2015 ኖቬምበር 25, ረቡዕ

ሁቱትሲ፡ የወጣቷ ልብ አንጠልጣይ ትውስታዎች



ይህ ሁቱትሲ የተባለው መጽሐፌ ታትሞ ወጥቷል፡፡ ለማከፋፈል ወይንም ለመግዛት ከፈለጉ በ0913658839 ይደውሉ፡፡ መልካም ንባብ! ለውይይት በፌስቡክ ፔጃችን ሁቱትሲ፡ የወጣቷ ልብ አንጠልጣይ ትውስታዎች ይከተሉን፡፡


2015 ኖቬምበር 16, ሰኞ

ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ቡና የጋበዘቻቸው መንዜ ልጃገረድ


የአሁኑ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የዳሽን ቢራ ፋብሪካን ሊያስመርቁ ደብረብርሃን ከተማ ይገኛሉ፡፡ እንደሚመጡ ከሁለት ቀን በፊት በራዲዮ ፋና ሰምቼ ነበር፡፡ በሄሊኮፕተር መሆኑን ማን ጠርጥሮ! ግልገልና እናትየዋ ሜዳ ላይ ቆመዋል፡፡ በ2001 ዓ.ም. ሰሜን ሸዋን የጎበኙት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሲመጡ ወደ ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ ጠዋት ክፍለጊዜ ስለነበረኝ ስሄድ በትጥቅ አጀብ ሲሄዱ አይቻለሁ፡፡ እርሳቸው ይሆናሉ ብዬ ልጠረጥር አልችልም ነበር፡፡ በዚያ የሚያንገጫግጭ አስቸጋሪ ጎዳና፣ በተለይ ከጣርማበር በኋላ ባለው 130 ኪሎሜትር ኮረኮንቻማ መንገድ በመኪና ለምን ሄዱ እያልኩ አስባለሁ፡፡ የመሃል ሜዳ ሆስፒታልን ያስመረቁት ሚኒስትር እንኳን በሄሊኮፕተር ነበር የሄዱት፡፡ ታጋዮች በእግራቸው መሄዳቸውን አስበው ወይንም አገሩን ቀረብ ብለው ለመቃኘት ፈልገው ይሆናል፡፡ ለማንኛውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሃል ሜዳ ሲገቡ ህዝቡ አያውቅም ነበር፡፡ ጥበቃዎች ታዳሚዎቹን አብጠርጥረው ፈትሸው አስገቧቸው፡፡ ዛሬ ጠዋት ያገኘኋት ልጅ ቡና አፍዪ ነበረች፡፡ "እርሳቸው ምን እንደተናገሩ ትዝ አይለኝም፡፡ ጋቢ፣ ዝተትና መንዝ ጌራ የሚል ምንጣፍ ሰጧቸው፡፡ አንዲት ሆድዬ የተባሉ እናት ወደ እርሳቸው ለመጠጋት ሲሞክሩ ጠባቂዎቹ አናስጠጋም አሏቸው፡፡ መለስ ግን ይምጡ አሉ፡፡ ቤቴ በባንክ ተወርሶብኛል ብለው እግራቸው ላይ ወደቁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ይመለስልዎታል፤ ባይሆን እዳዎትን እከፍላለሁ አሏቸው፡፡ ሴትየዋም ትከሻቸውን ሳሙ፡፡ አሁን ሆድዬ በቀበሌያችን ዋና የመንግሥት ደጋፊ ሆነዋል፡፡ እርሳቸው የሌሉበት ስብሰባ አይደምቅም፡፡ አበባ ያበረከተችው ልጅ አንድ ዓመት ሙሉ ፊቷን ታመመች፡፡ የሰዉ ዓይን! የመሀል ሜዳው ሁለገብ አዳራሽ የመጀመሪያውን የአገር መሪ አስተናገደ፡፡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እንደመጡ ህዝቡ ለመኪናቸው ሳር በማቅረቡ 'እናንተ በጣም የዋሆች ስለሆናችሁና ፈረንጅ መጥቶ ሊጎዳችሁ ስለሚችል መንገድ አናሰራላችሁም' እንዳሏቸው አንድ አዛውንት አጫውተውኛል" ብላኛለች፡፡ መራዊ ከተማ ባህርዳር አቅራቢያ ግን የቀድሞው መሪ ሲያልፉ አስፋልት ላይ ተንበርክከው የለመኑ ቤታቸው የተወረሰባቸውን የደርግ ባለስልጣን መኪናው ገሸሽ ብሎ አልፏቸዋል አሉ፡፡ ጃንሆይ ሲመጡ ነጠላ ካነጠፋችሁ አቤቱታ ይቀበሉ ነበር አሉ፡፡ መንግሥቱ ኃይለማርያም ደብረብርሃን እንደመጡስ ታስታውሳላችሁ? ሌላ የመሪዎች ጉብኝት ትዝታ አላችሁ?

2015 ኦክቶበር 6, ማክሰኞ

የተርጓሚው መግቢያ

ወዳጆቼ፣
ይህን ለተረጎምኩት መጽሐፍ መግቢያ የጻፍኩትን ጽሑፍ አንብባችሁ  አስተያየት ብትሰጡኝ ደስ ይለኛል፤ ስለትብብራችሁ አስቀድሜ አመሰግናለሁ፡፡
ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ
ከስቲቭ ኤርዊን ጋር


ሁቱትሲ 
የወጣቷ ልብ አንጠልጣይ ትውስታዎች
ተርጓሚ
መዘምር ግርማ

በተለያዩ ዘመናት በብዙ ሀገራት የሰው ልጅ በዘውግ እየተቧደነ ሲጠቃቃ እንደኖረ ከታሪክ ድርሳናት እንረዳለን፡፡ ምሳሌ ለመጥቀስ ያክል 13 ሚሊዮን የአሜሪካ ቀደምት ሕዝቦች በአውሮፓውያን መጤዎች ተጨፍጭፈዋል፡፡ በቤልጅዬሙ ንጉሥ ሊኦፖልድ ዳግማዊ ትዕዛዝ 10 ሚሊዮን ኮንጓውያን በተወለዱበት ቀዬ ሲገደሉ፤ ናዚ ጀርመኖች በበኩላቸው በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ስድስት ሚሊዮን ይሁዲዎችን በዘመናዊ መንገድ በመግደያ ጣቢያዎች እያከማቹ በጅምላ ፈጅተዋቸዋል፡፡ በመሰረተ-ቢስ ጥላቻና በራስ-ወዳድነት መነሻነት ይህ ሁሉ ሕዝብ በግፍ ተገደለ እንጂ እነዚህን የተጨፈጨፉ ሰዎች የተጠቀሱት ሀገራት ከነጨፍጫፊዎቻቸው ለማኖር የተፈጥሮ ገጸ-በረከቱ ነበራቸው፡፡ በየሀገሩ የተፈጸሙትንና ታሪክ ሲያወሳቸው የሚኖሩትን ጎልተው የወጡ ፍጅቶች በተመለከተ ዶክተር ያዕቆብ ኃይለማርያም እንደጻፉት ቦስኒያ ውስጥ ሰርብ ያልሆኑት ዜጎች መጨፍጨፍ፣ አርመኖች በኦቶማኖች የደረሰባቸው እልቂት፣ ኩርዶች በሳዳም ሁሴን የተካሄደባቸው የዘር ምንጠራ፣ የካምቦዲያው ፖል ፖት ያካሄደው ገደብ የለሽ ጭፍጨፋ በዘር ጥላቻ ላይ ተመስርተው ከተፈጸሙ ግድያዎችና ሰቆቃዎች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ በመካለኛው አፍሪካ በምትገኘው በሩዋንዳ የተካሄደውና አንድ ሚሊዮን ገደማ የሚሆኑ ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈው የዘር ማጥፋት በንጹሐን ዜጎች ላይ ከተፈጸሙ የተደራጁና መጠነ-ሰፊ ዘግናኝ ድርጊቶች አንዱ ነው፡፡ የዚች ሀገር ሁቱ መሪ ከሀገሪቱ ያባረራቸውን ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ቱትሲ ስደተኞች ተመልሰው ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ በሕግ በመከልከልና ሀገር ውስጥ የነበሩትንም በማሰቃየት ቱትሲዎችን ከግፍ ጽዋ እንዲጎነጩ አስገድዷል፡፡ ከ1959 ጀምሮ ሁቱዎች ቱትሲዎችን በጠላትነት እንዲያዩ የሰበከው አገዛዙ ነው፡፡ ይህ ጸረ-ቱትሲ የጥላቻ ውትወታ በየወቅቱ ሁቱዎች ቱትሲዎችን የጥቃታቸው ሰለባ እንዲያደርጉ ገፋፍቷቸዋል፡፡ የሩዋንዳው ጭፍጨፋ ሕዝብ በሰፊው ያተሳተፈበትና ‹ቱትሲዎች መጤዎች ናቸው› በሚለው የቆየ ቅስቀሳ ምክንያትነት በጨፍጫፊዎቹ ዓይን የነባርና የመጤ ግጭት ጉዳይ ተደርጎ የሚታይ ነው፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ነገር ቢኖር ሁቱዎች ሥልጣንና ትምህርት እንዲያገኙ ቱትሲዎችን ማጥፋት እንዳለባቸው ተሰበኩ እንጂ በተፈጥሯቸው ገዳዮች ሆነው አይደለም፡፡ መንግሥት የጥላቻውን ስብከት እንዲያቆም፣ በቱትሲዎች ላይ ይፈጽም የነበረውን ግፍ እንዲተውም ሆነ ጭፍጨፋውን እንዳያካሂድ ለማድረግ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም ሆነ የተመድ ሳይቃጠል በቅጠል ብለው ጣልቃ አልገቡም፡፡ ይህም ለተጨፍጫፊዎቹ ጀርባቸውን መስጠታቸው እስከአሁን እንዳስተቻቸው ነው፡፡
የሩዋንዳውን ፍጅት ከፈፀሙት ወንጀለኞች መካከል 35 ዋነኛ ተዋናይ የነበሩት ሰዎች በተመድ ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ሲዳኙ ሁለት ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ በሀገር-በቀሎቹ የጋቻቻ ፍርድ ቤቶች ፍርድ አግኝተዋል፡፡ ሰውን እንደ እንስሳ በማደን ሲደሰቱ የነበሩና ከዘር ፍጅቱ ያመለጡ ሰዎች እንዴት ነው ወደፊት አብረው መኖር የሚቀጥሉት? የሚል ጥያቄ በሁላችንም አእምሮ መምጣቱ አይቀርም፡፡
በሩዋንዳ በቸልታ የታለፈው የዚህ የዘር ፍጅት መዘዝ የዛየርን መፈራረስ እንዳስከተለና እስካሁን መቋጫ ባላገኘው የኮንጎ ጦርነት እስከ ስድስት ሚሊዮን ሕዝብ ሊያልቅ እንደቻለ ምርምሮች ያሳያሉ፡፡ የሩዋንዳው ሕመም መገረን ወደ ኮንጎ ሊተላለፍ የቻለው ይህች ሀገር የዘር ፍጅቱን የፈጸሙትን ወንጀለኞች በማስጠጋቷ ከሩዋንዳ መንግሥት በደረሰባት ተጽዕኖ ነው፡፡ ወደ ቻድ፣ ማእከላዊት አፍሪካ ሪፐበሊክና ዳርፉርም የዘር-ፍጅቱ ግርሻ ተላልፏል፡፡ ዓለማችን አንድ መንደር ሆናለች እየተባለም የዘር ጭፍጨፋ በዓለም የተለያዩ ክፍሎች በመፈጸም ላይ ነው፤ ስጋቱም እስከአሁን ድረስ እንዳንዣበበ አለ፡፡
ዘውግ-ተኮር የሆኑ መቃቃሮችንና አለመግባባቶችን በኀይል ለመፍታት ሲሞከር የሚደርሰውን ጥፋት አስከፊነት ከሩዋንዳው ጭፍጨፋ በላይ የሚያሳይ የለም ብል ማጋነን አይሆንም፡፡ የዚች ሀገር ሕዝብ ሀገሩን ያወደመውን የዘር-ጭፍጨፋ ካስከተሉት ተግባራቱ መማሩንና ችግሩ እንዳይደገም መቁረጡን የሚያሳዩ ምልክቶች አሉ፡፡ በአዲሱ የሩዋንዳ ሕገ-መንግሥት መግቢያ ላይ ‹‹እኛ ሩዋንዳውያን፣ የዘር-ፍጅትንና ሁሉንም መገለጫዎቹን ለመዋጋትና ማናቸውንም ዓይነት የጎሣ፣ የክልልና ሌሎች ክፍፍሎችን ለማጥፋት ወስነናል›› የሚል በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቻቸውን ካጡ በኋላ የደረሱበት ውሳኔ ሰፍሯል፡፡ ከውድመቱ ቀድሞ ግን ይህ ቢገባቸው እንዴት ጥሩ ነበር! ከአንድነት ይልቅ ልዩነትን የማጉላትና የማራገብ ጠንቅ የገባቸው በቅርቡ ነው፡፡ የአዲሲቷ ሩዋንዳ ባለሥልጣናት እንደሚናገሩት ማንም ሰው ሁቱ ወይንም ቱትሲ ስለሆነ ብቻ የተለየ ጥቅም ወይም አገልግሎት ማግኘትም ሆነ ከሀገሪቱ መባረር የለበትም፡፡ ማናቸውም ሩዋንዳዊ ልጅም ሁቱ፣ ቱትሲ ወይንም ትዋ ነህ ተብሎ እንዲያድግ አይደረግም - ሩዋንዳዊ እንጂ፡፡ ለያይቶ ማየት ነውር ሆኗል፡፡
ይህ መጽሐፍ በ1994 በሩዋንዳ ከሁቱ ዘውግ የሚመደቡ ራሳቸውን ያደራጁ አካላት በተቀናጀ መልኩ በቱትሲዎችና አልፎ አልፎም ለዘብተኛ ሁቱዎች ላይ ባካሄዱት ፍጅት ወቅት ከግድያ የተረፈችው የቱትሲዋ የኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ትዝብትና ትውስታ ተተርኮበታል፡፡ ይህ የኢማኪዩሌ መጽሐፍ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ናዚ ጀርመኖች ይሁዲዎችን ሲጨፈጭፉ በተደበቀችበት ማስታወሻ ስትጽፍ ቆይታ መጨረሻ ላይ የናዚ ወታደሮች አግኝተዋት የተገደለችውን የአና ፍራንክን ማስታወሻ የሚያስታውሰን ነው፡፡ ‹ሩዋንዳዊቷ አና ፍራንክ› ብለው የሚጠሯም አሉ፡፡ ከጭፍጨፋው ከገዳዮቿ ጋር በግንባር ጭምር ከተገናኘች በኋላ በተአምር የተረፈችው ይህች ሰው የእምነት ጽናትና ይቅር-ባይነት ቋሚ አርዓያ ነች፡፡ በዳዮቿን በዝምታ ብዛት ሳትቀጣ ምህረት በማድረግ እፎይታን ለግሳቸዋች፡፡ መጽሐፏ ሦስት ክፍሎችንና 24 ምዕራፎችን የያዘ ሲሆን የመጀመሪያው ክፉ ቀን ዳር ዳር ሲል የሚለው ክፍል ከጭፍጨፋው በፊት የነበራትን ሕይወት ይዳስሳል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ የተደበኩባቸው ጊዜያት የሚል ሲሆን ከገዳዮች ተሸሽጋ የነበረችበትን ቆይታዋን ይተርካል፡፡ የመጨረሻውና አዲስ መንገድ የሚለው ክፍል ከጭፍጨፋው ማክተሚያ ቤተሰብ እስከመሰረተችበትና ተረጋግታ መኖር እስከጀመረችበት ጊዜ ያለውን ይይዛል፡፡ መጽሐፉ ስለ ሩዋንዳው ጭፍጨፋና ስለ ኢማኪዩሌ ታሪክ በሚገባ ከማስረዳቱ በተጨማሪ የአንባቢውን ስሜት በእጅጉ በሚስብ አቀራረብ ተጽፏል፡፡ ኢማኪዩሌ ይህን መጽሐፍ ስትጽፍ ለቋንቋው ውበትና ለቅንጅቱ ስምረት ሲባል የረዳት ካናዳዊ ጋዜጠኛና የልብ ወለድ ደራሲ ስቲቭ ኤርዊን ታሪኩን ያቀናበረው ልብ አንጠልጣይ አድርጎና በሚያስተምር መልኩ ነው፡፡ ምስል ከሳች የሆነ ገለጻና ለጽሑፉ ሕይወት የሰጠውን ምልልስ መጠቀሙም ጽሑፉን ማንበብ ከጀመሩ ሳይጨርሱ እንዳያቆሙት ያስገድዳል፡፡ ይህ የኢማኪዩሌ የመጀመሪያ መጽሐፍ እስካሁን ይህ የአማርኛው ትርጉሙ ሳይቆጠር ወደ 17 ቋንቋዎች ተተርጉሟል፤ ሽያጩም ከሁለት ሚሊዮን ቅጂ በላይ ነው፡፡ ኒው ዮርክ ታይምስ ከፍተኛ ሽያጭ ያገኘ በማለት ያወደሰው መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ ‹‹የሰውን ልጅ መንፈስ እጅግ ከፍተኛ እሴቶች የሚያረጋግጥ›› ተብሎ በመወደስ የክርስቶፈር ሽልማትን ለኢማዩሌ አስገኝቷታል፡፡ ታሪኩ በተንቀሳቃሽ ምስል ተቀርጾ በመገናኛ ብዙኃን ቀርቧል፡፡ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የክብር ዶክትሬት ዲግሪ የተበረከተላት ባለ ታሪኳም ስላለፈችበትና ዓለማችንም ወደፊት ስለሚያስፈልጋት ሰላማዊ ዓለም በየአህጉሩ እየተዘዋወረች ታስተምራለች፡፡
የኢማኪዩሌን መጽሐፍ ያገኘሁት በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ክፍል አነስተኛ የመጻሕፍት ስብስብ ውስጥ ነው፡፡ የመጻሕፍት ስብስቡን ያደራጁት አሜሪካዊቷ ካትሪን ይህን መጽሐፍ ገዝተው አሊያም ከወዳጆቻቸው በልገሳ አግኝተውት ሊሆን ይችላል፡፡ መጽሐፉን ማንበባቸውንም ሆነ ሥራዬ ብለው ስለዘር ጭፍጨፋ አውዳሚነት እንድናውቅ ፈልገው ማስቀመጣቸውን ባላውቅም ይህን መጽሐፍ የለገሱን ኢትዮጵያን እንደሚያፈቅሩ አዘውትረው ይነግሩኝ የነበሩት አፍሪካ-አሜሪካዊቷ ጡረተኛ ካትሪን ክራይተን ሼይ ታላቅ ሥራ ሰርተዋል የሚል እምነት አለኝ፡፡ ሌፍት ቱ ቴል (Left to Tell) የሚለውን የኢማኪዩሌን መጽሐፍ የተረጎምኩት ምን ልተርጉም ብዬ የሚተረጎም መጽሐፍ ሳፈላልግ አግኝቼው ሳይሆን ከላይ በተጠቀሰው ሁኔታ እጄ ገብቶ ካነበብኩት በኋላ ሥሜቴን በእጅጉ ስለነካውና የሚሰጠው የይቅርታና ከውድመት የማገገም ትምህርት ለሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ አስፈላጊ መሆኑን በማመኔና ለአማርኛ አንባቢያን ተርጉሞ ማቅረብ የዜግነት ግዴታዬ መሆኑ ስለገባኝ ነው፡፡ መሳጭና አስተማሪ ታሪኩ በዚች የበርካታ ዘውጎች መገኛ በሆነችው ሀገራችን አብሮነታችንን ተንከባክበን የማቆየትን ጸጋ ስለሚያስተምረንም ነው፡፡ መጽሐፉን ወደ አማርኛ ስተረጉም በታሪኩ ውስጥ የሚነሱትን ማናቸውንም ሃሳቦች እንዳይቀሩ በማሰብ ለይዘት ትኩረት በመስጠት ነው፡፡ ቋንቋውን ጉራማይሌ ላለማድረግም በተቻለኝ መጠን አማርኛ አማርኛ የሚሉ ቃላትን ለመጠቀም ሞክሬያለሁ፡፡
ኢማኪዩሌን እየተረዳኋት የመጣሁ ይመስለኛል፡፡ ያለፈችበትን እያንዳንዱን ሥቃይ መላልሼ ስላጤንኩትና ስላሰብኩበት አብሬያት የነበርኩ ያህል ይሰማኛል፤ ሰቀቀኗም በአእምሮዬ ይመጣብኛል፡፡ ሁላችንም እርሷ የታደለችው ይቅር ባይነትና መረጋጋት እንዲኖረን እመኛለሁ፡፡ ማናቸውም የሰው ልጅ በተፈጥሮ አስገዳጅነት በሚገባበት ዘውግ መነሻነት ብቻ አላስፈላጊ ሥጋት ውስጥ እንዳይገባ፣ በማናቸውም መንገድ ጉዳት እንዳይደርስበትና ከሌሎች ጋር በመፈቃቀርና በመተሳሰብ እንዲኖር እስኪ እንጣር፡፡
የ12ኛ ክፍል ተማሪ ሆኜ በአፍሪካ ህብረት አሳሳቢነት መላው አፍሪካውያን የኅሊና ጸሎት እንድናደርግ በተላለፈው መልዕክት ምክንያት የፍጅቱን ሰለባዎች እንድናስብ መደረጉን አስታውሳለሁ፡፡ ይህም የተደረገው የዚህ ዓይነቱ ከአብዛኞቻችን አእምሮ መጥፋት የማይችል አሰቃቂ ድርጊት በማንኛውም የዓለም ክፍል ባለ መጪ ትውልድ ላይ እንዳይታሰብም ሆነ እንዳይፈጸም ለማሳሰብ ይመስለኛል፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን እስካሁን ስለ ሩዋንዳው የዘር-ጭፍጨፋ በተለያዩ የመገናኛ አውታሮች፣ በመጻሕፍት፣ በተንቀሳቃሽ ምስል ትዕይንት (ለምሳሌ፣ ሆቴል ሩዋንዳ፣ ሹቲንግ ዶግስ፣ ሳምታይምስ ኢን ኤፕሪል) እና በሌሎችም መንገዶች ግንዛቤ አግኝተናል፡፡ የሀገራችን ሰላም አስከባሪ ሠራዊትም ሩዋንዳ ከጭፍጨፋው ታገግም ዘንድ ማገዙ የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው፡፡ ይህም መጽሐፍ ተጨማሪ ግብዓት ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ በሩዋንዳው ችግር ላይ በአማርኛ የተጻፉ ጽሑፎችን እጥረትም በመጠኑ በመፍታት ሌሎችም እንዲጻፉ ያነሳሳል የሚል እምነት አለኝ፡፡ ችግሩ በአንዲት ከጭፍጨፋው በተረፈች ግለሰብ ዓይን እንዴት እንደሚታይ እንታዘብበታለን፡፡ በነገራን ላይ ጨፍጫፊዎቹንና ራሳቸውን ቱትሲዎቹንም ጨምሮ ቱትሲዎች ከኢትዮጵያ የሄዱ ናቸው የሚሉ አካላት አሉ - ፡፡
አንድ ዘውግ ሌላውን በጠላትነት ፈርጆ ሲያጎሳቁል፣ ሲያገል፣ ሲያሳድድ፣ ሲያስር፣ ሲገድል፣ ብሎም እጅግ የከፋውን የዘር-ፍጅት ሲፈጽም ምን ዓይነት ውድመት እንደሚያስከትል ለመገንዘብ አያዳግትም፡፡ አንድ በመቻቻል ላይ የተጻፈ ጽሑፍ እንደሚያትተው ዘውግን መነሻ ያደረገ ጭፍን ጥላቻ፣ አግላይ ብሔራዊ ስሜት (የሌላን ሀገር ዜጎች እንዲጠሉ የሚያደርገው)፣ ወገናዊነትና ሃይማኖታዊ ጽንፈኝነት የሚያሳድጉት በዓለማችን የተወሰኑ ክፍሎች የነገሰው ተቻችሎ ያለመኖር አውሬ ሰዎችን በሰውነታቸው እንዳንቀበል፣ ይቅር ባይ እንዳንሆንና ሰላማዊ ግንኙነትም እንዳይሰፍን ያደርጋል፡፡ የዘር-ፍጅት እንዳይፈጸም በመከላከልና ሲፈጸምም በማስቆም ላይ የሚሰራው ተቋም የጄኖሳይድ ዎች ሊቀመንበር የሆኑት ግሪጎሪ ስታንተን ባቀረቡት ምርምር የሰው ልጆችን የደደረ ልብ የሚጠናወተው ይህ አውዳሚ አባዜ ስምንት ደረጃዎች እንዳሉት ይገልጻሉ፡፡ እነዚህም በተደራጀና ተቋማዊ በሆነ መንገድ የሚፈጸሙት ደረጃዎች የሚከተሉት ናቸው፡-
ሀ. መከፋፈል (Classification) - እኛና እነርሱ ብሎ በመከፋፈል ለየት ይላሉ ተብለው የሚታሰቡትን የኅብረተሰብ ክፍሎች በቀልድም ጭምር በማንቋሸሽ በሰዎች መካከል ያለውን ልዩነት አለማክበር
ለ. የሚታይ መገለጫ መስጠት (Symbolization) - ይህ የጥላቻ ግልጽ መገለጫ ሲሆን ይሁዲዎች በናዚ ጀርመን ቢጫ ኮከብ ያለበት ልብስ እንዲለብሱ እንደተደረገው ነው፡፡
ሐ. ከሰው ክብር ዝቅ ማድረግ (Dehumanization) - ይህ ተግባር ከራስ የተለዩትን ሰብዓዊ ክብርም ሆነ መብት በመንፈግ ይፈጸማል፡፡ በሩዋንዳ ሁቱዎች የቱትሲ ዘውግ ተወላጆችን ‹በረሮ› ይሏቸው እንደነበረው መሆኑ ነው፡፡ ይህ ሂደት ገዳዮቹ ‹እየገደልን ያለነው ሰው አይደለም፤ ታዲያ ድርጊታችን ምኑ ላይ ነው ጥፋትነቱ?› እንዲሉ መንገዱን ይጠርግላቸዋል፡፡
መ. ማደራጀት (Organization) - በጥላቻ ላይ የተመሠረቱ መንግሥታት አንድን ሕዝብ የሚያጠፋላቸውን ኀይል ያሰለጥናሉ፡፡
ሠ. በተቃራኒ ጎራዎች ማሰለፍ (Polarization) - ሕዝቡ በዘውጉ ከጨፍጫፊውና ከተጨፍጫፊው ወገን ሚናውን እንዲለይ ይደረጋል፡፡ በብዛት ይህ የሚሆነው በጥላቻ ቡድኖች ውትወታ በጋዜጣና በመገናኛ ብዙሃን የጥላቻውን መርዝ በመርጨት ነው፡፡ አንዱን ዘውግ ከሌላው ለይቶ በማውጣት ጠላት ነው ብሎ ማወጁ ጀርመኖች ይሁዲዎችን ከመፍጀታቸው በፊት በምዕራብ አፍሪካ በሄሬሮዎች ላይ የ20ኛውን ክፍለዘመን አሰቃቂ ጭፍጨፋ ሲፈጽሙ፣ ይሁዲዎችን ሲፈጁና የሩዋንዳ አክራሪ ሁቱዎች ቱትሲዎችን ሲጨርሱ የገዳዩን ዘውግ አባላት በቀላሉ ለማሳመንና ለህሊናው እንዲቀለው ለማድረግ ተጠቅመውበታል፡፡
ረ. ዝግጅት (Preparation) - ሰለባዎቹ በልዩነቶቻቸው ተለይተው ይፈረጃሉ፡፡ የጭፍጨፋው ንድፍ አውጭዎች ሰዎችን በመኖሪያ አድራሻቸውና በሌሎችም መለያዎች ይፈርጁና ለፍጅት ያዘጋጇቸዋል፡፡
ሰ. ፍጅት (Extermination) - በታቀደና ሆነ ተብሎ በተመቻቸ ዘመቻ የጥላቻ ቡድኖቹ ሰለባዎቻቸውን ይጨፈጭፋሉ፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በዘር-ፍጅት ማንነታቸውን መለየት እስኪከብድ ድረስ ተጨፍጭፈዋል፡፡
ሸ. ክህደት (Denial) - ግድያውን የፈጸሙት ወይንም ቀጣይ ትውልዶች ምንም ዓይነት ጥፋት እንዳልተፈጸመ በማስመሰል ክህደት ይፈጽማሉ፡፡
ከዚህ የጭፍጨፋ ሂደት የምንረዳው የዘር-ፍጅት በአንድ ሌሊት ያለምንም ዝግጅት የሚፈጸም አለመሆኑን ሲሆን ራሳችንን ከላይ ከተጠቀሱት በሌላው ላይ ጉዳት ከሚያደርሱ ክስተቶች ፈጽሞ ማራቅና የዕለት ከዕለት ድርጊቶቻችንን መገምገምም ያስፈልገናል፡፡ እነዚህን የዘር ፍጅት አመላካች ሂደቶች በማናቸውም ደረጃ በእንጭጩ መቅጨት ከተቻለ የዘር ፍጅትን ማስቀረት ይቻላል፡፡
በመጨረሻም ይህን መጽሐፍ አንዴ አንብበን ስንተወው ሳይሆን ደግመን ደጋግመን ስናነበው፣ ሃሳቡን ስናብላላውና ስንወያይበት ታላቅ ትምህርት እንቀስማለን ብዬ እገምታለሁ፡፡ እርስዎም ይህን አስከፊ ታሪክ አንብበው ሲጨርሱ ከአሁኑ በላቀ ሁኔታ ለሰው አዛኝ፣ ርህሩህና በጎ-አሳቢ እንደሚሆኑ አልጠራጠርም፡፡ እንደ ሩዋንዳው ችግር ባሉ ጠንቆች ላይ የራሳችንን ግንዛቤ ለማጎልበትና ሀገራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ የማኅበረሰባችንን ጤናማ መስተጋብር ለማጠናከር እንጠቀምበት ዘንድ የሚረዳንን ይህን መጽሐፍ እንዲያነቡት በአክብሮት እጋብዝዎታለሁ፡፡
መልካም ንባብ!
መዘምር ግርማ (mezemir@yahoo.com)
ደብረ ብርሃን
2008 ዓ.ም.

2015 ሴፕቴምበር 21, ሰኞ

Thesis Pains




Class work over
Proposal over
Research money comes
Thesis work starts
Hard work darts
Gripping my senses

This, that, those, I read
Time wasted
Unfocused
To the target
Not yet

Hurry
Library
Kennedy
Embassy
Graduate 
ILS
IES
Upstairs
Downstairs

Buy old books
Seek rare ones
Biherawi
Piazza
Mercato
Lagar
Book world
New ones
Book centre
Book Bazaar

In those last days of the month
I am happy because salary comes
Sad because the month is over
And deadline is nearer

Day and night
Read, write
Write, read,
Write, delete
My advisor
The worst dictator
The pace of time and my paper
Totally improper
“I have finished chapter three,”
Classmates say to me
Knowingly or unknowingly
This made me angry

For my nagging landlady
I tutored her child for free
In my busiest time she orders me
I had to do it to keep living there
And not waste my time looking for another 

Typing speed clumsy
Reading speed scary
But finally all is over
And I am back home again
But it will take me longer
To picture Addis without paper
And being kept busy
To forget the pot made coffee
To quote one DBU graffiti
“Without tension
No graduation”

By Mezemir Girma (mezemir.blogspot.com)
2011, Debre Birhan, Ethiopia

2015 ሴፕቴምበር 19, ቅዳሜ

INDIA EDUCATING ETHIOPIA: IN RETROSPECT AND PROSPECT




Coming soon! Comment on it please!
This is how my story begins:

Campfire Farewell
In July 2014, outside one of the condominium buildings in Tebase, Debre Birhan, Ethiopia, a group of local Debre Birhan University (DBU) lecturers and their friends gathered. People speak with beaming faces; live local dances and songs help make the party lively and memorable. For Chanamalikarjuna, Arjun in short, this is a second farewell. His colleagues, the staff of the Department of Electrical and Computer Engineering, DBU, threw a lavish party at a trendy hotel. Arjun showed all present at the condominium party the picture from his previous farewell. In that photo, the professors, technicians and other members of his department surrounded him.
The feeling among DBU staff and the town’s people who knew the tough teacher was that he had to stay and teach some more years. Even some contacted the officers who had to decide on his fate to facilitate a renewal. Truly, this man spent much of his earnings in Ethiopia treating local friends and buying from local businesses. Generosity is not the crux of the matter, though. Hard work, passion, punctuality, sympathy … there was much into this comfortable career. In fact, he himself was the one who bought the ram for the condominium campfire grill. University officials were unmovable. Arjun and many many Indian lecturers left that semester.    
Arjun told me that he would rather assume an Ethiopian citizenship and live on the 5400 Birr (less than three hundred USD then) salary compared to the 1500 to many thousands of USD salary Indians earn in Ethiopia. In an exclusive interview he gave me in June 2014 regarding the Ethiopian people, he said, “Whenever you call any Ethiopian teacher or any Ethiopian, first they ask how you are – the best thing I learnt from you guys. In India, you will not find such things. Whenever we call our friends or anyone, we just ask where they are or what they are doing. That is the worst thing in India. Here, the social life is very good. In India, you will not find such a social life. Everybody is busy with his work. He runs behind money.” These are some of the pull and push factors about his stay in the Ethiopian highlands! He was a regular visitor of the nightclubs and he is a man who enjoyed nightlife, a rare occurrence since the other Indians have never been seen with locals on such occasions. He threw party many a time. He covers the bill of everyone present and feels us with excitement. One night, he insisted going home early when we told him to stay a bit longer, he was unmovable. He confided in me that the community complained to the university officials about teachers who frequent clubs. “This would endanger my renewal,” he feared.

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...