2016 ጃንዋሪ 29, ዓርብ

(ከእኛ በላይ) - ተርጓሚ - መዘምር ግርማ



We Are the World
(ከእኛ በላይ) - ተርጓሚ - መዘምር ግርማ
ይህ ዘፈን ‹አሜሪካ ለአፍሪካ› የተባለው ቡድን ያዘጋጀውና  በወቅቱ የዓመቱን የግራሚ የነጠላ ዜማ ውድድር ያሸነፈ ነው፡፡ 60 ሚሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ የተቻለበትና ከ20 ሚሊዮን በላይ ኮፒ የተሸጠለት ይህ ዘፈን በኢትዮጵያ በረሃብ ለተጠቁት ወገኖች ታስቦ የተዘፈነ ነው፡፡ ዛሬ ጥር 20 ቀን 2008 ዓ.ም. ዘፈኑ ከተቀረጸ 32ኛ ዓመቱን ደፍኗል፡፡ ማይክል ጃክሰንና ሊዮኔል ሪሼ የጻፉት ይህ የዘፈን ግጥም ወደ አማርኛ እስካሁን መመለሱን አላወኩም፡፡ እንዲያውም ዘንድሮው በሃገራችን በተከሰተው ረሃብ ለተጎዱት ወገኖች እርዳታ ለማሰባሰብ የሚችል አካል በጥሩ ሁኔታ ተርጉሞ በሙዚቃ መልክ ቢያወጣው ጥሩ ይሆናል እላለሁ፡፡ እኛ ደብረ ብርሃን ላይ ባለን ግጥም በመሰንቆ መርሃ-ግብር ዛሬ ማታ የዚህን ዘፈን ተሳታፊዎች በሙሉ ልናስብ ተዘጋጅተናል፡፡ 0913 65 88 39

(ከእኛ በላይ)

አንድ ማያችን አሁን ነው ይህን የዋይታ ጥሪ
ዛሬ እንኳን ይሙላልሽና እስኪ ዓለም  ተባበሪ
ሰዎች እንደዋዛ ሲሞቱ
መታደጊያው መጣ ጊዜያቱ
ታላቁን ስጦታ ዛሬ አበርክቱ

መቼም ቀን በቀን በማስመሰል አንኖር
ላጣዳፊዋ ችግር ከየጎራው እንተባበር
የአምላክ ታላቅና ድንቅ ቤተሰብ ስለሆናችሁ
አንድ እውነታ እንንገራችሁ
ይርበናል ንጹሕ ፍቅራችሁ

ለዓለም እኛው ነን ልጆቿ
ደስታ እማጪ አለኝታዎቿ
እስኪ ቸርነትን እናድርግ
ህይወታችንን እንታደግ
በምርጫችን …
እኔም፣ አንተም፣ አንቺም
የተሻለች ነገን እናልም

ከልባችሁ አቅርቧቸው
እንደምታስቡላቸው ይረዱ
ለብርቱ ነጻ ሕይወት ይሰናዱ
አምላክ ድንጋይን ዳቦ እንዳደረገልን
እኛም ልግስና ይልመድብን

ተስፋቸውን እንዳያጨልም የኛ ቸልታ
ምርጫም የለን የሚያዘናጋ ላፍታ
አብረን ስንቆም አሁኑኑ
ለውጥ እንደሚመጣ ተማመኑ፡፡

"We're The World (USA For Africa)"
There comes a time when we heed a certain call
When the world must come together as one
There are people dying
And it's time to lend a hand to life
The greatest gift of all

We can't go on pretending day by day
That someone, somewhere will soon make a change
We all are a part of God's great big family
And the truth, you know,
Love is all we need

[Chorus:]
We are the world, we are the children
We are the ones who make a brighter day
So let's start giving
There's a choice we're making
We're saving our own lives
It's true we'll make a better day
Just you and me

Send them your heart so they'll know that someone cares
And their lives will be stronger and free
As God has shown us by turning stone to bread
So we all must lend a helping hand

[Chorus]

When you're down and out, there seems no hope at all
But if you just believe there's no way we can fall
Well...well...well
Let's realize that a change can only come
When we stand together as one

[Chorus]

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...