2019 ኖቬምበር 2, ቅዳሜ

አንድ ሰሞን በአክራ፣ ጋና



(An Account of My trip to Accra, Ghana, in Amharic)
የጉዞ ማስታወሻ
በመዘምር ግርማ
ጥቅምት 21 2012

‹‹ወደ ምስራቅም ወደ ምዕራብም አናንጋጥጥም፤ ወደ ፊታችን እናያለን እንጂ›› ዶክተር ክዋሜ ንክሩማ




ለጉዞ ዝግጅት የጀመርኩት ክረምት ላይ ነበር፡፡
ፓስፖርቴ የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈበት ስለነበር እሱን ለማሳደስ ከአርብ እስከ ሰኞ አዲስ አበባ ጠብቄ፣ አርብንም ሰኞንም ተሰልፌ ነበር ከሳምንት በኋላ መውሰድ እንደምችል የተረዳሁት፡፡አስቸኳይለተባለው ለዚህ ተግባር 2186 ብር መክፈል ግድ ነበር፡፡ በዋናው ፖስታቤት አዲሱን ፓስፖርት ከሳምንት በኋላ ስወስድ የተከፈለችም 45 ብር አለች፡፡
ከአዲስ አበባው የጋና ኢምባሲ ቪዛ ለማግኘት ድረገጽ ላይ ስልክ ቁጥራቸውን ፈልጌ ደወልኩ፡፡ የሚያስፈልገው ነገር ብዙ ነበር፡፡ የሚከተሉትን ነገሮች እያንዳንዳቸውን ሦስት ያቅርቡ ተባለ፡፡ ፎቶ፣ መታወቂያ፣ ማመልከቻ፣ የፓስፖርት ኮፒ፣ የግብዣ ደብዳቤ፣ ሆቴል የያዙበት፣ የአየር ቲኬት እና የመስሪያ ቤት የትብብር ደብዳቤ፡፡ በሦስት ቀን ውስጥ ቪዛ መተው ሰጡኝ፡፡
ወደ ጋና የምሄደው ረቡዕ 13.2.2012 ሌሊት 930 ቢሆንም ማክሰኞ ጠዋት ከደብረ ብርሃን ተነስቼ ወደ አዲስ አበባ መንገድ ጀመርኩ፡፡ ለዚህም ምክንያቴ የነበረው ወቅታዊው የመንገድ መዘጋጋት ስጋት ነበር፡፡ ቢዘጋጋ እንኳን ቀደም ብዬ ልሂድ ብዬ ነው፡፡ አዲስ አበባ እንደደረስኩ ወደ አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ ዋና መስሪያ ቤት ባምቢስ ሄጄ ለደብረ ብርሃን ቅርንጫፋቸው ባቀረብኩት ማመልከቻ መሰረት 500 ዶላር ወሰድኩ፡፡ ለዚህም ትብብራቸው አመሰግናለሁ፡፡
በዚህ ጉዞ የያዝኩት አንድ በጀርባ የምትታዘል ሻንጣ ስትሆን የያዝኩባትም በብዛት ልብስ ነበር፡፡ ምክንያቱን ልብስ ካልያዙ በውጭ ሃገር መቆየት እንዴት እንደሚከብድ ከአሁን በፊት ስለተማርኩ ነው፡፡ ከዚህ በመቀጠል ወደ ብሔራዊ ቤተመጻሕፍትና ቤተመዛግብት በመሄድ ዋና ኃላፊውን ለማግኘት ቻልኩ፡፡ እየሰራን ስላለነው ስራ መልካም ውይይት አድርገን አመስግኜ ተለያየን፡፡ በዕለቱ በተረፈኝ ጊዜ ደራሲ ጥላሁን ጣሰውን አግኝቼ እንደተለመደው ተጋብዤ ተለያየን፡፡ ደራሲ አጥናፍሰገድ ይልማ ስደውል መኪና እየነዱ ነው ብለው ሌላ ሰው አነጋገሩኝ፡፡ ሌላ ቀን አገኛቸዋለሁ ብዬ ማስታወሻ ያዝኩ፡፡
የማክሰኞ ምሽት አንዳንድ ወጣ ያሉ ነገሮች ነበሩበት፡፡ በመጀመሪያ እስካሁን የበጎ አድራጊ ድርጅት ገንዘብ እንድጠቀም በሚፈቀድልኝ ጊዜ በአነስተኛ ዋጋ አልጋ እየያዝኩ በሙዚቃ ስረበሽና ቻርጀርና መታጠቢያ እንኳን በሌላው ሁኔታ ስቸገር ስለማድር በአሁኑ ጉዞ ይህን ለማስተካከል ወስኛለሁ፡፡ ራት የበላሁት በአይቤክስ ሬስቶራንት ነው፡፡ ማምሸ ላይ ከዚያው ላዳ ለመያዝ አስቤ ሃሳቤን ቀየርኩ፡፡ ጊዜው ከአንድ ሠዓት አልፎ ስለነበርና ድርጅቱም ይከፍልልኝ ስለነበር ትልቅ ስህተት መስራቴ አሁን ነው የገባኝ፡፡ በሃይገር መገናኛ ሄድኩ፡፡ ከመገናኛ ወደ ላምበረት ለመሄድ በደረጃዎቹ ለመውጣት ስሄድ የሰው መጨናነቅ ነበር፡፡ በዚህም ጊዜ የቅሚያ ሙከራ ያደረገብኝ አንድ ሰው ነበር፡፡ ከዚህ የተረዳሁት ሌሎችም ጓደኞች እንደሚኖሩት ስለነበር የፖሊስን እገዛ መጠየቅ ነበረብኝ፡፡ በተዓምር ይህን ችግር አለፍኩት፡፡ ማንራሲዋ ሆቴል ደርሼ 600 ብር ቁርስ የሌለው አልጋ ያዝኩ፡፡ ጥሩ መኝታ ቤት አላቸው፡፡
በዚህ ቀንና ማታ ላይ በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ እንደ ቦሌ አራብሳ ያሉ አካባዎች ላይ በአማርኛ የተጻፉ ማስታወቂያዎችን ማንሳት መጀመሩንና ሰዎችም ላይ ጥቃት እየተፈጸመ እንደሆነ በፌስቡክ አይቼ ነበር፡፡ እኩለ ሌሊት አካባቢ ይመስለኛል በማህበራዊ የትስስር ገጾች የጃዋር መሐመድንየተከበብኩጥሪ አየሁ፡፡ ጠባቂዬ ከኮማንደር ጋር ሲነጋገር ቀረጽኩ ያለውንም አዳመጥኩ፡፡ የሱን መጨረሻ ለማየት ጓጉቼ ስከታተል አደርኩ፡፡ ሌሊቱን ብዙም አልተኛሁም ነበር፡፡ ባለኝ ግንዛቤና ንባብ ሌሊት ላይ ህዝቡ በተኛበት ብዙ አስጊ ነገሮች ስለሚጠነሰሱ የሁኔታውን አካሄድ ማጥናት ነበረብኝ፡፡   
በዕለተ ረቡዕ መጠያየቅ የነበረብኝን ሰዎች ስጠያይቅ ቆየሁ፡፡ በዚህ ዕለት ወደ አዲስ አበባ የሚያስገቡ መንገዶች ሁሉ ዝግ ነበሩ፡፡ የዘጉትም በጃዋር መሐመድ ላይ ተደረገ የተባለውን የጠባቂዎች ማንሳት ሂደት ተቃወሙ የተባሉ ወጣቶች ናቸው፡፡ በከተማውና በአካባቢ አስጊ ሁኔታ ነበር፡፡ ሌሊትና ጠዋት አካባቢ ድረስ እውነትም ጠባቂዎቹ ሊነሱበት ተደርጎ ይሆናል የሚል ግምት ነበረ፡፡ እየቆየ ሲሄድ ግን ነገሩ ሌላ መልክ እንዳለው ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ ረቡዕ አመሻሽ ላይ ወደ ቦሌ አየር ማረፊያ ሄድኩ፡፡ በዋዜማው ምሽት ላይ የደረሰብኝ የቅሚያ ሙከራ በዚያ ቀን እንድጠነቀቅ አድርጎኛል፡፡ የረብሻ ስጋትም አለ፡፡ ይሁን እንጂ 1200 እስከ ሌሊት 930 መጠበቅ እንዴት አሰልቺ እንደሆነ ልትገነዘቡልት ትችላላችሁ፡፡
ረጅሙን ታሪክ ለማሳጠር ሌሊት 930 በኬኒያ ኤርዌይስ አውሮፕላን ተሳፍሬ ወደ ናይሮቢ ጉዞ ጀመርኩ፡፡ ከአዲስ አበባ ናይሮቢ ሁለት ሰዓት የሚፈጅ አልመሰለኝም ነበር፡፡ ግን ፈጀ፡፡ ኬኒያም ትራንዚት ሳደርግ የኬኒያ ሻይ በወተት ጠጣሁ፡፡ ውኃም ያዝኩ፡፡ የአውሮፕላን ውስጥ መስተንግዶውና ድግሱ እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ትልቅ አልነበረም፡፡
በኬኒያ የሄድኩት የምሄድበት ስብሰባ አስተባባሪዎች በቆረጡልኝ ትኬት መሰረት ነው፡፡ ባይሆን ኖሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቀጥታ አክራ ድረስ በረራ ስላለው በሱ መጓዝ እችል ነበር፡፡ ከሁለት ሰዓታት ረፍት በኋላ ወደ አክራ በሌላ የኬኒያ አውሮፕላን ጉዞ ጀመርኩ፡፡ ማክሰኞ ሌሊት በደንብ አለመተኛቴ፣ ረቡዕ ሌሊትም አየር ማረፊያ ግቢ ሳልተኛ ማደሬ የራሱ የሆነ ጫና አለው፡፡ አሁን የምሄድበት አክራ ደግሞ ከኛ ሦስት ሰዓት ስለሚቀድም ቀን እየሆነ ነው የሚሄደው፡፡ ጀት ላግ የሚባለው ነገር ገጥሞኛል፡፡ ከናይሮቢ አክራ ለመድረስ አምስት ሰዓት ተኩል ወስዶብናል፡፡ አክራ ኮቶካ አውሮፕላን ማረፊያ አዲስ መሰራቱ ነው፡፡ በዩቱብ አይቼው ስለነበር አዲስ አልሆነብኝም፡፡ የተለመደችው የኢሚግሬሽን ባለስልጣኖች የጉቦ ጥያቄ ነበረች፡፡ በልምምጥና በዘዴ አልፌያታለሁ፡፡ በአየር ማረፊያው የሆቴሉ ታክሲ ይጠብቀኝ ስለነበር አግኝቸው ይዞኝ ወደ ሆቴሉ ሄደ፡፡ ከተማዋን እየቃኘሁ ኢራታ ሆቴል ገባሁና ቦታዬን ያዝኩ፡፡ የሆቴሉ ብዙዎቹ ነገሮች የአዲስ አበባውን ማንራሲዋ ሆቴል ስለሚመስልና ካሁን በፊትም ካየኋቸው ሆቴሎች ጋር ስለሚቀራረብ አላስቸገረኝም፡፡ ለነገሩ አስተናጋጇ በደንብ አሳይታኛለች፡፡
በዚሁ ዕለት የፕሮጀክታችን አስተባባሪ ጋናዊው ስታንሊ ሆቴል መጥቶ አግኝቶኛል፡፡ የማላዊ ብሔራዊ ቤተመጻሕፍት ኃላፊ የሆነው ግሬይ ኒያሊንም በእራት ሰዓት አግኝቸዋለሁ፡፡ የሆቴሉ ምቾት ጥሩ የሚባል ነው፡፡ በማግስቱ ጠዋት ምን እንደምንሰራ በማሰብ ላይ ሳለሁ ለአስተባባሪዎች ስብሰባ የመጣውን ስታንሊን አግኝቼ ጠየቅሁት፡፡ የሆቴሉን ሰዎች አነጋግሮ እነሱ የሚያውቁት የታክሲ ሾፌር አስመጣልን፡፡ እኔና ግሬይ በጋራ 45 ዶላር እንደምንከፍል ተነጋግረን ጉዟችንን ቀጠልን፡፡ የዕለቱ ሽርሽር በመንገድ መዘጋጋት ትንሽ የዘገየ ቢሆንም ደህና ጀምሯል፡፡ በመንገዳችን ላይ ቤተመንግሥታቸውን፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱንና የጋና መስራች የሚባሉትን የአሻንቲ ህዝቦች ሰፈርን አየን፡፡ መንገድ መንገዱን ፎቶ ሳነሳና የህዝቡን አኗኗር እያየሁ ከሹፌሩና ከግሬይ ጋር ሳወጋ ነበር፡፡   

የውቅያኖስ ዳርቻ
የባሪያ ንግድ 1673 ነበር አሉ የጀመረው፡፡ ከዚህ ጋር የሚያያዝ ቦታ ልናይ ነው፡፡ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ዳርቻ አቀናን፡፡ በስፍራው አንድ ወጣት አግኝተን የማስገብኘት ስራውን ጀመረልን፡፡ ይህ የውቅያኖስ ዳርቻ ጀምስ ታውን ይባላል፡፡ እዚያ አንዲት ቀይ የተቀባች በግምት አስር ሜትር የምትረዝም ማማ አለች፡፡ የብርሃን ቤት ትባላለች፡፡ እሷን ከውጭ ጎበኘን፡፡ እንዳንገባ እድሳት ላይ ስለሆነች ነው፡፡ 1871 የተሰራች ስለሆነች እድሳቱ ግድ የሚላት ይመስላል፡፡ 1930 ባትታደስማ ወድቃ ነበር፡፡ መርከቦች ከሩቅ ሲመጡ ብርሃን እንዲያዩባት የምትደረግ ክፍል ነች፡፡ ከእርሷ ጎን የጋና የመጀመሪያው ፕሬዚዳንት ለአንድ ዓመት የታሰሩበት ታሪካዊ ቤት አለ፡፡ በዚህ አክራ እድሜጠገብ ክፍል ዓሳ ማጥመድ ዋነኛ የስራ ዘርፍ ነው፡፡ ልጆች በዘጠኝ ዓመታቸው ሳይቀር ዓሳ ያጠምዳሉ ተብለናል፡፡ በመንግስት የመልሶ ማልማት ስራ ምክንያት በአካባቢው ያለው መንደር ፈርሷል፡፡ ፈርሶ ለአንድ ዓመት ያህል ምንም ስላልተሰራበትም ህዝቡ መልሶ ሸራም ምንም እየጣለ ሰፍሯል፡፡ በወደቡ ድህነት እንዳለ አስጎብኛችን ነገረን፡፡ ዘጠኝ ቤትር የሚረዝሙ አከንድ ወጥ እንጨት በባህላዊ መንገድ የተሰሩ ጀልባዎችን አየን፡፡ ግማሹ ዓሳ ይፍቃል፣ ይበልታል፤ ግማሹ ቀንድ አውጣ ያጥባል፡፡ የውቅያኖሱን ዳርቻ አየን፡፡ መርከብና ጀልባወችንም በውቅያኖሱ ለማየት ችለናል፡፡ ለበርካታ ቀናት ዓሳ ለማስገር ሲወጡ በዚያው ሞተው የሚቀሩም እንዳሉ ተረዳን፡፡ ለአስጎብኛችን 20 የጋና ሴዲ (አራት የአሜሪካን ዶላር) ሰጥተን ተሰናበትን፡፡

የንክሩማህ ሙዞሊየም
ቀጣይ መዳረሻችን የዶክተር ክዋሜ ንክሩማህ ሙዞሊየም ነው፡፡ የመጀመሪያው የነጻይቱ ጋና ፕሬዚዳንት የነበሩትን የክዋሜ ንክሩማህን ሙዞሊየም ስንጎበኝ በህይወት ዘመናቸው የተጠቀሙባቸውን ቁሳቁስ፣ የጻፏቸውን መጻሕፍት፣ ከተለያዩ የዓለም መሪዎች ጋር ተነሷቸውን ፎቶዎችና የመሳሰሉትን አይተናል፡፡ በልጅነቱ ሴት አያቱ የሰጡት ከሴሴ እንጨት የተሰራ ወንበር (ግርምቡድ) አይተናል፡፡ ቤተመንግስት ላይ ይጠቀሙበት የነበረው ጠረጴዛ ከነ ወንበሩም አለ፡፡ ትልቅ ፒያኖም እንዲሁ፡፡
የደረቀ አስከሬናቸው ያለበትን መቃብር ቤት ከሙዞሊየሙ ፊት ለፊት አለ፡፡ እሱንም አይተናል፡፡ ጋናውያን ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከመምህራን ጋር ሆነው ስፍራውን እየጎበኙ ገለጻ ሲደረግላቸውም አይተናል፡፡ ቀጣዩን ትውልድ ማነጽ ማለት ይህ ነው፡፡ ህጻናቱም እንግሊዝኛ ይችላሉ፡፡ ከቋንቋቸው በተጨማሪ መሆኑ ነው፡፡ ከነዚህ ስፍራዎች ፊት ለፊት ያለው የውሃ ገንዳ የሙዚቃ መሳሪያ በሚጫወቱ በርካታ ሀውልቶች አጊጧል፡፡ ከዚያ ፊት ለፊት ያለው ለምለም ሻር ጌፀ ሜዳ አእምሮን ያሸፍታል፡፡  
የንክሩማህን ህይወት ታሪክ ፈልጋችሁ እንድታነቡ እጋብዛችኋለሁ፡፡ አዲስ አበባ ሲመጣ በነጠላ ጫማና በሽርጥ መምጣቱን ሳትሰሙ አትቀሩም፡፡ ማንነቱን አስበልጦ ነው፡፡ ንክሩማይዝም የሚባል እንቅስቃሴ እንዳለ አንብቤያለሁ፡፡ በርካታ መጻሕፍትን እንደደረሰም አይቻለሁ፡፡ ‹‹ወደ ምስራቅም ወደ ምዕራብም አናንጋጥጥም፤ ወደ ፊታችን እንጂ›› የሚለው ዶክተር ክዋሜ ንክሩማ ከቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጋር የስልጣን ሽኩቻ እንደነበራቸው አንብቤያለሁ፡፡ በመፈንቅለ መንግስት የተገረሰሰው የንክሩማህ መንግስት ሲወድቅ ንክሩማህ የጊኒ አጋር ፕሬዚዳንት ለመሆን ቻለ፡፡ በመጨረሻም በህመም ምክንያት ህይወቱ ስታልፍ በጊኒ 1972 ተቀበረ፡፡
ከዚህ ቦታ ወጥተን የባህል ዕቃዎች ወደሚሸጡበት ስፍራ ሄደን የተለያዩ ልብሶችንና የስጦታ ዕቃዎችን ሸመትን፡፡ ለማሳረጊያም ወደ አንድ የውቅያኖስ ዳርቻ መናፈሻ ዘልቀን ውቅያኖሱን በቅርበት አየን፡፡ ለማስዋሻም ፎቶ ተነሳን፡፡
ወደ ሆቴላችን ተመልሰን ከየሃገሩ የሚመጡትን ተሰብሳቢዎች ስንተዋወቅ አመሸን፡፡
በማግስቱ ቅዳሜም ስብሰባችን ጀመረ፡፡ ስብሰባችን ምን እንደሚመስል ከመግለጼ በፊት ስለ ፕሮጀክቱ አንዳንድ ነገር እንነጋገር፡፡ የአፍሪካ ቤተመጻሕፍት ማህበር ከዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ ጋር የሚያካሂዱት ይህ ፕሮጀክት በቢልና ሚሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ስፖንሰር የተደረገ ነው፡፡ የአብያተ መጻሕፍትን እይታ መጨመር (Advancing Library Visibility in Africa) ይባላል፡፡ አብያተ መጻሕፍትን በያሉበት እየተገኙ የሚመዘገብበት ሂደት ነው፡፡ በመጀመሪያ ያሉበትን ቦታ፣ የቤተመጻሕፍት ሰራተኛውን አድራሻ መሳሰሉትን ከመዘገብን በኋላ በቀጣይ ዙር ደግሞ የሚሰጡትን አገልግሎት እንደያይነቱ እንመዘግባለን፡፡ የዚህ ሁሉ የድረገጽ ምዝገባ ዓላማ የልማት አጋሮች የሆኑ ድርጅቶች አብያተመጻሕፍትን እንዲያግዙ መንገድ መጥረግና ክፍተቱን ማሳየት ነው፡፡ ሌሎችም ጥቅሞች አሉት፡፡ ዝርዝሩን librarysites.io ብላችሁ በመግባት ታገኙታላችሁ፡፡ በአቅራቢያችሁ ያለውን የህዝብ ቤተመጻሕፍት እንድትመዘግቡ ተጋብዛችኋል፡፡
ስብሰባችን ስራችንን የምንገመግምበትና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የምናስቀምጥበት ነው፡፡ እንግሊዝኛ፣ ፈረንሳይኛና ፖርቹጋልኛ የምንናገር አፍሪካውያን እንደየቋንቋው በቡድን ሆነን በአንድ አዳራሽ ስንሰበሰብ የማስተርጎሙን ስራ እንዲሰሩ የመጡት ስድስት ባለሙያዎች በአንድ ጥግ በተዘጋጀላቸው ቦታ ሆነው ያስተረጉማሉ፡፡ ተሳታፊው የጆሮ ማዳመጫውን ሰክቶና የሚመቸውን ቋንቋ መርጦ ይሰማል፡፡ ቅዳሜና እሁድ ሪፖርቶቻችንን ስናቀርብ፣ የቡድን ስራ እየሰራን ስንወያይና መድረክም ላይ ስናቀርብ፣ የአዘጋጆቹንም ገለጻዎች ስንከታተል ቆይተን ሰኞ ወደ ሁለት አብያተመጻሕፍት የጉብኝት መርሃግብር ነበረን፡፡ ወደ ጋና መምህራን ኮሌጅ ማህበረሰብ ቤተመጻሕፍትና ወደ ችርስ የግል የህጻናት ቤተመጻሕፍት፡፡ ብዙ የተማርንበት ጉብኝት ነበር፡፡ 
ማክሰኞ ብዙው ሰው ወደ ሃገሩ ሄዶ ወይም ወደ ሌላኛው የብሔራዊ ቤተመጻሕፍትና ሚኒስትሮች ስብሰባ ገብቶ ስለነበር እኔ በሆቴሉ ብቻዬን ማለት በሚቻል ሁኔታ ነበርኩ፡፡ በረራዬ ማታ ነበር፡፡ በዚህም ጊዜ ማታ እንደምሄድ የተረዱ የሆቴል አስተናጋጆች ዛሬ ምሳ አትበላም አሉኝ፡፡ ሞባይልክን ስጠኝ ያለኝም ነበር፡፡ ስቄ አለፍኩት፡፡ ምሳ ሰዓት ላይ የሌሴቶዋ በጎ ፈቃደኛና ተሰብሳቢ ስትመጣ ምሳችንን በልተን መፈረሚያውን አምጡ ብላ ስታፋጥጣቸው አስፈረሙን፡፡ እኔንም 40 ሴዲስ ትከፍላለህ ብሎ ላቀረበልኝ ምሳ ሳያስከፍለኝ ቀረ፡፡ እግሬ ሆቴሉን ከረገጠባት እስከምወጣባት ጊዜ እንደሚከፈልልኝ እየታወቀ ይህ ውንብድና ከአስተናጋጁ አይጠበቅም ነበር፡፡
ወደ አየር ማረፊያው ስሄድ አብሮኝ የሄደው የኒውዮክ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ ፕሮፌሰር ነው፡፡ አድራሻውን ይዣለሁ፡፡ የአፍሪካ ጥናት ማህበርን ያስተባብራል፡፡
 አዲስ አበባ ተመልሼ የጋናውን የአስተርጓሚ ድርጅት ግማሽ ባለቤትና ጋና ያገኘሁት ሰው መንትያ ወንድም የሆነውን ኮፊ ኮራንተንን ደውዬ አገኘሁት፡፡ በራስ ሆቴልም አወጋን፡፡ በአፍሪካ ህብረት እንግሊሊኛና ፈረንሳይኛ በማስተርጎም አስር ዓመት ሰርቷል፡፡ ‹‹ንክሩማህ ይመስገን አገራችን ሰላም ነች፡፡ ሁሉም አሁን ያለን ነገር እሱ የጣለው መሰረት ውጤት ነው፡፡ አእምሮን ለማልማት እንሰራን ፡፡ የኢትዮጵያ መሪዎች የሰው ኃይሉን አገር ውስጥ ለማቆየት ነው አሉ እንግሊዝኛ በጥራት እንዳይማር የሚያደርጉት፡፡ ዓለምአቀፍ ድርጅት ለመግባት፣ እድገትን ለማምጣትና ውጭ ለመማር እንግሊዝኛንና የውጭ ፈተናዎችን አሰራር ለልጆቻችን ማስጠናት አለብን፡፡ ስዋህሊ፣ ትዊና አማርኛ ያለነሱ ያሉባቸውን አገሮች ማሰብ አይቻልም፡፡ ጋና፣ ምስራቅ አፍሪካና ኢትዮጵያ በእነዚህ ቋንቋዎች ስለሆነ ህልውናቸው የተረጋገጠው እንዲበለጽጉ መስራት አለብን፡፡›› የሚሉትንና ሌሎችንም ሃሳቦች ኮፊ አካፍሎኛል፡፡ ወደፊትም እንደምንገናኝ ቃል ገብቶልኛል፡፡
የበፊቱን ሚት ኢቲቪ የአሁኑን ሚት ኢቢሲን አዘጋጅ ተፈራ ገዳሙንም እንዲሁ ብሔራዊ በሚገኘው ቢሮው አግኝቼ ቀድሞ ስለነበረን ቀጠሮ ጉዳይ አነጋግሬዋለሁ፡፡

ምልከታ
የመንገድ ላይ ሻጮች በርካታ ናቸው፡፡ የሚያሳድዳቸውም የለም፡፡ እንዲያውም ይበረታታሉ፡፡ ራሳቸው ላይ የተሸከሙ መነገድ ብቻ ነው፡፡
ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ጋና አጥር የለውም፡፡ ህብረተሰቡም በውስጡ በእግርም ሆነ በመኪና አቋርጦ ያልፋል፡፡ ስለ ጉዳዩ የጠየኩት አንድ ተማሪ ‹‹መልካሙን ስለምንጠብቅ አጥር አያስፈልገውም፡›› ብሎኛል፡፡ እኛ አገር በአንጻሩ ጠቀም ያለ በጀት ለአጥርና ለዋና በር ይያዛል፡፡ እርስዎ የትኛው የሚሻል ይመስልዎታል? ሰዎቹ ከቺንዋ አቸቤ ልብወለድ Dead Men’s Path የተማሩ ይመስላሉ፡፡
ሆቴል መኝታ ቤት ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስ ይቀመጣል፡፡ ስብሰባ በጸሎት የሚጀመርበት ጊዜም እንዳለ ሰምቻለሁ፡፡
የኢትዮጵያውያን ሴቶችን ውበት የማያነሳ የለም፡፡ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሄዱና ቦሌ አየር ማረፊያን ደጋግመው የረገጡ በርካቶችን አግኝቻለሁ - ከጋናውያንም ሆነ ከሌሎቹ አፍሪካውያን!
ሰው ሁሉ ሲያየኝ ኢትዮጵያ ይለኛል፡፡ ይህ በመልክ የመለየት ነገር ግን ለክፉ ቀንም ያሰጋል የሚል ነገር ታይቶኛል፡፡
‹‹ኢትዮጵያውያን እንግሊዝኛ ያስቸግራቸዋል፡፡ አንተ ግን እንዴት ቻልክ?›› ያለችኝ በጎ ፈቃደኛ ነበረች፡፡ በትምህርት ጥራት ማነስ መታወቃችን አሳስቦኛል፡፡
ማላዊያዊው ግሬይ ኒያሊ ደግሞ ኢትዮጵያ ለስብሰባ አምስት ጊዜ እንደመጣ ነግሮኛል፡፡ 9/11 ጊዜ አሜሪካ ነበርኩ ብሏል፡፡ በእንግሊዙ ባኪንግሃም ፓላስም ልዑሉን የማግኘት ዕድል ነበረው፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመንግስት ለውጥ ጊዜ እንዳይጎዳ ያሰቡ አርቆ አሳቢ አመራሮቹ በጊዜያዊነት ወደ ሌላ አገር አዛውረውት ነበርም ብሎኛል፡፡ 
ዱንስታኔት በምትባል በጎ ፈቃደኛ የተወከለችው ሴራሊዮን አየር መንገድ የላትም፡፡ ዱንስታኔት የልጆች ቤተመጻሕፍት ሰራተኛ ስትሆን ወደ አክራ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ እንደሄድን ለሞዴል ትምህርት ቤቱ ህጻናት መዝሙር አስጠንታቸዋለች፡፡ ሁለት ምርጥ ቃላት አሉ - አመሰግናለሁና እባክዎን የሚሉ፡፡ የሚል መዝሙር ነው፡፡ ዱንስታኔትን እንግሊዝኛ መምህርነት እናንተ አገር ልሞክር ወይ ስላት በአገሯ ስራ ፈላጊው ብዙ መሆኑን ነገረችኝ፡፡ 
‹‹ሌሴቶ የባህር በር የሌላት በደቡብ አፍሪካ የምትዋሰን ሃገር ነች፡፡›› ከዚያቸች ሃገር የመጣች የቤተመጻሕፍት ሰራተኛ አገሯን የገለጸችበት መንገድ፡፡
ሚኪያስ ካሳዬ ‹‹አትላንቲክ ድረስ ሄደህ ውቅያኖስ ላይ ሳትንቦጫረቅ መምጣት አልነበረብህም!›› ብሎኛል፡፡ ልክ ነው፡፡ ለጉዞው ካደረኩት ዝግጅትና በቦታው ምን ዓይነት መዝናኛ ቦታዎች እንዳሉ ካለማወቅ ነው እንጂ ባደርግ ጥሩ ነበር፡፡ 
ግሬይ በፊት የተመረቀው በግብርና ነበር፡፡ በኋላ የግብርና መረጃዎችን በመከታተል ስም ነው ወደ ቤተመጻሕፍት የገባውና በዚያው የቀረው፡፡
በመንገድ ዳር ምግብ የሸጣል፡፡ ዓሳ፣ ፍራፍሬ ወዘተ፡፡
‹‹ለምን መረጃ ትሸጣለህ›› የደቡብ አፍሪካዋ የቤተመጻሕፍት ሳይንስ መምህርት ለኔ ያለችኝ ነው፡፡ ቤተመጻሕፍታችን መጻሕፍትን እንደሚሸጥ ስነግራት ነው እንዲህ ያለችው፡፡
‹‹ኢምፔሪያሊዝም እንድንማርና ስራ እንድንጠላ ያደርገናል፡፡ ዲግሪ ይዘህ ያለ ስራ ትዞራለህ፡፡ ኢምፔሪያሊዝም የእድሜ ልክ ቅኝ ግዛት ነው፡፡›› የአብያተመጻሕፍት ሰራተኞች ሲያወሩ የሰማሁት ነው፡፡ ትክክለኛ ሃሳብ ይመስላል፡፡
አንቶኔታ የዝንባብዌ ቤተመጻሕፍት ተወካይ ናት፡፡ ከንዴቤሌ ጎሳ የመጣች ናት፡፡ በዘመነ ሙጋቤ ፍጅት የተካሄደባቸውን የንዴቤሌን ህዝቦች ብርቱ ተዋጊዎች ናቸው ትላለች፡፡ ፍጅቱን የፈጸመብን አሁን ስልጣን ላይ ያለው ሰውዬ ነው ብላኛለች፡፡ ስለ ኮለኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምም የምትለው አላት፡፡ ‹‹መንግሥቱ የመጡ ሰሞን አንድ ኢትዮጵያዊ ስዋዚላንድ አየር ማረፊያ አግኝቶኝ ‹እናንተ አምባገነን የደበቃችሁ› አለኝ፡፡ የምን አምባገነን እንደሆነ ስጠይቀው ‹ሳታውቂው ቀርተሽ ነው!› አለኝ፡፡ በንግግሬ እንደለየኝ ሲናገር ነበር፡፡ ይህ ሰው ጭራሽ እንደ ጠላት ነው ያየኝ›› ብላለች፡፡
የስዋዚላንድ በጎፈቃደኛዋ ደግሞ አገሯ ስሟን እንደቀየረች ነግራናለች፡፡ ይህን የቅኝ ግዛት ስም ወደ ኢስዋስቲኒ ቀይረዋል፡፡
የቆዳ ቀለሜ ከቀን ወደ ቀን እየጠቆረ ሲመጣ ‹‹ለካ እነ ስታንሊ ወደው አይደለም የጠቆሩት!›› አልኩ፡፡ እዚያ ያለውን ጋናዊ አስተባባሪያችንን ጥቁረት አይቼ ነው፡፡

2019 ኦክቶበር 18, ዓርብ

KARAA DU'AALEYYII


Asoosama gabaabaa

Baresaa – Chinua Achebe

Hiikaan - Odaa Waaqoo

Yunivarsitii Dabra Birhanirraa

Abbaltii barnoota - African Literature

Fedhiiwwan mikaa'eli oobi hanga inni yaadee oli milkaa'eef tureera. Innis Amajjii 1949 dura bu'aa mana barumsa giddu-galeessa Nidumee ta'e muudame. Manni barumsichaa yeroo hedduuf boodatti hafee waan tureef ergamooti amantaa abbootii aangoo dargaggoof nama humna haaraa akka manicha hogganuuf itti ergan. Oobi itti gaafatamummaa kana gammachuun fudhate. Yaadota gaggaari hedduu waan qabuuf carraan kun yaadota isaa hojjitti hiikuuf isa fayyade ture. Mana barumsaa sadarka 2ff sirna barsiisota amantaa jala kan ture jalaa baase maqaa "Barsiisa gaarii" jedhamu iddo hojii isaatti mana barumsichaarra argatee ture. Namoota gurguddoof baay'ee kan hin baratin ilaacha isaani dhiphaa sana baay'ee morma ture.
"Itti fayyadamuu qabna, mitii?" jedhee haadha mana isaa ishee dargaggeettii oduu gammadaa kan guddachuu isaa yeroo jalqabaaf akka dhaga'ani gaafate.
 "Wantaa caale hunda ni goona" jettee deebisteef. "Lafa qonnaa gaarii sana ni arganna,akkasumas wanti hundi ammayyaawaaf kan nama hawwatu ta'u..." Turti waggaa lama gaa'ilummaa isaan, "Tooftaa ammayyaawaan" jaalala qabuuf.. "Ogummaa barnoota kan yeroon darbeef moofaa keessa kan jiraniif daldaltoota magaalaa Oneeshaa ta'anii yo ramadaman warraa isaan woyyuufi" Baay'ee jaallattamtuuf ofi taasiste. Mataa ofii hadha manaa dargaggeettii kan hogganaa mana barumsicha fi akka mootitti mana barumsa ofi taasisuu jalqabde.
Mana isheetti haadha mana barsiisota kaawwaani bakka ishee narra hinaafu.Waan hundaan kan dursite taati... Kana booda akka tasaa haadhotiin manaa kan biroo hin jiraatan yaada jedhuun caalma isheef jira. Abdiif sodaa gidduu teesse abbaa mana ofi sodaan laalaa gaafatte.
"Hojjattooni keenya hundi dargaggoof kan hin fuudhinidha" Isheen jedhee wanta isheen hin yaadin miira gammachuutin. "Wanti gaariin nuufi ta'e jechuudha. Jedhee itti fufe.
"Maalif"
"Maalif" Yeroof humna isaan guutuu mana barumsichaati ni kennu."
Nansiin cal'isiiste yokaan yellaasiche. Daqiiqa xiqqaaf waa'ee mana haaraa sanaa shakkite. Garuu shakkiin kun daqiiqota xiqqaa qofaaf ture. Carraan xiqqaan dhuunfaa ishe kan hojii dhabuu kun gammachuu fulduraa gudda kan abbaa mana ishee sana itti dukkaneessu hin qabu. Akka abbaan manaa ishee teessumarratti qaana'ee hafe argite. Hidhi isaa gombifamaaf kan cabu fakkaate ture. Ta'us darbee darbee akka tasaa sochi humna qaamaa kan inni agarsiisuun namooti ni dinqisiifatu turan. Kan amma garuu ijaarsi qaama isa immoo ijaa isa kan boboolla'ee sana waliin awwaalame fakkaata. Ijaa isaatif humna cimaa dhokatee kenneera. Woggaa digdami jaha isaa ta'us namoota isa arganiif garuu soddoma yokaan achii oli fakkaata. Akka woli galaattuu yeroo laallamu jibbisiisa hin turre.
"Waa'ee maali yaadaa jirta mayiki?" jette Nansiin kitaaba shamarraan kan yeroo muraasa dura dubbisaa turte fakkeessuun.
"Manni barumsa akkamitti akka hogganamu namoota sanatti agarsiisuuf gara dhumaatti carraa akkam guddaa akka arganne yaadaa ture." isheen jedhe. Dhuguma manni barumsa Nidummeen boodatti hafaa ture. Obboo Oobi jireenya isaa guutuu hojii oolchee ture. Haadha manas akkasuma. Innis kaayyoo lama qaba ture.
Mana barumsa sadarkaa gaarii qabu dirqamatti gara bareedinnaati fiduutu isarra ture. Fedhiin Naansi kan ture iddo qonna roobni yeroon dhufuun lub-qabeessa rooba harkisu ta'an marganis. Biqiloota babbareedoo didiimaa ifaaf, keelloon kan tooraan itti dhaabaman mooraa mana barumsa kunuunsa cimaa qabu bosona keessa baasan.
Galgala tokko osoo Oobi hojii isaa dinqisiisaa jiruu jaartiin tokko suutaa deemaa toora biqiltoonni didiimoof kekeellonni itti dhaabaman sana miillaan irra dhaabbachaa qaxxaamurtu arguun miirri salphinna itti dhaga'ame. Karaa jaartittiin qaxxaamurte deemee yo laalu badas tajaajila kan hin kennine daandi bosona xiqqaa tokkorra gara kaan geessitu daandii badde takka arge.
"Ollaan daandii miillaa kana akka deeman eeyyamuun na dinqa"jedhe Oobi barsiisa waggaa sadiif mana barumsicha keessa waliin turanin mataa ofi raasaa.
"Daandichi"jedhe barsiisichi miira dhiifamaatin.
"Isaaniif baay'ee barbaachisaa fakkaata." Baay'ee yo itti fayyadamuu dhabanis bakka ollichi itti waaqessaniif iddoo awwaalchaa walqunnamsiisa." jedhe barsiisichi. Eeganaa kun mana barumsaatin maaltu walitti fida? "jedhee hoogganicha gaafate. "Hayi isamma ani hin beeku "jedhee maaltu na galche miira jedhuun barsiisichi gateetti isa sochoose deebiseef. "Garuu yeroo muraasa dura karicha cufiisaaf yaalle waldhabdeen waldhabdeen guddaan uumamuu isaa ni yaadadha"jedhe.
"Sun yeroo muraasa dura amma garuu eennulle itti fayyadamuu hin danda'u" jedhe Oobi deeme. "Hogganaan biiroo barnoota oso torbee dhuftu mana barumsa gulaalu dhufe maal yaada?" Ani akka naa galutti, olloonni sirnaan woqti kana daree barnoota waaqeeffannaa duudha isaanitti itti fayyadamna jedhani murteessuu dandada'u.
Daandi mana barumsa deemaniif galanin sana mukichi dhaabbame. Shiboo qoree qabduun jaarame.
 Guyyaa sadiin booda Abbaan amanta ollichaa kan Anii jedhamu tokko dura bu'aa mana barumsa dubbisa jedhaa dhufan. Innis jaarsa gugguufee deemuudha. Marii isaan giddutti yeroo wanti haaraan dubbatame mormuuf ulee sanaan lafa rurukutaa dhufani.
"Dhaga'eera" jedhan ergaa nagaa gaafata booda Daandiin abbootii keenyaa yeroo gabaaba keessatti cufamuu dhaga'eera jedhan.
"Eeyyeen" jedhe deebiseef obbo Oobi.
"Eenyulle mooraa mana barumsa keenya akka daandi godhu hin eeyyamnu". "Ilaa mucaa koo" daandiin kun si'is ta'e abbaan ke oso hin dhalatin ture" jedhe abbaan amantaa naannicha ulee ofin lafa tututumacha. Jireenyi Ollichas kan dhaabbate isarratti. Firoota keenya kan du'an daandi kanaanidha kan nu gaggeesan. Akkasumas Akaakayyooni keenyas oso hin hafin dhufaa kan nu ilaalanuun achiniidha. Hunda caalaa garuu dhalachuuf daa'imaan daandi faana dhufaniidha.
Obboo Oobi miira quufaa tokko agarsiisaa dhaggeefate. "Kaayyoon wali gala kan mana barumsa Amantaa akkanaa dhabamsiisudha" jedhe dhumarra. Namoota du'aniif daandi miillaa hin barbaachisu. Yaadichi walumagalatti waan hin taaneedha. Kaayyoon keenya ijoolleen keessan yaada akkanaa Akka itti kolfan barsiisudha.
"Wanti ati jettu dhugaa ta'uu danda'a." jedhan lubichi duudha. "Nuyi garuu Amantaa abbooti keenyaati kan nuyi hordofnu" Daandi yo nuuf bante wanti walnudhabsiisu hin jiru." Ani yeroo hundumaa kanaan jedhu, "Allaatinis Cululleenis haa jiraattudha." Lubichi deemuuf ka'e.
"Naan gadda" jedhe barsiisa dura bu'a dargaggeessi. "Garuu manni barumsa daandi darbiinsa hin ta'u." Seera keenya wajjiin hin deemu. Daandi bira mana barumsa keenya oso hin tuqin oso baastani gaarii natti fakkaata. Daandicha baasuuf nuyis ijoollee keenya isini kennuu dandeenya. "Abboti keessan kan duri daandiin jijjiiramuun baay'ee isaan rakkisa jedhe hin yaadu."
"Kan jedhu wanta bira hin qabu" jedhan Lubni ala ta'ani. Guyyoota lama booda ollicha keessa dubartiin dargaggeettin tokko sababa de'aatin duute. Yeruma sana beekaa tokko gaafannaan jaaramuu dallaatin Abbooti durii arrabsuun aarsaa guddaa akka barbaachisu dubbatan.
Ganama yeroo Oobi hiriiba ka'u wanti inni hojjate hundi diigameeruun arge. Toorri biqiltooti irra dhaabamanis badeera. Kunis karaa walfalmaa turanin sana qofa oso hin taane hunda dallicha ture. Biqiltootas miillan irra dhadhabatani balleesaniiru. Gamoo mana barumsa keessa tokko diigameera... Guyyaa san to'atan mana barumsa nama Adi kan ta'e tokko mana barumsa guulaalisa dhufe waa'ee mana barumsa diigamurratti yaadannoo hamaa qaama oli aanoof aanoof barreesse. Keesumattuu, akka dura bu'aan mana barumsa haaraan dogoggoreetti,mana barumsaatif Olloota giddutti waraanni sanyumma akka jiru fakkeesseti kan inni barreesse.
YAADAAF: odawako3@gmail.com, Facebook Oda Wako.





2019 ሴፕቴምበር 2, ሰኞ

A Reading Solution from Ethiopia – Part I


Debre Birhan, a two-hour drive from Addis Ababa, Ethiopia’s capital, is chilly year round. Liqour may come to people’s mind as they hear the name of the town. Most people would ask for it when we, the residents, go to other places. It is also a treat you should expect if you show up here. Recently, the opening of a university, colleges, factories and the population increase is changing the state of affairs in town. People are coming to work in the factories and other newly-opened places of work. The people from the districts around Debre Birhan also consider living in it as a lifelong achievement.
As a teacher living and working in this city administration, I thought I should address a need the increasing population demands. Demands? Yes! Even if they do not demand I shall make them demand it! They should feel hungry and thirsty of it. This need is none other than reading. How I addressed it shall be revealed to you down below.
It was in 2016 that I learned how the population was deprived of the opportunities to read and discover what the writing world thinks about. My own family members were the ones who needed the reading materials the most. As I walked in one of the outskirts of Debre Birhan, I saw one room vacant. I rushed to the guys next to that room and found out that the room was for rent. I paid on the spot and started to give a bookstore and library service.

Ras Abebe Aregay Library
 It is now a three-and-a-half year’s old library which is the first of its kind in town. However, the situation was not as rosy at the beginning. I had to post on every pole and stone to attract readers who would otherwise frequent places of entertainment that didn’t include reading.
A typical resident would do something for a living and spend his/her free time at a game zone, pub, with friends or so. Reading would come to the minds of lucky few. If the student who knew he/she had education as the only means of escape from the abject poverty, they may read. They read in a certain fashion. No one would tell them how to.
As a lecturer in English literature at Debre Birhan University, I had to employ my teaching position to promote books and reading. Students who need rare books for their courses and assignments access them at my place.  One would see me carrying a number of books to the university. I also lent them to my students, mostly free of charge.
How is the progress of the library over the years? I will treat this and other issues in my next article.

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...