2023 ፌብሩዋሪ 2, ሐሙስ

ለብዙዎቻችን የባከኑብን ዕድሎች

"I knew it was bad behavior. I knew it was wrong. My mates knew too. We talked about it often, while stoned, how stupid we were to be wasting an Eton education." 

Spare, Prince Harry, The Duke of Sussex, page 83.

"መጥፎ ባህሪ እንደነበረ አውቅ ነበር። ስህተት እንደነበረ አውቅ ነበር። ደባሎቼም ያውቁ ነበር።  በኤቶን ትምህርት ቤት ለመማር ያገኘነውን ዕድል በማባከናችን ምን ያህል ደንቆሮዎች እንደነበርን አደንዛዥ ዕፅ እያጨስን በምንደነዝዝባቸው በአብዛኞቹ ጊዜያት እናወራ ነበር።"

ስፔር (ቅያሪ)፣ ልዑል ሃሪ፣ የሰሴክሱ ዲዩክ፣ ገጽ 83 


ይህችን ገጽ አንብቦ ብቻ ማለፍ ይከብዳል። ብዙዎች ያላገኙትን የመማር ዕድል ያገኘን ስንቶቻችን እንደ ልዑሉና ጓደኞቹ ሁሉ አባከንነው! እነሱ ያባከኑት ዕፅ እያጨሱ ነው። ከሱሰኝነት ጉዳይ ዉጪ እንነጋገር። የመማር ዕድሉን ተጠቅመን የወጣብንን ያህል ወይም ከዚያ በላይ ማበርከት እንዴት ተሳነን? ለትምህርት ዓላማ የወጣው ገንዘብ፣ ጊዜ፣ ጉልበት ወዘተ ሲታሰብ ትርፉ የዚያን ያህል አይመስልም። በእርግጥ የትምህርት ሥርዓቱ በጥራት የማስተማርና የመከታተል ችግር ይኖርበታል። ከትምህርት ዉጪ ያሉ የኑሮ ጫናዎችም ይኖራሉ። ቤተሰብና አካባቢም ሚናቸው አይካድም። የሆነው ሆኖ ግን የኃይለማርያም ማሞ፣ የምኒልክ፣ የጥቁር አንበሳ፣ የአብዮት ቅርስ ወዘተ የትምህርት ዕድልና ልፋት ፍሬውና ምርቱ በጣም ብዙ መሆን ሲገባው የሆነ አይመስልም። የኔልሰን ማንዴላ የፎርት ሄር ትምህርት ብዙ እንዳፈራው አልሆነልንም። ከዚያም በመለስ አልሆነም። ይህን በወቅቱ እናውቀው ነበር? ካወቅነው ምን እርምጃ ወሰድን? ይህን ጉዳት እንደ አገር አስበነዋል? ወይስ አንድ መምህር የዩኒቨርስቲ የሕክምና መምህራንን የወር ደሞዝና ጥቅማጥቅም አስቦ መቶ ሺ ብር አድርሶ በትጋት አለመማሩ እንደቆጨው ከጥቅም አንፃር ብቻ እናስብ ይሆን? ከአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ በኋላስ? በኮሌጅስ? በዩኒቨርሲቲስ? የተሰጠንን ዕድል ተጠቀምን ወይንስ ዕድሜያችንን ጨረስን? በስራ ቦታስ? በአጠቃላይ ሕይወታችንስ? ዓላማ አለን?

አስባችሁት ታውቃላችሁ?

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...