2017 ጃንዋሪ 10, ማክሰኞ

የፈረንጁ ተልዕኮዎች - ከሠሞኑ ጉዳይ ጋር የሚሄድ ልቦለድ ታሪክ





መቼም አሜሪካዊ ሆኖ እንጓዝ ከተባለ እምቢ የሚል አይኖርም - እንደውሃ መሄድ ልምዳቸው ነውና፡፡
ከመሐል ሜዳ ሸሾ ድረስ ያለው መንገድ በጣም ሩቅ ነው፡፡ ቢሆንም ያን ሁሉ መንገድ ግማሹን በመኪና ግማሹን በእግራቸው  ለመሄድ ተዘጋጁ፡፡ መንዝ ብዙም ለዓይን የሚስብ ሰው ሰራሽም ሆነ የተፈጥሮ ልማት የለውም፡፡ ያንንና ሌሎችንም እያወሩ በእግራቸው ሄዱ፡፡ ከቆሎ ማርገፊያ ወዲያ ያለው የእግር መንገድ አሰልቺና የመንዝን እርቃን የሚያሳይ አሳባቂ ነው፡፡
መንገድ ላይ ልትስመው ትፈልጋለች፤ ልትላፋው ትጥራለች፡፡ እሱ ግን ግድም አልሰጠውም፡፡ ‹‹ምን ነካው!›› የሚል ዓይነት ጥያቄ አጭሮባታል፡፡ ‹‹ያለወትሮው ደግሞ ምን አኮራው!›› የሚል ሃሳብ በአእምሮዋ ቢመጣም በዚህ ሰው ዝር በማይልበት መንገድ ላይ ምንም ጥያቄ አንስታ ልትጨቃጨቀው አልፈለገችም፡፡ በሰው አገር የሰው ሆዱ ምን ይታወቃል?
እሱ በመሐልሜዳ ትምህርት ቤት የእንግሊዝኛ መምህር ሲሆን፤ እሷ ደግሞ ከአሜሪካ በበጎ ፈቃደኝነት የመጣች ጥቁር አሜሪካዊት ነች፡፡ ከጥቁር ይልቅ አፍሪካን አሜሪካን ሲሏት ነው ደስ የሚላት፡፡ ሄደው ከእናቱ ቤት ደረሱ፡፡
መንገድ ላይ ፍዝዝ ብሎ ሲያስብም ሆነ በተደጋጋሚ ፊት ሲነሳት አንዳንዴም ከንፈሩን ሲነክስ ምን ሆነ ብላ አስባለች፡፡ ጓደኛዋ ያለወትሮው አልሆን ስላላት በዚህ ‹‹ያልሰለጠነ›› አገር ነጻነትና ስለ ሕልውናዋ ዋስትና አልተሰማትም፡፡
ከአንድ ዓመት በፊት በሚሰራበት መስሪያ ቤት በሚገኘው የመምህራን ቢሮ በር ላይ አንድ ልጅ ቆሞ ‹‹ጋሼ ሀብቱ አሉ?›› ይላል፡፡ ተማሪው ቢሮ መፈለጉን ሊነግረው ከርዕሰ መምህሩ ዘንድ የተላከ ልጅ ነው፡፡ ርዕሰ መምህሩም በታማኝነቱና እንግሊዝኛም እንደሚሞካክር በማወቃቸው ሀብቱን ወደ አዲስ አበባ ለአንድ ተልዕኮ ሊልኩት እንደሆነ ነገሩት፡፡ አዲስ አበባ ሄዶም በጎ ፈቃደኛዋን ከፈረንጆችና ኢትዮጵያውያን አስተባባሪዎች ተረክቦ ትልቅ አደራ ተሸክሞ መጣ፡፡
አሜሪካዊቷ ካሏት ድብቅ አላማዎች አንዱ መጥበስ ነው፡፡ ወንድ ጓደኛ መፈለግ፡፡ ከዚህ ሌላ ማድረግ እንደሚያስቀስፋት ታውቃለች፡፡ ሌላውን ለሌላ ጊዜ ለራሷ የቤት ስራ ሰጥታ ለአሁኑ ይህንን መምህር በፍቅር ወጥመዷ ውስጥ አስገባችው፡፡ መንዝ ካሉት ሴቶች ያነሰ ውበት ስለነበራት በመጀመሪያ ያልተሸነፈላት ይህ ለፍቅር አዲስ የነበረ ወጣት መምህር ተሸነፈ፡፡ ‹‹የሴት ልጅ ልቧ ከንፈሯ ላይ ነው›› የተባለው ለወንዶች የተነገረ ይመስል ገና ስትስመው ልቡ ፍስስ አለች፡፡
በመሐል ሜዳ ብርድ የሷን ፍላጎት ለማሟላት ማታ ማታ ከከተማው አንደኛው ወደሌላኛው ጠርዝ  የእግር ጉዞ አብሯት ያደርጋል፡፡ የሰው አፍ እንደእሳት በላኝ ብሎ ያስባል፡፡ በሳይክል ወደ ሃያ ኪሎሜትር ወደሚርቀው ጓሳ የማህበረሰብ አቀፍ ጥብቅ ስፍራ አብሯት ይሄዳል፡፡ እሱ ራሱን ለማዝናናትና እሷን ለማጀብ ሲሆን፤ እሷ ደግሞ በዚያ ያሉ በእንስሳትና እጽዋት ሀብት ላይ የሚመራመሩ አሜሪካውያንን በካምፓቸው ለማግኘትና የሆድ የሆዷን ለማውራት ስለምትፈልግ ነው፡፡ በቃ እነዚህ ደግሞ አንዴ ከገጠሙ ይልና የጓሳን ጥብቅ ስፍራ በሳይክል ሲዞር፣ ዝንጀሮ፣ ቀበሮና አይጥ ሲያይ ይውላል፡፡ የጓሳውን ምድር ሽታ ይናፍቀዋል፤ ሰላም ከከተማ ወጥታ እዚያ የተደበቀች ይመስለዋል፡፡
ድሮም አንድ አንድ አሜሪካዊ የማያጣውን መንዝ ይህች ልጅ - ሊዛ ሲንግልተን - ትንሸራሸርበት ይዛለች፡፡ ትምህርት ቤቱም ከተለመደው አሰራሩ በመጠኑ ለየት ያሉ አሰራሮችን ጨምሯል፡፡ የእንግሊዝኛ ክበቡ በጣም ተጠናክሯል፤ መምህራን በቋንቋ ስልጠና እየታገዙ ነው፡፡ አንዳንድ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን፣ ጊዜ አጠቃቀምንና የማንበብ ልምድን የመሳሰሉትን ከአሜሪካዊቷ ለመኮረጅ የሚሞክሩ እየበዙ ነው፡፡  
ሀብቱ ከዳኛቸው ወርቁ አደፍርስ ልቦለድ ላይ ‹‹እንግዲህ ምን አውቃለሁ … በእንዴት ያለ መንገድ ቅኝ አገዛዛቸውን ሊቀጥሉ እንደሚፈልጉ ነጮች›› የሚለውን የአደፍርስን ንግግር ሸምድዶ ሁሌ ሰው አጥብቆ ሲጠይቀው ይናገረዋል፡፡ ለማናቸውም እነዚህ ሰዎች ዓላማቸው አልገባ ብሎታል ሀብቱ፡፡ ሙሉጌታ ኢተፋ የተባሉ ደራሲም የአሜሪካ ቆይታቸውን በተረኩበት ዘ ቢተር ሃኒ በተባለው መጽሐፋቸው በበጎ ፈቃደኝነት ስም የሚመጡት ሰዎች የአገሪቱ የስለላ ድርጅት ሲአይኤ መልምሎ የሚያሰለጥናቸው አባላቱ እንደሆኑ የጻፉትን አንብቧል፡፡ በቅርቡ ያነበበው በዊኪሊክስ አፈትልኮ የወጣ ፋይልም ኢትዮጵያ ያለ ማናቸውም አሜሪካዊ ሰላይ እንደሆነ ተረድቷል፡፡ አንድ ዘመዱን አዲስ አበባ አግኝቶ ጠይቋቸው ግን ‹‹ልጄ ልሙትልህ ፕሬዚዳት ኬኔዲ የኢትዮጵን ሕዝብ በቅንነት ለመርዳት ያቀዱት ነው፡፡ ምንም ሌላ ተልዕኮ የለውም›› ብለውታል፡፡
‹‹አሁን እኛስ ብንሆን አሜሪካ ሄደን ስለአገራነችን መጥፎ ሊደረግ ነው የሚል ነገር ብንሰማ ዝም እንላለን?›› እያለ ራሱን ያጽናናል፡፡ አገራቸውን የሚጎዳባቸውን ነገር መከታተል ብቻ ሳይሆን ለራሳቸው ዓላማ የሰውን አገር የሚጎዳ ነገር ሊያደርጉ እንደሚችሉም ይገምታል፡፡ እሱንም እየሰለለችውና የመረጃ መሰብሰቢያ እያደረገችው እንደሆነ ይጠረጥራል፡፡ ራሱን እንደከሃዲ የሚቆጥርበትም ጊዜ አለ፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ መንግስት መቼም መጥፎ ይሰራሉ ብሎ ቢያስብ አያስገባቸውም ነበር›› ብሎም ሳያስብ አልቀረም፡፡
በዩኒቨርሲቲ ትምህርቱ ወቅት ይግባባቸው የነበሩት ሕንዳዊ መምህሩ በሀገሩ ላይ የአሜሪካ ተጽዕኖ መብዛቱ በጣም እንደሚያሳዝናቸው ነግረውት ወደፊት ግን ይህን ለመቀልበስ መሰራት እንዳለበት አሳስበውት ነበር፡፡ ‹‹ሕንድ በፍጹም አሜሪካውያንን ወደ ፖለቲካዋ አታስገባም›› ያሉትን አይረሳም፡፡ ‹‹ብናስገባ እንደ ሽንት ቤት ወረቀት ተጠቅመው እንደሚጥሉን እናውቀዋለን፤ እስኪ ኢራቅንና አፍጋኒስታንን እይ!››
በዚህ ሁሉ መሀል የወደዳት የዚህች ልጅ ነገር ይከነክነዋል፡፡ መቼም አንድ ጊዜ ተነካክቷል፡፡ ‹‹ወይ አሜሪካ ትወስደኝ ይሆናል›› እያለም የተመኘበት ጊዜ አለ፡፡ እዚያ ሄዶ እንደሁኔታው አብሯት ለመኖር ወይንም ትቷት ላሽ ለማለት አስቧል፡፡ እቤታቸው በተሰቀለው የቀን መቁጠሪያ ላይ ሳይቀር የኖሯቸውን ቀናት እየሰረዘ አሜሪካ ለመሄድ የቀሩትን ቀናት ይቆጥራል፡፡ እንደ እርጉዝ አድርጎታል፡፡ የምን እርጉዝ ነው ደሞ? ይቺ ልጅ አታስረግዘው!
ዘ አዲስ ኦብዘርቨር የተባለው የእንግሊዝኛ ጋዜጣ ‹‹አሜሪካዊቷ መንዝ ውስጥ ታግታለች›› የሚል ዘገባ ይዞ ከወጣ ወዲህ ነገሮች በጣም ተካረዋል፡፡ በሁለቱ መንግስታት በጋራ የሚመራ ግብረሃይል ተቋቁሞ መንዝን ያስስ ይዟል፡፡ ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ፍለጋው ተጧጡፏል፡፡ ልጅቱ ያለችበትን ላወቀ የሚሰጥ ገንዘብ ግን የአሜሪካ መንግስት ቃል አልገባም፡፡ በአገሪቱ ህግ ይህን ማድረግ አሸባሪዎችን የበለጠ ስለሚያጠናክር አይበረታታም - ወንጀልም ነው፡፡
መንዞች ደርግ በአውሮፕላን ስለደበደባቸው አውሮፕላንም ሆነ ማናቸውንም በሰማይ ላይ የሚበር አካል ይፈራሉ፡፡ አሁን ሄሊኮፕተሮች መንዝን ያስሷት ገቡ፡፡ ድሮኖችም በፍለጋው ተሰማርተዋል፡፡ ህዝቡም እንዳሞራ ይቆጥራቸው ይዟል፡፡ ከየማሳው ዳር ሄሊኮፕተሮች እያረፉ ገበሬዎችን ይጠይቁ ይዘዋል፡፡ የመሐልሜዳው ትምህርት ቤት መምህራንና ማህበረሰብ፣ የልጅቱ ቤት አከራዮችም ሆኑ ጓሳ ላይ ያሉት አሜሪካውያን ይታመሳሉ፡፡ ከወንድ ጓደኛዋ ጋር መጥፋቷን የሚጠቁሙ መረጃዎች የደህንነት ባለስልጣናት አግኝተዋል፡፡ ግን ወዴት ጠፉ ነው ጥያቄው፡፡ አሜሪካዊቷን የሚያውቋት ሰዎች በአንድ መሐልሜዳ ባለ ጠጅ ቤት ስለጉዳዩ ያወራሉ፡፡ ‹‹አሁን ይችን ባሪያ የአሜሪካ መንግስት ፈልጓት ይሆን? ጠብሶስ ቢበላት ምን ቸገረው? የያዘችው የስለላ መረጃ ይኖራል እንጂ? ደሞ ለጥቁር ምን አስጨነቃቸው! የማናውቃቸው!›› ይላል አንድ የቀድሞ ወታደር፡፡ ጡረተኛው ወታደር ብዙም ለሕይወቱ ስለማይሰጋ ነው እንጂ ሰላይ እንደ አፈር ሞልቶበታል በሚባለው ከተማ ማንም ደፍሮ ስለዚህ ጉዳይ አያወራም፡፡
ሀብቱ በቤተሰቦቹ ቤት አቅራቢያ ባለ ዋሻ አጠገብ እንደታየ የአካባቢው ሰዎች ጥቆማ ሰጡ፡፡ ለመሾምና ለመሸለምም ተጣጣሩ፡፡
‹‹አሁን ሆድሽን ሳልዘረግፈው እውነቱን ታወጫለሽ አታወጪም?›› እያለ ጩቤውን እያሳየ ዋሻ ውስጥ ከወንድሞቹ ጋር ሆኖ ያሽቆጠቁጣታል፡፡ ‹‹እዚህ አገር ለምንድነው የምትላኩት?› ዓላማችሁስ ምንድነው? ባለፈው ከጓደኞችሽ ጋር በስፓኒሽ ስታወሩ ቋንቋውን አያውቅም ብላችሁ ነበር?›› እያለ ወጥሮ ይዟታል፡፡ ጎንደር አስጎብኚ ለሆነ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አብሮት ለተማረ የቅርብ ጓደኛው ከጓደኞቿ ጋር ሲያወሩ የቀረጸውን ኦዲዮ ልኮለት ትርጉሙ ባለፈው ሳምንት ነው የደረሰው፡፡ ‹‹በሀገሬ ላይ የምታደርጉትን አውቃለሁ›› አላት እንባው እየፈሰሰ፡፡ በስፓኒሽ ካወሩት ውስጥ ወንዶቹ አሜሪካውያን ወንድ ኢትዮጵያውያን ፍቅረኞች እንዳሏቸው ያወራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት መጤ ሳይሆን ነባር እንደሆነ ህዝቡን ማሳመን እንዳለባቸው ያቅዳሉ፡፡
ሊጨክንባት እንደሚችል በመገመት ሁሉንም አፍረጥርጣ ነገረችው፡፡
‹‹እሺ እኔንስ የሰራሽኝ ጉድ?›› ብሎ አንድ ከእናቱ ጋር የቆመ ልጅ ፎቶ አወጣ፡፡ የዚያን ጊዜ ይህች ልጅ የምትገባበት አጣች፡፡ አለቀሰች፡፡ ትንቀጠቀጥ ያዘች፡፡ የሀገሯን ምስጢር የነገረችው በሆነ መንገድ ከዚህ ቦታ ከወጣች ይህን ሰው የምታስወግድበትን መንገድ አስባ ነበር፡፡ አሁን ግን መውጫ ቀዳዳ የሌለውን ነገር አመጣባት፡፡
አንድ ቀን አንዳንድ ነገሮችን እየተጠራጠረ ሲመጣና በተመሳሳይ ጾታና ተያያዥ መጤ ጉዳዮች ላይ ያላትን አቋም ሲያይ የፌስቡክ የይለፍ ቃሏን ያውቅ ስለነበረ እስካሁን ድረስ በፌስቡክ የተላላከቻቸውን መልዕክቶች ሁሉ ወደኮምፒውተሩ አውርዶ ያዘ፡፡ ከዚያም የልጅነት ፎቶዋን አገኘው፡፡ ስምንተኛ ክፍል ሳለች የተነሳችው፡፡ ያኔ ወንድ ነበረች፡፡ ከጥቂት አመታት በፊት ተመጣጣኝ ሕክምና ወደሚገኝበት ወደ ሕንድ ሄዳ ሙሉ በሙሉ ጾታዋን አስቀየረች፡፡ ወንድነትን ፈጽሞ አትፈልገውም፡፡
ማይክል ጃክሰን ወደ ነጭነት መቀየሩን ያውቃል፡፡ በልጅነቱ ቡዳ የበላቸው ሰዎች ወደ እንስራነት እንደሚቀየሩና እንደሚሰወሩ ከመስማቱ በቀር ይህን ዓይነት ጡት የሚያበቅልና ሁለመናን ሴት የሚያደርግ ነገር አልሰማም፡፡ እንዴት ይጠርጥር?
ይህን ሁሉ ጉድ ካወጣ በኋላ፡፡ ‹‹ገደል ከምሰድሽ በፊት የምትናገሪው ነገር አለሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡ ‹‹ያለሁበትን ሁኔታ ተረድተህና እኔም አፍሪካዊት እህትህ እንደሆንኩ አስበህ ይቅርታ አድርግልኝ›› አለችው፡፡ ከአሁን በኋላም እንደማትሳሳት ቃል ገብታ ወደ ገዳም አብረው እንዲመንኑ ነገረችው፡፡ እኔ እንዳንቺ ያለን ከሃዲ ገዳም አልወስድም ብሎ የተፈጸመውን ለማንም እንዳትናገር አድርጎ ወደመጡበት ተመለሱ፡፡ ጉዳያቸውም በሚገርም አዘጋገብ ተዘገበ - ለማንም ሳያሳውቁ ጉብኝት ሄደው የነበሩት ጥንዶች ተገኙ፡፡  በ24 ሰዓታት ውስጥም ይህች/ይሀ አሜሪካዊ ስፍራውን ለቆ/ቃ እንዲ/ድትሄድ ተደረገ፡፡ የደረሰበ/ባትን ግን ለማንም ትንፍሽ አላለ/ችም ነበር፡፡ አሁን ግን ወደ ማተሚያ ቤት የገባ ‹‹ድብቁ የአጋች ታጋች ድራማ በሐበሾች ምድር›› የሚል መጽሐፍ ጽፎ/ፋ መግቢያውን ጻፍልኝ ሲል/ስትል የመጽሐፉን ሶፍት ኮፒ ለመንዜው መምህር ላከ/ችለት፡፡
‹‹መጽሐፉን በነጻ በኢንተርኔት ልልቀቀውና ላክስራት ወይንስ እንዳሰበችው መግቢያ ልጻፍላት?›› እያለ ይብከነከናል፡፡ ራሱን በራሱ ለማዋረድ ይፍቀድ ወይንስ ምን ይሻለዋል ትላላችሁ?
‹‹የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም›› ብሎ ጨክኖ ይጻፍላት ወይ? በ1977 እኤአ አሜሪካውያኑን ጠራርገው እንዳስወጧቸው እንደነ መንግስቱ ኃይለማርያም አይነት ወኔ አምጥቶ ይጨክንባት? ‹‹ ዛሬ አገሪቱ ለአሜሪካ እጅ ሰጥታ ከጉያዋ ተደብቃ ሳለ የኔ እምቢተኝነት የምን ይሉታል?›› እያለ እያንገራገረ ነው፡፡  
ይቺ ሴት ቢያንስ እንግሊዝኛ ያሰለጠነችውንና ዘመናዊነትን ያስተማረችውን እንዴት ይዘነጋዋል? እሱን ለመጉዳት ብላ ያደረገችው ነገር ነበር እንዴ? መንዝ ላይ በ2500 ብር ደምወዝ በዚያ ብርድ ተሰቃይታ ህዝቡን ያገለገለችውንስ? ለሷ መግቢያውን ከጻፈላት እሱም ሲጽፍ የቆየውን ማስታወሻውን ማሳተምና ለሀገሩ ሕዝብ ማጋራት ይችላል፡፡ አሜሪካንን ለመጎብኘት ያቀረበችለትንም ሀሳብ ይስማማበት ይሆናል፡፡ መጽሐፉንም አብረው ሊያስመርቁም ይችላሉ፡፡ የሱንም መጽሐፍ ህትመት ስፖንሰር ልታደርግለት ትችላለች፡፡ ነገሩ ሁሉ እርቃኑን ሲያስቀረው ተበሳጭቶ የሚገባበት አጥቶ ራሱን ቢያጠፋስ?


2017 ጃንዋሪ 5, ሐሙስ

The Libraries I Have Been to and related memories


It was teacher Haileyes who declared at lunch time that Sasit School opened a new library. I think I was in grade five then. One day our class was invited to read by teacher Shibeshi. All of us went into the room which had dirt floor. A corrugated iron roof, walls made of wood and mud and simple wooden door and windows made the library. The room was furnished with furniture made of locally available resources. I read a children’s story which was about people who travelled from Addis to Dire Dawa by train. They were sharing their food and showing hospitality for each other. I can’t tell if it was the “Shilingen” story many people narrate to me. At other times I remember reading about Aba Kostir, Belay Zeleke, an Ethiopian hero of the Gojjam region. (I travelled by train just last year!) The teacher who organized that library at Sasit School should be praised!
A small wicked boy! One of my memories of this library is him!  This small boy was older for that grade level. He had to be in grade nine if he attended class well. He would fail and every small boy and girl whose birth date he remembers becomes his classmate. They would pass to the next grade and he would fail. This boy would jump and catch the collars of his superiors, hit them with a header and run away. Imagine a short and stout boy hitting you and running. If you read Mulugeta Gudeta’s novel, Evil Days, you will understand me. That major character who catches birds, breaks their legs and wings and lets them suffer – this one did just the same thing  with birds. When I remember how he frightened us it shocks me! He would frighten everyone. He had stories of beating or being beaten every day. One day he stole a storybook from the school library and hid it in his bag. As every one of us, he had a bag sewn from pieces of sack. “If anyone in this class tells about this book to anyone, I will kill him!” he would frighten us. No one informed the teachers. For this reason, that boy was not held and the story of the book was forgotten. I think he kept that book for his daughter who is in grade one or two now.
Haile Mariam Mamo school library had wide tables. I read only some reference books there. I was not a person who frequents libraries. Most of the time I even found doing home works hard. This could be because of my laziness or the chills of Debre Birhan. I think I was not matured enough to receive the high school lesson. To tell you about the school, it was like a university at least in the capacity of the teachers.
Addis Ababa University has many libraries. The biggest one is the J. F. Kennedy Library, which has a ground floor and two other floors. I read some books there. I also borrowed some. The English Department of the University, which I joined, is where students are kept without reading as is the case elsewhere in the country. There is my weakness too. We were not given assignments and reading tasks. The current minister of government communication affairs, Dr Negeri Lencho, who taught us two public relations courses, gave us handouts that we did not go to the libraries. There are others who give nothing. In my graduate class I frequented the graduate library and spent some nights reading there. The library of the Institute of Ethiopian studies has a rich collection for students of the humanities and social sciences. There is also the library of the Institute of Language Studies (ILS). I heard that the floor where the library was found is given to the Chinese for their Confucius Institute. I can’t tell about the fate of the library. Memorable ILS! Others joked at as ‘I Like Sleeping’, ‘Institute of Lazy Student’ etc.
There are rare books at the library of the United States Embassy. Wemezekir is also good for people who can’t access school libraries.
The private school I worked in for a few months had a good small library that consisted of used donated books and cassettes from the British Council among others. My friend who worked at another school stole two books when he left the school. You just don’t read such books, you know! I know none who read stolen books. Just another book stealing I remember. Oh, another guy also stole Afework Gebreyesus’ novel from a school he was working in Oromia and he used to take it to khat houses. No one saw him read it though.
Debre birhan university libraries are expanding. They are trying to modernize them. More technology should come and students should access the lending service. The 24 hour service is admirable.
This idea of private libraries is what I am experimenting nowadays. I have opened Ras Abebe Library and Bookstore last year. We expect to learn from all the libraries we knew and new developments shall come in the near future. Housing is one of our problems. Capital is also the key. To enhance the people’s interest in reading, we should find a means. The Library of Congress is where I want to read in the future. Nowadays, digital libraries are new developments that made everyone access books everywhere. Anyhow, I think everyone of us has memories of actual libraries. Do you?

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...