2019 ማርች 31, እሑድ

በ‹‹የአንኮበሩ ሰው በጄኔቫ›› መጽሐፍ ምረቃ ወቅት ደራሲው ከተናገሯቸው

በ‹‹የአንኮበሩ ሰው በጄኔቫ›› መጽሐፍ ምረቃ ወቅት ደራሲው ከተናገሯቸው ሃሳቦች የወሰድኩት ማስታወሻ
ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን በእናቱ አንኮበሬ ነው፡፡ ቡም ቡም ቡም … ኢትዮጵያ ተፈጠረች አለ ጸጋየ ገብረመድህን አውሮፓ ጠርቼው መጥቶ ለፈረንጆቹ ንግግር እያደረገ፡፡ የሚገርም ችሎታ ያለው ሰው ነው፡፡ ሎሬት አፈወርቅ ለአንኮበር የተቻላቸውን ባለመስራታቸው ይቆጩ ነበር፡፡ ከአፍሪካ ወደ ጨረቃ የተላከው የአፈወርቅ ስም ነው፡፡
እዚህ የምንጃር፣ የጅሩ፣ የተጉለት ሰው ወይም ዘፈን እያልን እናጠባለን እንጂ ጎንደሬ ጎጃሜ እንደሚለው አናሰፋም፡፡ እንደ ሃገር (ኢትዮጵያ) ትልቅ ህዝብ ነው የያዝነው፡፡ አሁን መፍረክረክ የጀመርን ይመስላል፡፡ ኢትዮጵያ ግን አትወድቅም፡፡ ዛሬ ብዙ ኃይል አለን፡፡ 43 ዩኒቨርሲቲ አለን፡፡ የትምህርት ጥራት ጉዳይም ከሆነ ትምህርት አንጎልን መክፈት ብቻ ነው፡፡ ሰፋ አድርገን እንድንመራመር ያስችላል፡፡ ውጤት ያመጣል፡፡
የቢዲቲ ውድድር ላይ የገጠመኝ ችግር ትግሬ አማራ በሚባል በማይረባ ነገር ለ190 አገር ቴሌግራም ተላከ፡፡ የመንግሥት ባለስልጣኖችን ከመውቀስ ይልቅ ማስተማርን እመርጣለሁ፡፡ ዶክተር ቴድሮስ መመረጡ ብዙ ሰውን ያነሳሳል፡፡ አገርንም ይጠቅማል፡፡ ደስተኛ ነኝ፡፡
ኮፊ አናን መጀመሪያ ስራ የጀመረው አዲስ አበባ ነው፡፡ ውጪ ያለው ኢትዮጵያዊ 40 ዓመት እዚያ ኖሮ የሚበላው እንጀራ፣ የሚያስበው የሃገሩን ፖለቲካ ነው፡፡ ያንን ኃይል መጠቀም ይኖርብናል፡፡ ልጄ ከ500 – 600 ሰራተኛ ያለው ድርጅት ለንደን ላይ አላት፡፡
ጠባብ ማንነት የሚባል አዲስ ማንነት አልሰማም - ኢትዮጵያዊነታችንን እንጂ፡፡ በአጼ ምኒልክ አስተሳሰብ ሁሉም አንኮበር ነው፡፡ አዲስ አበባም አንኮበር ነው፡፡ የአንኮበሩን ሙዚየም የምንከፍተው የአስተዳደሩን ስራ ጨርሰን ነው፡፡ ቦይ ስካውት ደርግ አጠፋው እንጂ ጥሩ ነገር ነበር፡፡ አሁንም አላንሰራራም፡፡ አንድ ስካውት ሁልጊዜ ያፏጫል፣ ፈገግታም ያሳያል፡፡ ኢትዮጵያ የዓለም ማዕከል ነች፡፡ ፈረንጆች ይፈሩናል፡፡ እኛም በራሳችን እንተማመን ነበር፡፡ ጥቁር የኛን ባንዲራ ነው የሚያውለበልበው፡፡ ፈረንጁ የሚያጠቃን ለዚህ ነው፡፡ ደብረ ብርሃን እንዲህ ሆና ማየቴ ያስደንቀኛል፡፡ መጽሐፉ ሽቦሽቦ እንዳይሸት የግል ታሪኬን ጨመርኩ እንጂ ዋናዎቹ አባሪዎቹ ናቸው፡፡ ለምሳሌ Is global telecommunication feasible የሚል አለበት፡፡ የዓለም ሕዝብን ማስተሳሰር ይቻላል፡፡ ቴሌኮሚኒኬሽን በሁሉም ውስጥ ያለ ነው፡፡ በደንብም ለመብላትና ለማስተዳደር ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ያስፈልጋል፡፡ From Tam tam to the Internet የሚል ኮፊ አናንና ማንዴላ መግቢያውንና መቅድሙን የጻፉበት መጽሐፍም አለኝ፡፡ ለምርምር መነሻ ይሆናሉ፡፡
ግራሃምቤል ስልክን በፈጠረ በሰባት ዓመት ውስጥ አንኮበር ስልክ ገብቷል፡፡ የመጽሐፉን ርዕስ ሆን ብዬ ነው ያደረኩት፡፡ አንድ ሁለት ቀንም ቢሆን ፍየል አግጃለሁ፡፡ አንድ የአንኮበር ባላገር ከአንኮበር ተነስቼ፣ 70 አገር ጎብኝቼ፣ የዓለም መሪዎችን አግኝቼ፣ የዓለምን ቴሌኮሚኒኬሽን ለውጬ፣ አንድ ሰው ተግቶ ከሰራ የት መድረስ እንደሚችል ምሳሌ እንዲሆናችሁ ነው፡፡
ድሮ አፍሪካ በቴሌኮሚኒኬሽን ከሌላው ዓለም ትበልጥ ነበር፡፡ አንድ መርከብ ናይጀሪያ ሰምጣ በሶስተኛው ቀን ምስራቅ አፍሪካ ተሰምቶ ነበር፡፡
ዩኒቨርሲቲዎች ታሪክ ትዘጉ! 43ቱም ታሪክ አስተምሩ፡፡
በመጽሐፋቸው ላይ ያቀረብኩትም ዳሰሳ ‹‹የአንኮበሩ ሰው በጄኔቫ›› በሚል ርዕስ ከገጼ ይገኛል፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...