2015 ኖቬምበር 25, ረቡዕ

ሁቱትሲ፡ የወጣቷ ልብ አንጠልጣይ ትውስታዎች



ይህ ሁቱትሲ የተባለው መጽሐፌ ታትሞ ወጥቷል፡፡ ለማከፋፈል ወይንም ለመግዛት ከፈለጉ በ0913658839 ይደውሉ፡፡ መልካም ንባብ! ለውይይት በፌስቡክ ፔጃችን ሁቱትሲ፡ የወጣቷ ልብ አንጠልጣይ ትውስታዎች ይከተሉን፡፡


2015 ኖቬምበር 16, ሰኞ

ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ቡና የጋበዘቻቸው መንዜ ልጃገረድ


የአሁኑ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የዳሽን ቢራ ፋብሪካን ሊያስመርቁ ደብረብርሃን ከተማ ይገኛሉ፡፡ እንደሚመጡ ከሁለት ቀን በፊት በራዲዮ ፋና ሰምቼ ነበር፡፡ በሄሊኮፕተር መሆኑን ማን ጠርጥሮ! ግልገልና እናትየዋ ሜዳ ላይ ቆመዋል፡፡ በ2001 ዓ.ም. ሰሜን ሸዋን የጎበኙት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሲመጡ ወደ ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ ጠዋት ክፍለጊዜ ስለነበረኝ ስሄድ በትጥቅ አጀብ ሲሄዱ አይቻለሁ፡፡ እርሳቸው ይሆናሉ ብዬ ልጠረጥር አልችልም ነበር፡፡ በዚያ የሚያንገጫግጭ አስቸጋሪ ጎዳና፣ በተለይ ከጣርማበር በኋላ ባለው 130 ኪሎሜትር ኮረኮንቻማ መንገድ በመኪና ለምን ሄዱ እያልኩ አስባለሁ፡፡ የመሃል ሜዳ ሆስፒታልን ያስመረቁት ሚኒስትር እንኳን በሄሊኮፕተር ነበር የሄዱት፡፡ ታጋዮች በእግራቸው መሄዳቸውን አስበው ወይንም አገሩን ቀረብ ብለው ለመቃኘት ፈልገው ይሆናል፡፡ ለማንኛውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሃል ሜዳ ሲገቡ ህዝቡ አያውቅም ነበር፡፡ ጥበቃዎች ታዳሚዎቹን አብጠርጥረው ፈትሸው አስገቧቸው፡፡ ዛሬ ጠዋት ያገኘኋት ልጅ ቡና አፍዪ ነበረች፡፡ "እርሳቸው ምን እንደተናገሩ ትዝ አይለኝም፡፡ ጋቢ፣ ዝተትና መንዝ ጌራ የሚል ምንጣፍ ሰጧቸው፡፡ አንዲት ሆድዬ የተባሉ እናት ወደ እርሳቸው ለመጠጋት ሲሞክሩ ጠባቂዎቹ አናስጠጋም አሏቸው፡፡ መለስ ግን ይምጡ አሉ፡፡ ቤቴ በባንክ ተወርሶብኛል ብለው እግራቸው ላይ ወደቁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ይመለስልዎታል፤ ባይሆን እዳዎትን እከፍላለሁ አሏቸው፡፡ ሴትየዋም ትከሻቸውን ሳሙ፡፡ አሁን ሆድዬ በቀበሌያችን ዋና የመንግሥት ደጋፊ ሆነዋል፡፡ እርሳቸው የሌሉበት ስብሰባ አይደምቅም፡፡ አበባ ያበረከተችው ልጅ አንድ ዓመት ሙሉ ፊቷን ታመመች፡፡ የሰዉ ዓይን! የመሀል ሜዳው ሁለገብ አዳራሽ የመጀመሪያውን የአገር መሪ አስተናገደ፡፡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እንደመጡ ህዝቡ ለመኪናቸው ሳር በማቅረቡ 'እናንተ በጣም የዋሆች ስለሆናችሁና ፈረንጅ መጥቶ ሊጎዳችሁ ስለሚችል መንገድ አናሰራላችሁም' እንዳሏቸው አንድ አዛውንት አጫውተውኛል" ብላኛለች፡፡ መራዊ ከተማ ባህርዳር አቅራቢያ ግን የቀድሞው መሪ ሲያልፉ አስፋልት ላይ ተንበርክከው የለመኑ ቤታቸው የተወረሰባቸውን የደርግ ባለስልጣን መኪናው ገሸሽ ብሎ አልፏቸዋል አሉ፡፡ ጃንሆይ ሲመጡ ነጠላ ካነጠፋችሁ አቤቱታ ይቀበሉ ነበር አሉ፡፡ መንግሥቱ ኃይለማርያም ደብረብርሃን እንደመጡስ ታስታውሳላችሁ? ሌላ የመሪዎች ጉብኝት ትዝታ አላችሁ?

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...