2018 ኦገስት 30, ሐሙስ

የሥኬት ፈር-ቀዳጁ የደብረ ብርሃን ቆዳ ፋብሪካ





የሥኬት ሥልጠና ቡድናችን አባላት አርፍደው ስለነበር ከቀኑ 11፡00 ሳይሞላና የፋብሪካው ዋና ዋና ዘመናዊ የሥራ ክፍሎች ሳይዘጉብኝ ብቻዬን ከራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት ወደ ጅሩ መስመር በእግሬ በጥድፊያ አቀናሁ፡፡ ከጅሩ መስመርም በጋሪ ተነስቼ ከአምስት ደቂቃ ገደማ በኋላ ፋብሪካው በር ላይ ደረስኩ፡፡ እዚያም በደረስኩ ጊዜ አቶ ኃይሉንና ሌሎችንም የማውቃቸውን ሰራተኞች አገኘሁ፡፡ ሰራተኞቹ የቤተመጻሕፍታችን አንባቢዎች በመሆናቸውና እንዲያውም የራሳቸው የመጻሕፍት ዕቁብ ጀምረው መጽሐፍ እየገዙ ያበረታቱንም ስለነበር ፈጽሞ ባይተዋርነት አልተሰማኝም፡፡  የተለያዩ የስራ ክፍሎችን ለሥራው ያላቸውን ፍቅር በሚያሳይ መልኩ አንድ በአንድ ያስጎበኙኝ ጀመር፡፡
የደብረ ብርሃን ቆዳ ፋብሪካ በጥቁር አባይ ጫማ አክስዮን ማህበር ስር ካሉት ሰባት የስራ ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ ከሃያ አንድ ዓመታት በፊት በአንድ ባለሐብት ተቋቁሞ በኋላ ላይ በልማት ባንክ በሃራጅ ለጥቁር አባይ ጫማ ፋብሪካ የተሸጠ ነው፡፡ የሥራ ክፍሎቹን በወፍ በረር እንቃኛቸው፡፡

1. ቢም ሃውስ
በተንጣለለው አዳራሽ ምዕራባዊ ክፍል የሚገኘው ይህ ሥፍራ መጋዘኑን ጭምር ያቀፈ ነው፡፡ መጋዘኑም አዲስ ቆዳ እንደመጣ የሚከማችበት ነው፡፡ ከመጋዘኑ ወደዚህ ሲል በአቅራቢያው ቆዳዎቹ የሚታጠቡባቸው ትልልቅ ገንዳዎች አሉ፡፡ ቆዳውን ከውኃ ጋር እያሽከረከሩ የሚያጥቡት ማሽኖች እንጂ ሰዎች እንዳልሆኑ ተረዱልኝ፡፡ ደም፣ ቁርጥራጭ ስጋ (በተለምዶ ደደብ የሚባለው) እና ጸጉርን የመሳሰሉት አላስፈላጊ ነገሮች ከቆዳዎቹ ላይ ይነሳላቸዋል፡፡
የቆዳን አያያዝ አስመልክቶ እርዱ በጥንቃቄ ቢሆን ይመከራል፡፡ ከቄራ የሚመጣው አስተራረዱም ሆነ አያያዙ ጥሩ ነው፡፡ የሚገፈፈው በንፋስ ነው፡፡ ቆዳ ከእርድ በኋላ መጋዘን ሳይቆይ ወደ ፋብሪካ ከገባ ለሥራ ቀና ይሆናል፡፡ የአገራችን የቆዳ ሁኔታ አሳሳቢ ነው፡፡ በህይወት ሳሉ የማይታጠቡና ቆዳቸው የሚበላሽ እንስሳት፤ እከክ የሚያጠቃቸው፤ ከግንድ ሲታከኩ ቆዳቸው የሚጎዳ ወዘተ አሉ፡፡ ይህም በፈብሪካውም ሆነ በአገራችን ሃብት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ስላለው ጥንቃቄው ከሁሉም ወገን ይጠበቃል፡፡ ይህን መልዕክት አበክረው የነገሩኝ የፋብሪካው ሰራተኞች የሚባክነው የሃገር ሃብት በየቀኑ ሲጣል ስለሚያዩ ምክራቸው በህብረተሰቡ ሊተገበር ይገባዋል፡፡
በትልቁ አዳራሽ በስተቀኝ ክፍል ተጨማሪ ትልልቅ በርሜሎች (ድራሞች) የሚያርፉባቸው ማቆሚያ ግንቦች እየተገነቡ አይተናል፡፡ እንዲያውም አንደኛው ግንበኛ ዓይኑ ውስጥ ሲሚንቶ ገብቶበት አውጥተንለታል፡፡ ሁሉም የሥራ ርብርቡ የሚያስቀና ነው፡፡ ‹‹በእውነቱ እኔስ ምን ያህል እየሰራሁ ነው?›› ብለን ራሳችንን እንድንጠይቅ ያደርገናል፡፡
2. ታኒንግ
በዚህ ክፍል እያንዳንዳቸው እስከ 2200 ወይም 6000 ስኩየር ጫማ ቆዳ የሚይዙ በርሜሎች (ድራሞች) አሉ፡፡ ከእንጨት የተሰሩና ምናልባትም በአልኮል መጠጥ ዝግጅት በየቴሌቭዥኑ ያየናቸውን የሚመሳስሉ ናቸው፡፡ ቆዳው በተለያዩ ኬሚካሎች የመታሸት ሂደት ውስጥ ያልፋል፡፡ ከበርሜል በርሜልም ይገላበጣል፡፡ ከነዚህም ሂደቶች አንዱ የሆነው ቆዳው ከ14 እስከ 18 ሰዓት ለሚሆን ጊዜ ክሮም በተባለ ኬሚካል የመልፋት ሂደት ውስጥ የሚያልፍበት ነው፡፡ ክሮም ምርጥ የቆዳ መስሪያ ኬሚካል ነው፡፡ ቆዳን ሰማያዊ ያደርጋል፡፡ ያሳምራል፡፡ በሱ የለፋው ቆዳ ሰማያዊ ሲሆን የስራን ብቃት ያሳያል፡፡ መጀመሪያ ላይ አካላዊ የነበረው የቆዳ ማልፋት ስራ ካለቀ በኋላና ቆዳው በክሮም ከታሸ ሙቀትና ባክቴሪያን ይቋቋማል፡፡ ቢወጠርም አይጎዳም፡፡ ቢቀጣጠል መኪና የመጎተት አቅም አለው፡፡ ያ እርጥብ ቆዳ ለዐሥር ዓመታት በዚያ ሁኔታ መቆየት ይችላል ሲሏችሁ የኬሚስትሪንና የሣይነስን ገጸበረከት ከማመስገን በላይ ምን ማድረግ ይቻላችኋል?
3. ሪታኒንግ
ቆዳው እንዳስፈላጊነቱ በተለያዩ ቀለማት ይቀልማል፡፡ ይህም የሚከናወነው በበርሜል ውስጥ ነው፡፡ ዘይቶችና ሲንታኖች የሚባሉ የሚያሳምሩ ቅባቶች ናቸው ለማልፋት የሚጠቅሙት፡፡ በዚህኛው የበርሜሎች ስብስብ አካባቢ ወጣት ሰራተኞች እየተዘዋወሩ የስራውን ሂደት ሲቆጣጠሩ አይተናል፡፡ ድራሙ ሲዞር እየሾለኩ የሚጡ ቆዳዎችን ማንሳትና ማስገባት፣ የማሽኑን ስራና የኤሌክትሪክ ሁኔታውን መቃኘት ያስፈልጋል፡፡ የሥራ ጋወን የለበሱ ሰራተኞች ይህን ይሰራሉ፡፡ በየደቂቃው ደግሞ በጋሪ ቆዳ የሚገፉ በቡድን የሚሰሩ ወጣቶችን ማየት የተለመደ ነው፡፡ ሁሉም ባተሌ፣ ሁሉም ንቁ፣ ሁሉም ትጉህ ሲሆን በዓይናችን በብረቱ አይተናል፡፡
4. የምርምር ድረም - በደንበኛ ስሩልን ተብሎ የሚመጣውን ናሙና ቆዳ ዓይነት በአነስተኛ መጠን ሞክሮ መስሪያ የምርምር ቦታ ነው ይህኛው፡፡ ያንን ቆዳ ሰርቶ በተባለው ዓይነት ለማምጣት ልምድና ጥንቃቄ የሚጠይቅ ሲሆን እስከ ዐሥር ጊዜ የሚሞክሩ ይኖራሉ፡፡ ሞክረው ሞክረው የሚፈለገው ዓይነት አንዴ ከመጣላቸው ግን ያንን የመዘገቡትን ሂደት ተከትሎ ወደ ምርት መግባትና በታዘዘው መጠን ማዘጋጀት ነው፡፡ የድራም ነገር አልቆ ልክ ከመጋዘኑ ፊትለፊት በዚህኛው የአዳራሹ ጥግ ሌላ ክፍል አለ፡፡ እንደሚከተለው ነው፡-

5.  ሰሌክሽን (መረጣ)
ቆዳዎች በያይነታቸው፤ ከደረጃ አንድ እስከ ሰባት (አፐር፣ ኤክስፖርት ሺፕ ላይኒንግ፣ ሺፕ ጋርመንት፣ ላርጅ፣ ስሞል፣ ኤክስትራ ላርጅ ወዘተ) እየተባሉ ረጅም ጠረጴዛ ላይ የሚመረጡበት ክፍል ነው፡፡ ሰባተኛው ደረጃ ተወጋጅ ቆዳ ነው፡፡ ሲወገድም የመግዣ ዋጋውን ጨምሮ ለዚህ ቆዳ የተለፋበትና የወጣበት ሁሉ ይታጣል ማለት ነው፡፡ በነገራችን ላይ በዚህ ፋብሪካ 65 በመቶ ገደማ የበግና ከ10 እስከ 25 መቶ የፍየል ቆዳ አገልግሎት ላይ ይውላል፡፡ የበሬ ቆዳ አይጠቀሙም፡፡ የበሬ ለመስራት የሚያስፈልጉ ማሽኖች ስለሌሉ አሁን እየተሰራ ካለው የፋብሪካው ማስፋፊያ ስራ በኋላ የሚካሄድ ይሆናል፡፡ ያኔ ጥቁር አባይ ከሌሎች ፈብሪካዎች የሚገዛው የበሬ ቆዳ በራሱ ፋብሪካ ይሸፈናል፡፡
ዘግይተው የመጡት ባልደረቦቼ ተካተው ጉብኝቱም ስራቸውን ጨርሰው በተቀላቀሉን በአቶ ኤርሚያስ ወሰኑ አስጎብኝነት ቀጠለ፡፡ የዚህን ፋብሪካ በር ስንረግጥ ስለ ቆዳ ምንም የማናውቅ የነበርነው አሁን ምስጢሩ እየተገለጠልን ነው፡፡ በመጀመሪያ ወደፋብሪካው በር ስንመጣ ያየነው የስራ ትጋትና ጥድፊያ ፋብሪካ በምን ዓይነት ሁኔታ እንደሚካሄድ ግንዛቤያችንን አሻሽሎልናል፡፡ አዲስ ዓለ፣ አዲስ ትዕይንት፣ አዲስ መገለጥ!
ጥያቄዎቻችንን በትጋትና በአድናቆት የሚቀበሉና የሚመልሱት ሰራተኞች በመልሳቸው አጥጋቢነት ያስደምሟችኋል፡፡ ፋብሪካው ኬሚካል 95 በመቶ የሚያስመጣው ከውጪ ነው፡፡ ከነዚህም ውስጥ ብዛት ያላቸው ኦርጋኒክ ኬሚካሎች ናቸው፡፡ ክሮሙን አስመልክቶ እንደተነገረን አደገኛው ዓይነት አይደለም፡፡
በፋብሪካው 119 ሰራተኞች ሲኖሩ፤ አብዛኞቹ ሴቶች ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ክፍል የራሱ ኃላፊ አለው፡፡ ፍሎር ኦፐሬተሮች፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ የቴክኒክ ማኔጀሮች፣ ፎርማኖች አሉ፡፡ ለፋብሪካው ስራ የተለያዩ አስፈላጊ ሙያዎች ሲኖሩ፤ በዋነኝነት ግን የኬሚስትሪና የኬሚካል ኢንጂነሪንግ ባለሙያዎች ናቸው ስራውን እያስኬዱ ያሉት፡፡ አዲስ አበባ ሊድ የሚባል ተቋም ስላለ መሰረታዊ የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን የጨረሱ ሰዎች እዚያ የቆዳን ስራ  ይሰለጥናሉ፡፡ በኬሚስትሪ ላይም ስለቆዳ ኮመን ኮርስ ይወስዳሉ፡፡ የውጪ አገር የትምህርት ዕድልም ሲያገኙ እንግሊዝ ድረስ የሚሄዱ አሉ፡፡ በዚህ ፈብሪካ የኛው አገር ልጆች ስራውን መስራታቸው ያስመሰግናል፡፡ ዩኒቨርሲቲም ስለተማሩ ላይገርም ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ እኛው አገር ላይ ይህንን ዓይነት የኛኑ ጥሬ ዕቃን መልክ የማስያዝ ስራ መሰራቱ በሌላም ዘርፍ መቀጠል ይኖርበታል፡፡ ለሃገር እድገትና እንቅስቃሴ መሰረታዊ ስራ እየተሰራ አይተናል፡፡
በፋብሪካው ትናንሽ መድማቶችና መቆረጦች  ካልሆኑ በስተቀር አደጋ አልተከሰተም፡፡  ሰራተኞቹ ካይዘን ሰልጥነዋል፡፡ ሙሉ በሙሉ ለመጀመርም እየተዘጋጁ ነው፡፡ ከአብዛኞቹ ፋብሪካዎች እንደሚሻሉና ሌላ ቦታዎች ላይ መረማመድ እንኳን እንደሚያስቸግር መመልከታቸውን ነግረውናል፡፡
በዚህ ፋብሪካ ብዙ ጥንቃቄ እንደሚያሻ ተምረናል፡፡ ‹‹ከሚመለከተው ሰራተኛ በስተቀር መንካት ክልክል ነው፡፡›› ‹‹ቅድሚያ ለደህንነትዎ›› የሚሉ የጥንቃቄ ማስታወቂያዎችን አክብሮ መንቀሳቀስ ግድ ይላል፡፡  ሙሉ የጤና ዋስትናና ዓመታዊ የጤና ምርመራ ለሰራተኞች እንደሚሰጥ ሰምተናል፡፡
በስራውም በኩል የደቂቃዎች ስህተት ብዙ ገንዘብ ያከስራል፡፡ ባክቴሪያ እንዳይበዛ መጠንቀቅ ያሻል፡፡ ኢዛይሞቹ ቆዳውን ሾርባ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡
የመብራት ጉዳይ
ባንዴ 120 ሊትር ድፍድፍ ነዳጅ ለእንፋሎት ማዘጋጃ ይጠቀማሉ፡፡ ይህን የሚሰሩት ማለዳ ገብተው ዝግጁ አድርገው ይጠብቃሉ፡፡ መብራት ሲጠፋ የተለፋበትና 120 ሊትር የባከነበት ሰራ እንዳልነበር ይሆናል፡፡ ጄኔሬተርም ይጠቀማሉ፡፡ 60 ሰራተኛ ከማሽን ጋር ስለሚገናኝ የደሞዝ ኪሳራም ይኖራል፡፡ በመብራት ምክንያት ብዙ ኪሳራ እንዳለ ለመገንዘብ ችለናል፡፡ ይህ ሃገር አቀፍ ችግረ አንገብጋቢ በሆኑ የስራ ቦታዎች ልዩ ትኩረት ቢሰጠው እንላለን፡፡ ለምሳሌ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መብራት አይጠፋም ለማለት የሚያስደፍር ነገር አለ፡፡

በፋብሪካው 2ኛው ክፍል
መጭመቂያ ማሽኖች የዚህ ክፍል ድምቀቶች ናቸው፡፡ ጣራውን ታኮ በተሰራ ማንጠልጠያ የሰንሰለት ጋሪ ላይ ተንጠልጥለው እንዲደርቁ ቤቱን ሲዞሩ የሚውሉ በሺዎች የሚቆጠሩ የሚመስሉ ቆዳዎች በመጀመሪያው ክፍል እንዳየናቸው ተሽከርካሪ በርሜሎች ሁሉ በስራ ላይ ያለውን ፋብሪካ ድምቀት ሰጥተውታል፡፡ አገሩ ደብረ ብርሃን ስለሆነ የመድረቂያ ጊዜያቸው ረጅም ነው፡፡ ሞጆ በግማሽ ቀን የሚደርቀው እዚህ ሦስት ቀንም ሊወስድበት ይችላል፡፡
ጊዜው ደርሶ የደረቀውን ቆዳ ስቴኪንግ ማሽኖች ያለሰልሱታል፡፡ ሌላ ደግሞ ሙቀትና ርጥበትን ጠብቆ የሚያሽ ማሽን አለ፡፡ የቆዳውን ውፍረት እየለካ የሚያለሰልሰው ማሽን ቀጣዩ ነው፡፡ ቆዳው እንዲያብረቀርቅ የሚያደርግ ማሽን አለ፡፡ ማቅለሚያ፣ መለኪያ ማሽን… ከ70 በላይ አውሮፓና ቻይና ሰራሽ ማሽኖች ብዙ ናቸው፡፡ ዘመናዊ ማሽኖች ብቻ ሳይሆኑ እነሱን ኦፐሬት የሚያደርጉትም ልጆች ዘመናዊነት ይታያችሁ! ከሁለት ሰራተኞች በቀር የደብረብርሃንና አካበቢው ተወላጆች ናቸው፡፡ ድርጅቱ በወጣቶች ስለሚተማመን የብዙ ክፍሎች ስራ አስኪያጆች ወጣቶች እንዲሆኑ አድርጓል፡፡
አፐር፣ ላይኒንግ፣ ጋርመንት፣ ግላቭ እየተባለ ቆዳው እንዳገልግሎቱና መጠኑ መለየት እየጀመረ ነው፡፡ ልስላሴውን ልነግራችሁ አልችልም፡፡ የፋብሪካውን አርማ እየመቱ ማሸግ የመጨረሻው ስራ መጀመሪያ ነው፡፡
ፋብሪካው የፍሻሽ ቆሻሻውን ችግር ለመፍታት ዘመናዊ ትሪትመንት እያሰራ ነው፡፡ በጥቂት ወራት የሚደርሰው ይህ ማጣሪያ እስካሁን ያለውን የሚተካ ሲሆን ሃያ ሚሊየን ብር ወጪ ተደርጎበታል፡፡
ይህ ፋብሪካ ቆዳን ለአገራችን፣ ለአፍሪካና ለዓለም ገበያ ማቅረብ እንጂ ልብሶችንና ጫማዎችን አይሰራም፡፡ አዲስ አበባ ያለው የጥቁር አባይ ፋብሪካ ነው ጫማ የሚሰራው፡፡ የአገራችን የፖሊስ፣ የመከላከያና ሌሎችም ድርጅቶች አባላት ጫማ ከፋብሪካው ያዛሉ፡፡ የምስራቅ አፍሪካ አገራትም እንዲሁ፡፡
ዓላማችን ፋብሪካ ውስጥ ያለውን የስራ ትጋት አይተን ለግላችን ስኬት ለመጠቀም ወይም ትምህርት ለመውሰድ ነበር፡፡ ብዙ እዚህ ጋ ያልጻፈኳቸውን ትምህርቶች አግኝተናል፡፡
አስፈላጊውን የጥራት ደረጃ ሳያሟሉ ቀርተው የሚወገዱ ቆዳዎችና ቁርጥራጮችም በእጅ በሚሰሩ አነስተኛ ካፒታል ባላቸው ሰዎች ይፈለጋሉ፡፡ በጣም አነስተኞቹም ለመቀመጫ መስሪያና ለችፑድ ይሆናሉ፡፡ በዚህ ረገድ ለመስራት ያሰቡ ጎብኝዎችን ፋብረካው እንደሚያበረታታ ተነግሮናል፡፡ የምሰራች በሉ!
ምስጋና
አስጎብኛችን ኤርሚያስ ወሰኑ ባለፈው ዓመት እንጦጦ ቤተመንግስትን ስንጎበኝ ‹‹ብራና አስነኩኝ›› ብሎ አስጎብኝውን ሲጠይቅ ነበር ለቆዳ ዘርፍ በሙሉ ልቡ የሚሰራ ወጣት መሆኑን ያወኩት፡፡ ፋብሪካውን እንድንጎበኝ በመፍቀድና ጉብኝቱንም በመምራት ላደረገልን ቀና ትብብር የቡድኑ አባላት ምስጋናችን የላቀ ነው፡፡ እሱን ብቻም ሳይሆን ሁሉንም የፋብሪካውን ሰራተኞች እናመሰግናለን ለማለት እንወዳለን፡፡
ከጽሑፉ በኋላ 1
በጽሑፌ ሰበብ በዚህ ጉብኝት ላይ በምናደርገው ውይይት ውስጥ የአካባቢ ብክለት ጉዳይ ሊነሳ ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ ፋብሪካው ሁኔታውን ለማሻሻል ብዙ ጥረቶችን እንዳደረገ ተረድተናል፡፡ የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ አለማግኘትና በፋብሪካው ዙሪያ የመኖሪያ ስፍራ እንዲሆን መፈቀዱ እንደችግሮች ተነስተዋል፡፡ ችግሮቹ በቅርቡ ተፈተው እንደምናይ ያለው ተስፋ ሰጪ ሁኔታ ያሳያል፡፡
ከጹሁፉ በኋላ 2
በራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሐፍት የሐሙስ የሥነጽሑፍ ምሽት የጉብኝቱን ነገርና የፋብሪካውን የስራ አካሄድ ተወያይተንበታል፡፡
እኔና ኤርሚያስ ወሰኑ የፋብሪካውን የቆዳ ቁርጥራጭ ቆሻሻ አወጋገድ ለማስተካከል እንዲረዳን ወደ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ አቅንተን ብዙ ተስፋ ሰጪ ነገሮችን አግኝተን ተመልሰናል፡፡ በዚህ ጥረትም ያ በማስወገጃ ቦታ አለመኖር ምክንያት ተከምሮ የሚሸተው ቆሻሻ መፍትሔ ካገኘ አስገራሚ ይሆናል፡፡ ውጤቱን አብረን እናየዋለን፡፡
ከጽሑፉ በኋላ 3
ታክመን የምንድንበትን፣ ተምረን የምንለወጥበትን፣ ብዙ መድህን የምናገኝበትን ዘመናዊ ነገር ሀሉ ከውጪ አገር እንደምናስመጣ ይታወቃል፡፡ ለዚህም ሞተሩ የውጪ ምንዛሬ ነው፡፡ ይህን ምንዛሬ የምናገኘው እጅግ ውሱን ከሆኑ ዘርፎች ሲሆን፤ የቆዳው ኢንዱስትሪ አንዱ ነው፡፡ ታዲያ ለምን 35 የቆዳ ፋብሪካዎች ሲዘጉ ዝም አልን? በተሻለ ሁኔታ እንዲሰቱ መንገዱን ማመቻቸት ከሁላችንም ይጠበቃል፡፡ ከጸሐፊዎችም ጭምር፡፡                                                     ይቀጥላል። Because you read this I give you this mobile card as an encouragement. If you are the first one, inform me. number: 55125341922384
በእንግሊዝኛም ይተረጎማል።
ሥራ አስኪያጁንም በቃለመጠይቅ እናቀርባለን።

2018 ኦገስት 28, ማክሰኞ

የኦሮምኛ ቋንቋ ገጠመኞቼ



አንደኛ፣ ቶኮፋ

አሁን አንድ መጽሐፍ እያነበብኩ ነው፡፡ መጽሐፉ <<Afan Oromo, A guide to speaking the language of the Oromo people in Ethiopia>> የሚል ሲሆን በአበበ ቡልቶ የተጻፈ ነው፡፡ የትግርኛ፣ የአማርኛና የኦሮምኛ መማሪያ መጻሕፍትን በጥሩ አቀራረብ ከቋንቋዎቹ ተናጋሪዎች ጋር እየሆነ የሚያጽፈው አሜሪካዊው ሠላም ጓድ አንድሩ ቴድሮስ ነው የመጽሐፍ ዝግጅቱ አስተባባሪና አርታኢ፡፡

ኦሮምኛን በእንግሊዝኛ እያብራራ የሚያስተምር መጽሐፍ እስካሁን ያገኘሁት በ1997 በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከባሌው ተወላጅ ጓደኛዬ ከኑሪ ነበር፡፡ ኑሪ ግን አንድ ቀን ከተጠቀምኳት በኋላ ወሰደብኝ፡፡ የሂንሰኔ መኩሪያን መዝገበ ቃለት ከዩኒቨርሲቲው ቡክ ሴንተር በ199 በ30 ብር ገዝቼ ስጠቀም ቆይቻለሁ፡፡ ይሁን እንጂ ከዚህ መዝገበ ቃላት የወሰድኩትን ቃል ስናገር የቋንቋው ተናጋሪዎች ግር ይላቸዋል፡፡ ሦስት ገጽ ውስጥ ያሉ ቃላትን ከመጽሐፉ ወስጄ ታሪኩ አነጋን ምን ያህል ታውቃቸዋለህ ብዬ ጠይቄው 47 በመቶ ብቻ ነበር ያወቀው፡፡ እንግዲህ ቀበሌኛ ምንምን ይሆናል ተጽዕኖው፡፡

የአሜሪካ ሠላም ጓዶች ማሰልጠኛው ሰነድ የአማርኛው በጣም ጥሩ ነው፡፡ የኦሮምኛውንም ፈልጌ ኮፒ ሰላደርገው ቀረሁ እንጂ ጥሩ  እንደሚሆን አይጠረጠርም፡፡ የማስተማሪያ መንገዳቸው ግሩም ነው፡፡ የሆነ ሆኖ ይህ አሁን እያነበብኩ ያለሁት መጽሐፍ ዋጋው 200 ብር ነው፡፡ ከቡክ ወርልድ ነው የገዛሁት፡፡ ይህንም መጽሐፍ በማግኘቴ እድለኛ ነኝ፡፡

ከዚህ መጽሐፍ ንባቤ ከገጽ 81 መጨረሻ አንዲት ቃል ባይ አንድ ነገር ትዝ አለኝ፡፡ ቃሏ ‹‹Anis = mee too›› ተብላ ቀርባለች፡፡ እና ምን ትዝ አለኝ መሰላችሁ፡፡ ሠላም ጋ ቡና የምታፈላው ልጅ ከመናገሻ ነበር የመጣችው፡፡ አማርኛ በመልመድ ላይ ስለነበረች፡፡ አንዲት ያልቻለቻት ነገር ነበረቻት፡፡ በምናብ አንድ ምልልስ ላቅርብ፡-

‹‹እንዴት ነሽ?››

‹‹ደህና ነኝ፡፡››

‹‹ይሄን የታደለ ገመቹን ዘፈን እወደዋለሁ፡፡ አንቺስ?››

‹‹እኔስ እወደዋለሁ፡፡››

ይህች ልጅ ገና ያልተማረች ቅጥያ ነበራት፡፡ ይህም የአማርኛው ‹-ም› ነው፡፡ እኔም፣ አንተም፣ አንቺም፣ እሷም ስንል የምንጠቀመውና ከአንድ ሌላ ሰው ጋር ተመሳሳይ ድርጊት ስናደርግ ወይም ተመሳሳይ ሁኔታ ላይ ስንሆን የምንጠቀመው፡፡ የኦሮምኛ አቻው ‹-ስ› ነው፡፡ አኒስ፣ አቲስ፣ ኢሳኒስ እያለ የሚሄደው ማለት ነው፡፡

ልጅቱ ታዲያ የኦሮምኛውን ቅጥያ ለአማርኛ መጠቀሟ ነው የዛሬ ወጌ መነሻ፡፡ ይህንም ኦሮምኛን ለመማር ለሚፈልጉ እንደመነሻ አቀረብኩ፡፡ ይቀጥላል፡፡  

2018 ኦገስት 24, ዓርብ

Meditating by Remembering Yesterday’s Events

As any programmed, disciplined and creative person does meditation is one of my morning routines. Now, at 4:21 AM, I am just done with warming up activities. Let me think about yesterday’s events. It was early in the morning that I woke, had a breathing activity, ate a light breakfast and headed to the university. At around 6:45 I started my plan for the day.
It has been a while since Benjamin Rearick recommended me to take part in a social entrepreneurs’ competition. I directly went into my inbox and reached out for the message and followed the link. After reading the instruction that requires competitors to have ideas that go in line with the 17 SDGs, I started the activity. Personal information, entrepreneurial background, interest areas and description of the innovation were some of the information sought.
After I tried to write the 1000 word article about the problem I am addressing, I went to the English department to print the essay and reread it. There I met Firehiwot, who was surrounded by summer-in-service students. As a secretary of the department, she was answering questions the students had. She asked me why I didn’t show up this summer. I told her the reason and she inquired if I am granted the sabbatical leave. I told her that the leave has not yet materialized due to some problems.
I grabbed a two-page print-out and left for the lounge. There I reread the essay and started my editing work. I also shared the idea with an experienced teacher and got constructive comments. Up until around 2:00 I pursued the endeavor and finished successfully. It was an inspiring feat of the day.
When I arrived home, I found that my brother cooked and had a late lunch. Then after, I went to Badmas Hotel, where I met a health practitioner and a nutritionist from the university and had a good stay with them for an hour and a half. Our talk was on how to conduct a health screening and a menu planning for my Effectiveness trainees. It was an inspiring lecture that the two guys gave me. I am deeply indebted to them.
At 4:00 PM I availed myself at the Ras Abebe Aregay Library and replaced Rut, the librarian who has replaced Genet who is on a leave. The English language students did not come on this day due to their own reasons. The occasional shower might be one factor. After 11:00 the Effectiveness trainees started to come. Seven people showed up. It is a good number. Some people who have not come will be compensating in the next few days. I am inspired by this closing session of the first week training. Monday was for the pain, Wednesday the problem and Friday the solution. Everyone’s face was glowing with satisfaction and hope. We will keep meeting every MWF 5:00 – 6:30. Last night’s was until after 7:00.
I went back to Badmas and met two of my colleagues from the Psychology and Amharic departments. We had a talk on various topics and it was 9:00 when I arrived at my home. I had a late dinner and an idea crossed my mind. I thought aloud, “I can call it a day! It is Friday! Why don’t I go to the club?” I acted on this idea and headed to Sheger House Cultural Club.
I had two bottles of beer, enjoyed the music, dancing and left the club. On my way home, I saw street children sleeping on a verandah. In this chilly town, at this summer season, there are such people. I talked to the bajaj driver who brought me home and learned that there could be around a hundred people sleeping outside in the town, churches, hotels, streets and new buildings being the places they frequent. After all these activities, I came back home and gave time to my addiction – social media. It was mid night when I went to bed. After four hours, I have just woke up. As you might know, effective people should wake up early. I know my sleep was shorter tonight. However, I find it adequate and have happily started the day. Writing and remembering this has just taken me an hour. Have a nice day!           
Photo: Street children in Debre Birhan

2018 ኦገስት 22, ረቡዕ

በራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት፣ ደብረ ብርሃን ስለተጀመረው ስልጠና



ከሥልጠናው በፊት አንድ ሃሳብ ልስጥዎት፡፡ ይኸውም እንደሚከተለው ነው፡፡ እቤትዎ ምግብ እያዘጋጁ የሚመገቡበት ሳምንታዊ የምግብ ሰንጠረዥ አለዎት? ወይንስ የለዎትም? እኛ በሥልጠናችን የምናደርገው የመጀመሪያው ነገር የምግብ ሰንጠረዥዎን አዘጋጅተው በአባላት እንዲተችልዎት ማድረግ ነው፡፡ በተቻለ መጠን የምግቡን ዓይነት ስብጥር ለማስተካከል ይሞክሩ፡፡ ቁርስ ከበድ ያለ ይሁን፡፡ ከምግብ በፊት ወይም በኋላ የሚበሉ ፍራፍሬዎችን ያካቱ፡፡ ይህ በፕሮግራም ምግብን የማዘጋጀት ነገር በህይወትዎ ሥነስርዓትን ለመልመድና የመርህ ሰው ለመሆን የመጀመሪያው እርምጃ ነው፡፡ ካሉን ቢያንስ አራት ስብዕናዎች የአንዱ፣ ማለትም የአካላዊ ማንነታችን፣ ግንባታ መሰረት ምግብ ስለሆነ የሱን ነገር መልክ ካስያዝን ሌላው ሰልፉን አሳምሮ ይከተላል፡፡
እን እኮ ሃብታም አይደለሁም!
 አይ እዚህ ቦታ ብዙም ስለማልቆይ!
 በፕሮግራም መታሰር አልሻም!
ሰበቡ፣ ሰበብ ሰበብ አለች! አንች ሰበበኛ፡፡
ሰበቡን ተወት አድርገው ይህን ዛሬ ይጀምሩትና የስኬት እርምጃዎን አንድ ይበሉ፡፡ የምግብ ሰንጠረዥዎን በኢንቦክስ ቢልኩልን ሃሳብ እንሰጥበታለን፡፡
ሌላው፡-
ዓመታዊ የጤና ምርመራ ማድረግ ሲሆን፤ በደብረ ብርሃን ከተማ ያን ያህል የሚያስተማምንና ከተላላፊ በሽታ የዘለለ ምርመራና ክትትል የለም ተብለናል፡፡ እስኪ የሕክምና ሰዎች አማክሩን፡፡
መልካም ቀን
መዘምር ግርማ
የእንግሊዝኛ ሥነ-ጽሑፍ መምህር
የራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍተ መስራችና
ሐሳብ አመንጪ
mezemir@yahoo.com

The Boy Wearing the Arenguage Fota


This year, 2017, has kindly given me the chance to look back into my life. That is why yesterday I wrote to you how I felt hungry one day when I was in grade eight.
It was in that same year that I took Gash Tesfaye’s fota (scarf). My stepfather, Gash Tesfaye, is the father of my half-brother. If you find it hard to make a mental picture of me then, I had a pair of blue locally made trousers. Tadese made them for me, I remember. Thank you uncle! I forgot the color of my jacket which was made by my father. I wore pink sandals. I was not carrying sticks though. Before I forget it, let me tell you why this story is entitled as such. Arenguade Fota means green scarf. This Amharic phrase makes more sense to me than the English one. My friends who heard this story also refer to it using this Amharic phrase.
At 14, I was in Debre Birhan town to register in the high school. While I was walking idly and visiting this town, I discovered that I felt hungry. It was, I think, the bread a woman was selling that reminded me of my hunger. They were small round bread that this woman was selling for just 25 cents. What a time!
“Mam, how much is the bread?” I asked. “Twenty five cents!” she responded. I sent my hands to my pocket and took out fifty cents. Do you think that I thought I could be satisfied with one? No! I ordered two. I stood by the woman and ate one of the bread. It was hard to finish that bread without at least tea. After I was done with one, I didn’t know what to do with the other one.
“I would appreciate it if you take this one loaf of bread and give me the money back,” I begged the woman. She stared at me and giggled, “Hahahahahaha!” “Where do you come from?” she asked me. I told her. “Do you think a town like Debre Birhan is like your country? No bread can be returned. Just get out of my sight!” she responded. “Please Mam. I didn’t think that one would satisfy me,” I begged her. “Put it in your pocket and you will eat it later when you feel hungry,” she advised me. After I assured myself that she was unmovable, I cursed her in my heart, put my bread in my pocket and left.

The Day I felt very hungry


For an Ethiopian this experience cannot be a strange one. Feeling hungry has been a normal condition here. Unless, you know, you have some means to amass some fortune in an 'innovative' way. Personally, the word ‘hungry’ is one of the first adjectives I learned hungrily at lower grades. Teacher would say,"I am hungry." The whole class will keep repeating this realistic sentence after him.
(A note to the reader: If you think my English sounds bad, you better quit reading this story here. I learned it without bread that it sounds lifeless.)
I am inspired to write this story by the discussants at our library yesterday. Part of the New Year celebrations at the library was a discussion on the two calendars we use side by side, the Gregorian and the Julian. As a result of this emerged, albeit slowly, the issue of we and they – the West and the East – at least concerning the churches.
Regarding food, my friend Kibru told us that in the countries he had visited in Europe access to food is not a big deal. One Euro can feed you much. One Dollar can satisfy you. “What about one Birr?” I thought. This brought my childhood experience to life. Nowadays, a decent meal costs you more than fifty Birr in the town I live in. Forget today! Let us consider yesterday’s. My yesterdays were the bad and long old days.
I think I was in grade eight when I felt very hungry and asked my father for a solution. It was night. At that night we had no food at home for some reason. The main reason was I didn’t have a mother nearby. My mother went far. Where? Please don’t ask me. I just don’t know how to explain this.
My father gave me one Birr and told me to go to one of the restaurants and eat. You could buy enjera with wot for just one Birr. It was in 1992 Ethiopian Calender or 2000 G.C. Sasit was then just a small village which had a few restaurants. These were places where people sold food in their houses. I visited one after the other. They had no food for the night. When I told my father this news, I saw that he was deeply moved. He knew and I also definitely knew that there is another restaurant – which we didn’t visit in our lives. The question of the century I always ask myself is why I didn’t want to go to that place.
“Mezemir, why don’t you go to your granny’s restaurant and buy,” Dadi permitted me. The only place in Sasit where there was food for sale at that night was my granny’s place. I wondered if I should go there. Underneath my belly a hyena is residing and asking for food, at least in my mother’s words. After a long while, I decided to visit my granny’s place and headed towards there.
Standing by the door, I called out to the people inside and enquired if there was any meal for sale. After some thought, my granny invited me to enter. She explained that she had no wot/stew to serve the enjera/bread with. I was asked if I go for enjera with yoghurt. I nodded. She gave me enjera with yoghurt and pepper. I ate, her children watching every move I made. I was surrounded by people who ate alone. One of them once invited me to receive a mouthful and denied me and swallowed that himself. He also used to hit, hate and insult me.
Here follows the greatest and unexpected experience of my life. Humanity descended from the dark sky to my village. I tried to hand the Birr over to my granny. She saw me in astonishment. She felt sorry for me. “Mezemir, you don’t have to pay at your granny’s house. Do you think I take money from my children? Come at any time and eat. My son!” she said. I think she also hit her chest in sadness. I wondered what to do with the money my father gave me.
This story is part of the reason why I still don’t eat with people. This story reminds me of not visiting my granny’s house when I felt hungry unless I have money at hand. The issue of grandmother to me is - just she is my ancestor. This could be part of the reason why I don’t visit my family who are three-hour drive away from the place I live in. It could be for this reason that I am lonely among an ocean of people.
This is why I laugh at the hospitality Ethiopians claim to have. This expalains the odd behaviours my friends notice in me. I just don't know how to say it!
What did your relationship with your granny look like?

2018 ኦገስት 14, ማክሰኞ

ከባንኩ ዘርፍ የምንማራቸው ሥርዓቶች



ዕለተ ሰኞ ነሐሴ 7፣ 2010 ዓ.ም ከሠዓት በኋላ በአዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ ተገኝቼ ነበር፡፡ በባንኩ በሥራአስኪያጅነት በሚሠራው በአዲሱ ዘለቀ መልካም ፈቃድ የባንኩን የተለያዩ ክፍሎች ለመጎብኘት ችያለሁ፡፡ ይህንንም ምልከታዬን አስመልክቼ ከባንኩ ዘርፍ ልንማር እንችላቸዋለን ስለምላቸው ትምህርቶች አንዳንድ ነገር ልጽፍ ወደድኩ፡፡ መልካም ንባብ፡፡

ሠዓት አክባሪነት
በባንኩ እንደሌሎች ባንኮች ሁሉ ሥራ የሚጀምረው በሠዓቱ ነው፡፡ ጠዋት 2፡00 ሠዓት ላይ መስኮቶች ሁሉ ለአገልግሎት ክፍት ናቸው፡፡ ማታም 12፡00 ላይ ሠራተኞች ሁሉ ሥራቸውን ጨራርሰው ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡ ቀድሞ መውጣት የማይታሰብ ነው፡፡

ንጽህና
የባንኩ ወለል፣ ግድግዳ፣ ጠረጴዛዎች፣ ዕቃዎች ሁሉ ንጹህ ናቸው፡፡ ይህም በአገልጋዮቹና በተገልጋዮቹ በአእምሮ ላይ የሚኖረውን አዎንታዊና አስደሳች ስሜት መገመት ይቻላል፡፡

አለባበስ
አለባበሳቸው ከአንድ ባለሙያ የሚጠበቅና ፕሮፌሽናል ነው፡፡ ቡራቡሬ ነገር የለም፡፡ ከጥበቃ እስከ ሥራአስኪያጅ ድረስ ሽክ ማለታቸው ትልቅ ነገር ነው፡፡ ቆንጆዎች!

የደንበኞች መስተንግዶ
ደንበኞችን ጠብ እርግፍ ብለው የሚያስተናግዱት ሰራተኞች አቀራረባቸው ያስደስታችኋል፡፡ ቤተሰብነት ይሰማችኋል፡፡ ደንበኛን ዛሬ በጥሩ ሁኔታ ማስተናገድ ለባንኩ አጠቃላይ ስኬት ያለው ጥቅም አያጠያይቅም፡፡ በመስሪያ ቤቶች የምንለመከተው የነበረው ተለምዷዊ ቢሮክራሲ እየተወገደ ነው፡፡ ስልክ ደውለው ስለ አካውንታችሁም ሆነ አዲስ ስለመጡ አሰራሮች ያስታውሷችኋል፡፡

የሥራ አፈጻጸም
የሥራ አፈጻጸማቸውን አስመልክቶ ስንነጋገር ማታ ስራቸውን ሲጨርሱ ሁሉም የዕለቱን ሒሳብ ዘግተውና ሥራአስኪያጁም ያንን አጽድቆ ይወጣል፡፡ በሌሎች ቅርንጫፎችም ያሉት እንደዚያው ያደርጋሉ፡፡ አጠቃላይ የባንኩን ቅርንጫፎች አፈጻጸም የሚያየው ዋናው ማዘዣም ይህንን ይከታተላል፡፡ አንዲት ግድፈት ካለች የተዘረጋው ስርዓት እንዳይሄድ ችግር ያስከትላል፡፡ በማግስቱ በሚኖረው ስራ ላይ ጫና ይኖረዋል፡፡ ስራቸውን ሳያሳድሩ ይሰራሉ፡፡

መደራጀት
ኢትዮጵያውያን እንዲህ ተሰባስበው ዘመናዊ አሰራር ማካሄዳቸው ትልቅ ትምህርት ነው፡፡ ለሌላው ዘርፍም አንድ ትምህርት የሚሰጥ ተሞክሮ ነው፡፡ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርና በደምሳሳው በሁሉም ዘርፎች ዘመናዊ አሰራርን ለመዘርጋት የሚያስችል ትምህርት ይሰጠናል ባይ ነኝ፡፡


ዘመናዊነት
በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የታገዘው፣ ዘመናዊ የአሰራርና የአመራር ሥርዓትን የተከተለውና ስሙም እንደሚያመለክተው ዓለም አቀፍ የሆነው ባንክ ለዕለት ከዕለት ኑሯችን ብዙ ትምህርት ልንወስድበት የምንችለው ነው፡፡

መረጃዎች
ከባንኩ ዓመታዊ መጽሔት እንዳገኘሁት በአገሪቱ
18 ባንኮች አሉ፡፡
16ቱ የግል ሲሆኑ 2ቱ የመንግሥት ናቸው፡፡
በ2017 ሦስተኛዋ ሩብ ዓመት 198 የባንክ ቅርንፎች በሃገሪቱ ተከፍተዋል፡፡
በመሆኑም የባንክ ቅርንጫፎች ቁጥር 3807 ደርሷል፡፡
አንድ ቅርንጫፍ ለ25000 ሰው ገደማ ያገለግላል፡፡
34 በመቶ ቅርንጫፎች በአዲስ አበባ ይገኛሉ፡፡
አጠቃላይ 49.2 ቢሊየን ብር ባንኮች ያንቀሳቅሳሉ፡፡
የግል ባንኮች 47.6 በመቶ ድርሻ አላቸው፡፡

ማጠቃለያ
ከውጭ እንዳመጣናቸው እንደ ባንክ፣ አየር መንገድ፣ ትልልቅ ሆቴሎች ዓይነት ዘመናዊነትን እንደሚከተሉ ተቋማት ሁሉ በየዘርፉ አሰራራችንን ብናዘምን የምንፈልገውን ብልጽግና ማምጣት እንችላለን፡፡ ለመሆኑ ከዚህ የባንኮች ተግባር እርስዎ ምን ተማሩ? ምንስ መተግበር ይቻልዎታል?



በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...