2016 ሴፕቴምበር 30, ዓርብ

‹‹ልጅ ቢኖረኝ እዚያ ነበር የማስተምረው›› አያስብልም?



ባለፈው ያቀረብኩት የአስራ አራት ስራ ፈጣሪ መምህራን ተሞክሮ አነጋጋሪ የነበረ ይመስለኛል፡፡ በዚያ ተነሳስተው በሰዓቱ መንገዳቸውን የጀመሩ እንዳሉ ተገንዝቤያለሁ፡፡ ዛሬ የማቀርበው መምህር እዚህ ደብረ ብርሃን ላይ የእውነት ስራ ፈጣሪ ነው ስላችሁ ከሐቅ ነው፡፡ የሚሰራው ስራ እነሆ፡-
‹‹በየዕለቱ ተማሪዎች ከትምህርት ቤት እንደተመለሱ የቤት ስራቸውን ተከታትሎ እንዲሰሩ ማድረግ፣ በየዕለቱ የተማሩትን ሁሉንም ትምህርት ወደሚቀጥለው ቀን ሳይሸጋገር እንዲከልሱና እንዲያጠኑ ማድረግ›› ይላል ማስታወቂያው፡፡
ከአንደኛ እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል በአምስት ትምህርቶች ላይ የማጠናከሪያ ትምህርት የሚሰጥበት ይህ ተቋም ኤፈርት ዞን የቱቶሪያል ማዕከል ይባላል፡፡  ልጆች ከጥገኝነት መንፈስ እንዲላቀቁና በራሳቸው እንዲያጠኑ ያደርጋል፡፡ መምህራንም ተማሪዎቹ በተቸገሩባቸው ነጥቦች ላይ መጠነኛ እገዛ ያደርጉላቸዋል፡፡ አብዛኛውን ስራ በራሳቸው እንዲሰሩ የሚደረጉት ወደዚህ ማዕከል የሚመጡት ተማሪዎች በራስ የመተማመን ስሜታቸው እየጎለበተ ይሄዳል፡፡ ታዲያ ለዚህ ስራው 200 ብር ወርሃዊ ክፍያ አንድን ተማሪ ማስከፈል ይበዛበታል?
ታዲያ በአብዱ ጀባር ህንጻ (ደብረ ብርሃን ቀበሌ 03) የማጠናከሪያ ትምህርቱን የመስጠቱ ሃሳብ ከየት ፈለቀ አይሉኝም? አሁን በማዕከሉ የማስጠናቱን ስራ የተያያዙት መምህራን በፊት በፊት በየቤቱ ያስጠኑ ነበር፡፡ ሲያስጠኑ ግን ተማሪው የሚጠብቁትን ያህል መሻሻል ሳያመጣ ይቀራል፡፡ ምክንያቱን ሲመረምሩት ብዙ ጥረት የሚያደርጉት መምህራኑ ራሳቸው እንጂ ተማሪዎች ስላልሆኑና ተማሪዎች የመለማመጃ ዕድላቸው አናሳ በመሆኑ ነው፡፡ ለዚህም መፍትሔ ያሉት አሁን የጀመሩት ስራ ነው፡፡ በየትምህርት ዘርፉ ከየትምህርት ቤቱ የተውጣጡትና በስነ-ምግባራቸው የተመሰገኑት መምህራን ከመደበኛ የስራ ሰዓት በኋላ እየተገኙ ተማሪዎችን ያግዛሉ፡፡ ቅዳሜ የመለማመጃ ጥያቄዎችን ያሰራሉ፡፡ እንግሊዝኛን ኦዲዮ ቪዲዮ ጭምር በመጠቀም ሲያስተምሩ አይቻለሁ፡፡ በክረምትም የማጠናከሪያ ትምህርቱ አይቋረጥም፡፡
ነሐሴ 15፣ 2008 ዓ.ም. ማዕከሉ በድምቀት ሲመረቅ በነበረው የሥልጠናና የውይይት መርሃ-ግብር ላይ የተገኙት ወላጆች፣ ተማሪዎች፣ ምሁራንና ባለድርሻ አካላት የሰጧቸውን ሃሳቦች በመጠቃቀስና እርስዎም ጥያቄና አስተያየትዎን እንዲለግሱ በመጋበዝ እዚህ ጋ ልሰናበት፡፡
-       ወላጆች ላይ ስለ አሰራራችሁ የግንዛቤ ስራ መሰራት አለበት፡፡
-       ለልጆቻችን በቂ ድጋፍ፣ ቁጥጥርና ክትትል ማድረግ ለማንችል ሰዎች መልካም ዕድል ነው፡፡
-       ከትምህርት ቤት መልስ በየቤታችን የልጆቻችንን አእምሮን የሚያበላሹ ነገሮች ስላሉ ልጆቹ እዚህ መቆየታቸው መልካም ነው፡
-       ሞባይልና ኢንተርኔት ጤናቸውን ስለጎዳብንና ሱሰኛም ስላደረገብን ቁጥጥር እናድርግባቸው፤ ልጆቹ ላይ የአመለካከት ለውጥ ለማምጣትም አሰልጥኑልን፡፡ የጊዜ አጠቃቀምና የአጠናን ስልት ስልጠና የሚያስፈልገው ብዙ ልጅ አለ፡፡
-       የፊልም አማራጭ የበዛበትና ቴክኖሎጂን በተሳሳተ መንገድ በሚጠቀሙበት ሁኔታ ይህ ማዕከል ሁነኛ ስፍራ ነው፡፡
-       ከፊልምና ከቴክኖሎጂ ጋር የሚከፈተው ውጊያ አንዱ ግንባር ይህ ቤት ነው፡፡
-       በቀን ከአራት እስከ አምስት ሰዓት በላይ ለፈልም የሚቀመጥ ወላጅ ለልጁ ትምህርት ትኩረት ባይሰጥ አይገርመኝም፡፡ ልጃችን ግን ቢያጠና ምን ይሆናል?
-       ያልነበረ ነገር እንደዚህ ፈጥራችሁ ልጆቹ ላይ ለውጥ አምጡልን፡፡
-       በዚህ አጀማመር ያላሰባችሁት ነገር ሁሉ ሊሳካላችሁ ይችላል፡፡
-       ትምህርታዊ ውድድሮች፣ ፊልሞች፣ የጥያቄና መልስ ውድድሮች ይኖሯችኋል ብዬ አስባለሁ፡፡
-       ወላጆች የልጃችንን ልብሱን ብቻ አይደለም መቀየር ያለብን፤ አእምሮውንም ነው፡፡
-       የዚህ ማዕከል ውጤት የሚታየው ከብዙ ዘመን በኋላ ነው፡፡ እስከዚያ ግን ብዙ መጋር ያሻል፡፡
-       ልጆቻችንን አያባትልብንም ወይ?

2016 ሴፕቴምበር 29, ሐሙስ

የሰሜን ሸዋ ልጅ

‹‹አትንኩኝ ነው እንጂ ከልክ አትለፉ እስኪ ሠሜን ሸዋን ማን ይለዋል ክፉ››  ይለናል አርቲስት ትዛዙ በትሩ፡፡ እስኪ ይመልከቱትና ለወዳጅዎ ያጋሩት!

2016 ሴፕቴምበር 5, ሰኞ

ያነበቡትን ይተገብራሉ?

ስለንባብ ሳማክር የምጠይቃቸውን እነዚህን ጥያቄዎች እርስዎንም ልጠይቅዎትና በሚጽፉት ምላሽ መሠረት እኔም አባላትም አስተያየት እንስጥዎት፡፡
1. ሲያነቡ ግልፅ ግብ/ዓላማ ያስቀምጣሉ?
2. መጥፎ ያነባበብ ልማዶች አሉብዎ?
3. በንባብ ወቅት የአትኩሮትዎ ሁኔታስ?
4. የፀጥታ መከበር ያሳስብዎታል?
5. ንቁ አንባቢነትን ይግለፁ
6. ምን ዓይነት መጻሕፍት ያነባሉ?
7. ንባብዎ የዕውቀት፣ ክህሎት ወይም ያመለካከት ተብሎ ተከፋፍሏል?
8. ያነበቡትን ለማስታወስ ይቸገራሉ?
9. ከአፍ መፍቻዎ ውጪ በሆነ ቋንቋ ሲያነቡ ይቸገራሉ?
10. ያነበቡትን ይተገብራሉ?
ለተጨማሪ ሐሳብ 0970381070

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...