2015 ኤፕሪል 20, ሰኞ

For the Ethiopian Christians Murdered in Libya

I have really been saddened to hear what happened to our fellow country men. We have not yet recovered from the pains the South African murderers inflicted upon us; nonetheless, this inhumane deed of the ISIS terrorists has left a big wound in the hearts of many of us. Sooner or later, death comes to everyone of us including these brutal murderers. When death takes your life with a an unbearable pain as to be burnt alive or slaughtered, your death is indescribable! In a situation where you are not attended to by your loved ones, given water to quench your thirst or bread to satisfy your hunger, and even more than that where you are attacked like a wild animal and when no one is able to avenge your death, there crawls sorrow in the correct sense of the word towards your loved ones! May we never hear such sad stories again! Please stop posting the ISIS photos and videos and show your sympathy to the dead and their family!

2015 ኤፕሪል 16, ሐሙስ

በዓል ባይኖር ኖሮ

የበዓል ሰሞን የሚገርም ግርግር ትታዘባለችሁ፡፡ በብዛት ሰዎች የመጎብኘት ልማድ ባይኖራቸውም በዚህ ወቅት ግን ተጓዡ ይበዛል፡፡ በሚገርም ሁኔታ የምግብ ዝግጅት፣ ሽያጭና ፍጆታ ደግሞ ይጧጧፋል፡፡ ራድዮ ጣቢያዎች የማስታወቂያ ውርጅብኝ፣ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፣ የሙዚቃ ግብዣ ብሎም የበዓል ዝግጅቶች ያበዛሉ፡፡ ቴሌቪዥን ጣቢዎችም ልክ ሰሞኑን ኢቢኤስ ከቴዲ አፍሮ ቤት የበዓል ዝግጅት እንደጋበዘን ሁሉ ቀደም ብለው የተቀረጹ ዝግጅቶችን እንካችሁ ተቃመሱ ይሏችኋል፡፡ የበዓል ሰሞን መቼም በአቅም ማነስ፣ ከቤተሰብ በመራቅ፣ በህመም፣ በምግብ አለመመቸትና ሌሎችም ምክንያቶች የሚከፋውም አይጠፋም፡፡ የመገናኛ ብዙሃኑ ደግሞ እነ እከሌ ቤት ይሄ ተበላ ይሄ ተጠጣ የሚለው ማሳበቅ ይረብሽም ይሆናል በተለይ እንዲህ የህዝቡ የኑሮ ደረጃ በተለያየበት ወቅት፡፡ ምንም ቢሆን ግን ስንትና ስንት በዓል ሲያሳልፉ የታዘቡት ብዙ ለውጥና ሁኔታ ይኖራል፡፡ ምንም እንኳን ማስታወሻ የመያዝ ልማዳችን ደከም ቢልም የማይረሱ ገጠመኞችና ትዝብቶች ስለሚኖሩ አንዳንዶቹን እያነሳን ብናወጋ ለሁላችንም ያስተምርና ያዝናና ይሆናል፡፡ ታዲያ ወረድ ብሎ ባለው የአስተያየት መስጫ ላይ እንድተጽፈልኝ ነው ይህን ማለቴ፡፡ በመጨረሻም የሚከተሉትን የውይይት ሃሳቦች እነሆ ልበላችሁ! 1. በጃንሆይ ጊዜ ትምህርት 15 ቀን ለፋሲካ ይዘጋ ነበር ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ ከሞላ ጎደል አሁንም እየተዘጋ ስለሆነ ለምን መንግስት እውቅና አይሰጠውም የሚል ሃሳቤን በትህትና አቀርባለሁ፡፡ 2. የህዝቡ ኑሮ ይሻሻል ዘንድ የሚታትሩ ሰዎች ዓላማቸው ይሳከላቸው ስትሉ ጸልዩ፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለበዓል በግ ቢያርድ ደስ ይላል! 3. የሌላ ሃይማኖት ተከታይ የሆነ ሰው እንኳን አደረሳችሁ ሲላችሁ ምላሹ ምንድነው? 4. እርጥብ ስጋ መብላት ሳይንስና ባህል ከሚጋጩባቸው ተግባራት አንዱ ነው፤ እርስዎ ከሳይንስ ወይስ ከባህልዎ ጋር ተባበሩ? 5.
ብለው አስበው ያውቃሉ? 6. የሌላ ሃይማኖት ተከታዮች በዓላቸውን ሲያከብሩ እርስዎ ምን ይሰማዎታል? 7. በዓል ሲከበር በሰው አገር ሆነው ያውቃሉ? 8. በ2050 የሚከበረውን አንድ ሃይማታዊ በዓል ስታስቡት ምን ገጽታዎች የሚኖሩት ይመስላችኋል? 9. ዘፈን ለራስዎ ወይንም ለሌላ ሰው ለበዓሉ ጋብዙ ቢባሉ የማንን ዘፈን ይጋብዛሉ? ለምን? 10. መጭውን በዓል በተሻለ ሁኔታ ለማክበር ምን ቢደረግ ጥሩ ነው ይላሉ? በመጨረሻም መልካም የበዓል ሳምንት እመኝልዎታለሁ!!!

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...