2018 ጁን 8, ዓርብ

ሴት ተመራማሪዎችና የምርምር ተግዳሮቶቻቸው

በትዝታ ገበየሁ

tizitageb12@gmail.com

መምህርት ትዝታ ገበየሁ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሐብት መምህርት ናቸው፡፡



የዩኒቨርስቲ መምህራን በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው ውስጥ ማስተማር፣ በየጊዜው ምርምሮችን መስራትና የማህበረሰብ አገልግሎት መስጠት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ጥናትና ምርምር ለመምህራን ከመማር ማስተማር ስራቸው ጎን ለጎን ሊያከናውኑት ግድ የሚል ተግባር ነው፡፡ ምርምር ተከታታይ ትግበራን ብዙ ጊዜ መመደብንና ቁርጠኝነትን የሚጠይቅ ስራ ነው፡፡

በዩኒቨርስቲዎች  በማስተማር ላይ ያሉ መምህራን የምርምር ስራቸውን ሲያከናውኑ ከመደበኛ የማስተማር ስራቸው ላይ የተወሰኑ ሰዓቶች ይቀነሱላቸዋል፡፡ ምክንያቱም ለመመራመር ያስችላቸው ዘንድ የሚያስፈልጋቸውን ጊዜ ሰፋ ለማድረግ ሲባል ነው፡፡ 

ምርመር የሚሰሩ መምህራን ማበረታቻ ይሆናቸው ዘንድ ክፍያም ይከፈላቸዋል፡፡ ታዲያ ይህ ሁሉ በጎ እገዛ ለምርምርና ለተመራማሪዎች እየተደረገ ባለበት ሁኔታ ውስጥ በየዪኒቨርስቲዎቻችን ያሉ ሴት መምህራን ለምን የሚፈለገውን ያህል ምርምር ላይ አይሳተፉም? ለመመራመር በሚነሱበት ሰዓትስ ምን ችግሮች ይገጥሟቸው ይሆን? ምንስ መፍትሄ ለተግዳሮቶቻቸው እንስጥ? በዛሬው ዕለት ብዕሬን ያነሳሁለት ርዕሰ- ጉዳይና ልመልሰው የወደድኩት ጥያቄ ይህ ነው፡፡ መልካም ንባብ፡፡

ሴት መምህራን በተለይም ደግሞ በቤት ውስጥ ከሚስትነት ባለፈ ኃላፊነት ያለባቸው ከሆነ  ለመመራመር ቢፈልጉም ያቅታቸዋል፡፡ ምክንያቱም የማስተማር ስራቸውን በቶሎ አጠናቀው ወደየቤታቸው መሔድና በቤት ውስጥ ደግሞ ልጆቻቸውን፣ ባሎቻቸውን ብሎም ቤተሰቦቻቸውን መንከባከብ ስላለባቸው ነው፡፡ ሴት ልጅ የቱንም ያህል ጠንካራ፣ ቆራጥና ብርቱ ሰራተኛ ብትሆን አብዛኛውን ጊዜ ልጅ የመንከባከቡ ኃላፊነት ከምትወደው ስራዋ ወደኋላ ያስቀራታል፡፡ ምርምር ማካሄድ ብትፈልግ እንኳን በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ባላጠናቅቀውስ? ጀምሬ ባልጨርሰውስ?  ቤቴን ቢጎዳብኝስ? የሚሉ ስጋቶች ከተሳትፎዋ እንድትቆጠብ ያስገድዷታል፡፡

በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የወንዶች የበላይነት ነግሶ በሚስተዋሉባቸው ሀገራት አድገው ተምረው ስራ ለያዙ ሴት መምህራን የባሎች እገዛ እንደ ግዴታ መውሰድና መተግበር ከባድ ሊሆን ስለሚችል ሴቷ ሁሉን ኃላፊነት ከመውሰድ ውጪ አማራጭ አይኖራትም፡፡ የኃላፊነቶች መደራረብ ደግሞ በማስተማር ስራዋና በምርምር ግዴታዋ ላይ አሉታዊ ተፅ  ይኖረዋል ማለት ነው፡፡

በምርምር ስራ ላይ ተሳትፎ እያደረገች ያለች መምህርትንና ምንም የምርምር ተሳትፎ የሌላትን መምህርት ለማነጋገርና ለምርምር ስራቸው ተግዳሮት የሆኑባቸውን ጉዳዮች ለማወቅ ጥረት አድርጌ ነበር፡፡

በቅድሚያ በምርምር ስራ ውስጥ ተሳትፎ ያላት የኬሚስትሪ  ትምህርት ክፍል መምህርት የሴት መምህራንን የምርምር ተግዳሮቶች እንዲህ አስረድታኛለች፡፡

መምህርት መቅደስ ጌራወርቅ የሁለት ልጆች እናት ብትሆንም የመምህርነት ስራዋን ከጀመረችበት ቀን አንስቶ ምርምሮችን እየሰራች ትገኛለች፡፡ ‹‹ሴት መምህራን ብዙ ኃላፊነቶች ቢኖሩባቸውም ከቤት ውስጥ ስራቸውና ከማስተማር ተግባራቸው ባሻገር ምርምር መስራት ያላቸውን እውቀትና ክህሎት ለማዳበር ያግዛቸዋል›› ብላኛለች፡፡ ሴት ተመራማሪዎች ለመረጃ ስብሰባ በሚወጡበት ጊዜ ረጅም ርቀት ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው ከመጓዝ አንስቶ መረጃ እስከመከልከል የደረሱ ተግዳሮቶች እንደሚገጥሟቸው ነግራኛለች፡፡

ሁሉም ሰው ሴትም ሆነ ወንድ በምርመር ስራው ውስጥ እንቅፋት እንደማያጣው በማሰብና እኛ ሴቶች ላይ ብቻ የተከሰተ ፈተና አለመሆኑን መቀበል የሚችል ቀና ልቦናና ስራን በአግባቡ ከፋፍሎ መስራት ዋነኛ የስኬት ሚስጥሮች መሆናቸውን / መቅደስ ረገጥ አድርጋ ትናገራለች፡፡ በቤት ውስጥ ከትዳር አጋሯ ጋር በተግባቦት መኖር መቻሏና የትዳር አጋሯ እገዛ የምርምር ስራዋ ላይ እንድታተኩር ድጋፍ እንዳደረገላት ብሎም የራሷም ቁርጠኝነት እስከአሁን ላጠናቀቀቻቸውና አሁንም  በመስራት ላይ ላለቻቸው የምርምር ስራዎች እገዛ እንዳደረጉላት ገልፃልኛለች፡፡

ቀጥዬ ያገኘኋት ሴት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ የኢንጅነሪንግ ኮሌጅ መምህርት ስለ ሴትነትና ምርምር እንዳወራት ስጠይቃት ፈቃደኛ ብትሆንም ስሟን እንድገልፅ ግን ፈቃድ አልሰጠችኝም፡፡ መምህርቷ የሲቪል ምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህርት ስትሆን የአንድ ሴት ልጅ እናት መሆኗን ገልፃ በቤቷ ውስጥ ከፍተኛ የስራ ጫና እንዳለባትና በትምህርት ክፍሏም ከፍተኛ የማስተማር ግዴታ እንዳለባት በቆይታችን ለመረዳት ችያለሁ፡፡ ‹‹ማስተማሩንም የማልተወው ሆኖብኝ ነው፤ እንኳን ምርምር ልሰራ›› ብላም ፈገግ አሰኝታኛለች፡፡ ከባለቤቷ ጋር ያላቸው መተጋገዝ እንዴት እንደሆነ የማወቅ ጉጉት አድሮብኝ ስለነበር ጥያቄውን አንስቼባት ነበር፡፡ ባለቤቷ እሷንም ሆነ ልጇን በሙሉ ልቡ የሚወድ ቅን ሰው ቢሆንም የቤት ውስጥ ስራ ፈፅሞ የማይሆንለት መሆኑን ነግራኛለች፡፡ ‹‹በመሆኑም ሙሉ ሰዓቴን በማስተማር ስራና ቤተሰብን በመንከባከብ አጠፋለሁ፡፡ ለምርመር ግዜ ያስፈልጋል፡፡ እሱ ደግሞ የለኝም፡፡ የራስ ተነሳሽነቴንም እጠራጠረዋለሁ›› ብላለች፡፡

በመጨረሻ ለመረዳት ከቻልኳቸው ነገሮች አንዱ ለሴት ተመራማሪዎች ዋነኛው ተግዳሮት የቤት ውስጥ የስራ ጫና ብቻ አለመሆኑ ነው፡፡ ከሴቶቹ ከራሳቸው የተነሳሽነት ማነስ የቤተሰቦቻቸው ድጋፍ አናሳ መሆንበምርምር ስራዎቻቸው የሚገጥሟቸው ተግዳሮቶች ለምሳሌ የመረጃ አሰጣጥ ሂደት ላይ ለሴት ተመራማሪዎች ትክክለኛ መረጃ አለመስጠት ፆታዊ ትንኮሳና የመሳሰሉት እንደ ተግዳሮት ያየኋቸው ሲሆኑ ሴት ተመራማሪዎች ጠንካራ መንፈሰ-ብርቱ ለተሰማሩበት የስራ መስክ የተሰጡ መሆን እንደሚገባቸው ማስተዋል ያሻዋል፡፡ ስራን ከፋፍሎ በተቀመጠው እቅድ መሰረት መተግበር ብሎም የስራንና የግል ሕይወትን ለይቶ ማየት ለሴት ተመራማሪዎች በምርምር ስራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያግዙ መንገዶች  ናቸው፡፡

በመሆኑም ሴት መምህራን ከማስተማር ባለፈ ጥናትና ምርምር ላይ መሳተፍ ለወንድ መምህራን ብቻ የወጣ መመሪያ እንዳልሆነ ተረድተው በምርምር ስራዎች ላይ መሳተፍ እንዲችሉ   እመክራለሁ፡፡ አበቃሁ፡

                                                    

2018 ሜይ 31, ሐሙስ

‹‹የሆሄ ጉዳይ ፈታኝ ነው፡፡›› መምህር ገብረሐና ዘለቀ


‹‹የሆሄ ጉዳይ ፈታኝ ነው፡፡›› መምህር ገብረሐና ዘለቀ
ሐሙስ ግንቦት 23፣ 2010 ዓ.ም. በራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት በነበረው የውይይት ምሽት ‹‹የአማርኛ ፊደላት አጠቃቀማችን›› በሚለው ርዕስ ላይ ተወያይተናል፡፡ ርዕሱን የመረጠልን ሳሙኤል በለጤ ሲሆን ሊመርጥልን ያነሣሣውም በማህበራዊ መገናኛ ብዙኃን እንግዳ የሆኑ ፊደሎች በእጅ ተጽፈው ለትዝብት ፎቷቸው ተለጥፎ ማየቱ ነው፡፡ ቁልፍ የሚል ጽሑፍ ላይ የ‹ል› ቀለበት ዞራ ያለውን ምስል ልብ ይሏል፡፡
በውይይታችን ወቅት በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡን ጋብዘናቸው የተገኙልን መምህር ገብረሐና ዘለቀ በደብረ ብርሃን መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የሥነሕይወት መምህር ናቸው፡፡ የሰጡንን ሐሳብ ሙሉ በሙሉ ማስፈር ባልችልም አልፎ አልፎ እጠቅሳለሁ፡፡
እንግዳችን በሆሄ ቀረጻ ነው እንጂ በድምጻቸው ላይ እንዳልሰሩ ይናገራሉ፡፡ ለእርሳቸው ድምጹ ሌላ ጉዳይ ነው፡፡ በኦሮምኛ ፈትና በአማርኛ ፈት ተማሪዎች ላይ የተደረገ ምርምር አላቸው፡፡ በፊደል አቀራረጽ ላይ በቤተመጻሕፍቱ አባላት ላይ መጠነኛ ፍተሻ አድርገው በሥዕል መምህራን የአጻጻፍ ስልጠና ሊያሰጡ እንደሚችሉም ቃል ገብተውልናል፡፡
የኢትዮጵያ ቋንቋዎች አካዳሚ ባዘጋጀው መዝገበ-ቃላት ላይ ሞክሼ ሆሄያትን እንዳልተጠቀመና አሁን በታተሙት የታች ክፍል ማስተማሪያ መጻሕፍት ላይም ፊደላቱ እንደሌሉ ነግረውናል፡፡ 
ስለ ድርብ ጽሑፍ ጉዳይ የሚመለከታቸው ባለሙያዎች እንዳሉም ከማራኪ ገለጻቸው ተገንዝበናል፡፡
ፍልጹቅ ሆሄያት፣ ማለትም እንደ ‹ጐ› ዓይነቶቹ እየጠፉ ነው፡፡
የአጻጻፍ፣ ብዕር አያያዝ፣ የፊደል አጣጣል ነገር እየተበለሻሸ መጥቷል፡፡ ለዚህም የመጀመሪያ ተጠያቂዎቹ እኛ መምህራን ነን፡፡

ከተሳታፊዎች የተነሡ ሐሳቦችም ነበሩ፡-
ሀ. የአማርኛ ፊደላት ያሏቸው የተለያዩ ዓይነት ፎንቶች ስም አላቸው ወይ?
ለ. ‹ይዋ› የሚለው ድምጽ፣ ለምሳሌ ተቀባይዋ የሚለው ቃል ላይ እንዳለው፣ አንድ ራሱን የቻለ ፊደል አለው ወይ?
ሐ. በዉበታቸው የምናውቃቸው በእጅ ብቻ ሲጻፉ የምናውቃቸው ፊደላት አሁን እየጠፉ ነው፡፡
መ. ሁለት ነጥብ የት ገባች?
ሠ. የመጀመሪያውን የቴሌክስ ጽሑፍ ኢንጂኔር ተፈራ የራስ ወርቅ ካስተዋወቁን በኋላ ብዙ ዓይነት ጽሑፎች መጥተዋል፡፡
ረ. በእጅ ጽሑፍ ጊዜ ከባድ ፊደላትን መጻፍ የሚያስቸግረን ብዙዎች ነን፡፡
ሰ. ፊደላትን ማንበብም የሚያስቸግረው አለ፡፡
ሸ. የዶክተር አምሳሉ አክሊሉ  ‹‹የአማርኛ ፊደላትን ጠንቅቆ ያለመጻፍ ችግርና ዘላቂ መፍትሔ›› እንደሚለው ያሉ መጻሕፍት ለዚህ ችግር ሁነኛ መፍትሐየ ይሆናሉ፡፡
ቀ. ድምጹን የማናውቀው ሞክሼ ፊደል ምን ይሰራልናል?
ተ. ጽሑፍ ሲሞት ቋንቋው ሞተ ይባላል ወይ?

የእጅ ጽሑፍ ተኮር ትዝታዎችና ምልከታዎችም ተቃኝተዋል፡-
አራት ዓይነት ‹ይ› እንዳለ፡፡
በጽሑፋቸው የሚታወቁ ሰዎች እንዳሉና ያልሆነ ነገርም ጽፈው የተገኙ ሰዎች በዚያው ተደርሶባቸው እርምጃ እንደተወሰደባቸው፡፡
የእጅ ጽሑፋችን የራሱ ውበት፣ ስብጥርና ፈጠራም አለው፡፡ ለትውልድ እንዴት ይተላለፍ?
በንግግር ብቻ ሳይሆን በጽሑፍም የእንግሊዝኛ ተጽዕኖ አለብን፡፡ ታች ክፍል ነው አማርኛ ያለው፡፡ ከዚያ በኋላ አማርኛ የምንጽፍበት ዕድል አናሳ ነው፡፡
ስለ ንብረትነቱ ከተነሣ የቋንቋው ባለቤት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ እንደ ምሣሌ ለማንሣት በአሁኑ ሰዓት ደቡብና ጋምቤላ ክልሎች ይጠቀሙበታል፡፡ ስለዚህ በምናደርገው የማሻሻያም ሆነ የአጠቃቀም ጉዳይ ሁሉንም ተጠቃሚ ማነጋገር አለብን፡፡
ከ‹ሀ› ወይስ ከ‹በ› ይጀመር?
ሁለተኛ ቋንቋ አድርገው ለሚናገሩት ወይም ለህጻናት ስለሚከብድ ማሻሻያ ይደረግ፡፡
የሌሉ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ድምጾች እንዲካተቱ የተደረጉ ጥረቶች ነበሩ፡፡
የላቲን ፊደል አጠቃቀም ሳይንሳዊ ነው ወይስ ፖለቲካዊ?
መሠረተ-ትምህርት ብዙ መጠነ-ሰፊ ፊደል-ተኮር ነገሮች የተነሡበት አጋጣሚ ነበር፡፡
ፈረንጆች የእጅ ጽሑፋቸውን ጠብቀው ቆይተዋል፡፡ ከርሲቭ (በተለምዶ ቅጥልጥል ጽሑፍ የሚባለው) ምናልባት የእጅ ጽሑፋቸውን ጠብቆ አቆይቶላቸው ይሆናል፡፡

ሁለት ወይም ሦስት እየሆኑ ስለ ጉዳዩ እንዲነጋሩ የተደረጉት ተሳታፊዎች ብዙ ሃሳቦችን አንስተው ጥለዋል፡፡
ዲቃላ ሆሄያትን (እንደ ‹ቋ› ያሉትን)፣ የ ‹የ›ን ዘሮች፣ የ ‹ኀ›ን ዘሮች መጻፍን ያካተተ መጠነኛ የጥያቄና መልስ ውድድርም ነበር፡፡ በዚህም የነበሩ ክፍተቶች በግልጽ ሊወጡ ችለዋል፡፡

2018 ኤፕሪል 11, ረቡዕ

Privatizing Libraries in Ethiopia: The Case of Ras Abebe Aregay Library, Debre Birhan

This is an upcoming blogpost on the activities our library is undertaking. Please write to me your views and I will address them accordingly. Do you believe that private libraries can be more successful than public ones? My article will be on that. For those of you who are new to the activities we do, this library has been functional for the last two years. We even had a branch which closed after seven months' service owing to the location which readers didn't like. We are running the library using our own funds. Below you see pictures of children reading and writing at our library.
Have a great day!
Mezemir Girma
General Manager
0913658839



2018 ማርች 26, ሰኞ

15 Signs you are an Entrepreneur:


A video lesson I transcribed. (Passion, dedication, optimism). Which ones do you have?

1.       You take action – invent as you go

2.       You’re insecure

3.       You’re crafty – responsible in what you do have

4.       You’re obsessed with cash flow

5.       You get into hot water – never satisfied with the status quo

6.       You’re fearless – will pay off

7.       You can’t sit still

8.       You’re malleable

9.       You enjoy navel gazing

10.   You’re motivated by challenges

11.   You consider yourself an outsider

12.   You recover quickly

13.   You fulfil needs

14.   You surround yourself with advisors

15.   You work and play hard.

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...