  
We wish everyone a joyful International Mother Language Day!
Friday, February 21, 2020
Debre Birhan, Ethiopia

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...