2021 ማርች 3, ረቡዕ

የራስ አበበ አረጋይ ማስታወሻ ስያሜ ሽሚያዎችን አስመልክቶ የቤተመጻሕፍታችን አቋም

 

የራስ አበበ አረጋይ ማስታወሻ ስያሜ ሽሚያዎችን አስመልክቶ የቤተመጻሕፍታችን አቋም

 

በሁለተኛው የኢጣሊያና ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት ከነበሩ ፈርጦች ግንባር ቀደሙ ራስ አበበ አረጋይ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ በአስር ሺዎች የሚቆጠር ጦር በስኬት በመምራት በዱር በገደል ለአምስት ዓመታት ታሪክ ሲያስታውሰው የሚኖር ፍልሚያ አድርገው የሃገራቸውን ነጻነት አረጋግጠዋል፡፡  በዚያ አስቸጋሪ ወቅት የኢትዮጵያን ባንዲራ ካውለበለቡ ጥቂቶች የጦር መሪዎች አንዱ ናቸው፡፡ የኢጣሊያ ፋሽስት መሪዎች የኢትዮጵያን ህዝብ በብሔርና በቋንቋ ከፋፍለው ለመግዛት ይጥሩ በነበረበት በዚያ ወቅት ራስ አበበ አረጋይ በአንጻሩ በሸዋ የአማራና የኦሮሞ ህዝብን አስተባብረው የተራዘመውን ጦርነት በመምራት ለድል የበቁ ናቸው፡፡

ራስ አበበ አረጋይ በ1953ቱ መፈንቅለ መንግሥት በአረንጓዴው ሳሎን ግድያ ሕይወታቸውን ያጡት ኢትዮጵያን ከሚወዱትና ለምዕራባውያን ከማይመቹት መሪዎች አንዱ በመሆናቸው ነበር፡፡ በ1950ዎቹ ታቅዶ የነበረው ጭሰኝነትን ከኢትዮጵያ የሚነቅል የተባለለት ሰፊ ፕሮጀክትም ሰይፈጸም ቀርቷል፡፡ ከዚያ ወዲህም ሃገሪቱ ወደባሱ ዘርፈብዙ አዘቅቶች በመግባት እድገቷ ቁልቁል እየወረደ መሆኑ ይታወቃል፡፡       

ታሪክን ለማስታወስ እነሆ ዘመኑ ደርሶ ራስ አበበ አረጋይም ሆነ ሌሎች የሃገር ባለውለታዎች በትውልድ እየታወሱ ይገኛሉ፡፡ እኔ በግሌ በታሪክ ትምህርት ስለጀግናው ራስ አበበ አረጋይ ተምሬ አልፌያለሁ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋዎች ጥናት ተቋም በመጀመሪያ ዲግሪ ስመረቅ የመመረቂያ ጽሑፌንም በአርበኞች ተጋድሎ ላይ በተጻፈ ታሪካዊ ልቦለድ ላይ ስሰራ ከዚሁ ፍላጎቴ ይመነጫል፡፡ ከምረቃ በኋላም ታሪካዊ ጉዞዎችን በማድረግ በማስተባበርና የጉዞ ማስታወሻዎችን ጽፌ በማስነበብ አርበኞቻችንና ታሪካችን እንዲታወሱ ጥሬያለሁ፡፡ በ2008 ዓ.ም. ከተርጓሚ፣ ደራሲና የትያትር ሰው አሊሹ ሙሜ ጋር ከአዲስ አበባ ወደ ደብረብርሃን ስንመጣ አካባባውንና ታሪኩን እያነሳን መንገድ መንገዱን ስናወራ አንድ ሃሳብ ተነሳ፡፡ ይኸውም አሊሹ ከዚህ ሁሉ ነገር የሚቆጨው ራስ አበበ አረጋይ ለዚህች ሃገር ይህን ሁሉ ውለታ ውለው አለመታወሳቸው መሆኑን ነገረኝ፡፡ በነገራችን ላይ አሊሹ የሃገራችንና የጥቁር ሕዝብ ትግል የሚስበው በማልከም ኤክስንና የማርከስ ጋርቪን ስራዎች የተረጎመ የጥበብ ሰው ነው፡፡ እኔም በጉዳዩ በመስማማት ደብረ ብርሃንም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱን በእርሳቸው ለመሰየም ተፈልጎ መንግሥት ስለተቀቃወመ መቅረቱን ነገርኩት፡፡ የሆነው ሆኖ ቀድሞ በነበረኝ ፍላጎትና ቁጭት በ2008 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ከተማ የግል ቤተመጻሕፍት ስከፍት ስያሜውን በራስ አበበ አረጋይ ለማድረግ ወሰንኩ፡፡ ይህም ቤተመጻሕፍት ህብረተሰቡን በነጻ እያስነበበ አምስተኛ ዓመቱን አስቆጥሯል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት (ወመዘክር) በደብረ ብርሃን ከተማ ባደረገው የንባብ ሳምንት ወቅት እውቅና ሰጥቶናል፡፡ የግል ቤተመጻሕፍት በፖሊሲ በማይደገፍበተ ሃገር በንባብ ላይ የሚሰራው ቤተመጻሕፍታችን በአፍሪካ ቤተመጻሕፍት ማህበር ንቁ ተሳታፊና በዋና ዋና መርሐግብሮች ኢትዮጵያን የወከለ ነው፡፡ የአሜሪካ ቤተመጻሕፍት ማህበርም በመጽሔቱ ስለቤተመጻሕፍታችን ጸፏል፡፡ ይህ እውቅናና አብሮ የመስራት ፍላጎት ከደቡብ አፍሪካው የርቀት ትምህርት ተቋምና ከሕንዱ ስቶሪ ዊቨርም መጥቶ አብረን እንሰራለን፡፡ በንባብ ላይ ባሳረፍነው አሻራም ምክንያት የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን (ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ዩቱብ ቻነሎችና ጋዜጦች) በቤተመጻሕፍታችን ላይ ዝግጅቶችን በማቅረብ የንባብ ባህልና የቤተመጻሕፍት አገልግሎት እንዲስፋፋ ሰርተዋል፡፡ የቤተመጻሕፍቱ አገልግሎትና ስራ ሰፊ ቢሆንም በዚህ ልቋጨው፡፡

ከተወሰኑ ሳምንታት በፊት በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አዲስ በተሰራው የሕክምና ካምፓስ ውስጥ የሚገኘውን ቤተመጻሕፍት በራስ አበበ አረጋይ ስም ለመሰየም መወሰኑን ይህ ውሳኔ በተላለፈበት ወቅት የነበሩ ግለሰቦች ነገሩኝ፡፡ ይህም ውሳኔ ራስ አበበ አረጋይን ለማስታወስ በማሰብ የተደረገ በመሆኑ አድናቆት ሊቸረው ይገባል፡፡ በፊት አስታዋሽ አጥተው የነበሩትን የሃገር ባለውለታ ዩኒቨርሲቲው ማስታወሱ የሚደነቅ ቢሆንም የራሱ አሉታዊ ጎኖች አሉት፡፡ይኸውም በከተማው ውስጥ በጀግናው የተሰየመ ቤተመጻሕፍት እያለ ሌላ ተጨማሪ መሰየሙ ግርታን የሚፈጥርና አንባቢያንንና ህብረተሰቡን የሚያሳስት ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ቤተመጻሕፍታችንም ምንም እንኳን በአነስተኛ ቦታ የተወሰነ ቢሆንም የራሱን አሻራ እያስቀመጠና በግል ቤተመጻሕፍት ዘርፍ ያለውን ክፍተት በማሳየት በትንሽ ገንዘብ፣ የሰው ሃይልና በውሱን አቅም ትልቅ ስራ መሰራት እንደሚችል እየሳየ ያለ ነው፡፡ መጻሕፍትን በማሳተምና በማከፋፈልም በመላ ሃገሪቱ የንባብና የዕውቀት ትሩፋት እንዲደርስ እየጣረ ያለ ነው፡፡ በመሆኑም ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ይህንን ውሳኔውን እንዲያጤነው ለማሳሰብ እወዳለሁ፡፡ ከተቻለም ቤተመጻሕፍቱ በሌሎች ታዋቂ ደራሲያን፣ ምሁራንና የአገር ባለውለታዎች (ደራሲ ዳኛቸው ወርቁ፣ እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ወዘተረፈ) እንዲሰየም ሊደረግ ይችላል፡፡ ራስ አበበ አረጋይ በብዙ መልኩ እንዲታወሱ ማደረግ ይቻላል፡፡ ግርታን በማይፈጥር መልኩም እስካሁን የታወሱበትንና የተወሰኑ ፍላጎቶችን እናሳይ፡፡ ከላይ እንደተገለጸው በደብረ ብርሃን በግል ቤተመጻሕፍት አስታውሰናቸዋል፡፡ አዲስ አበባ ላይ በስማቸው መንገድና ትምህርት ቤት አለ፡፡ እነዋሪ ላይ ሆቴል ተሰይሟል፡፡ የባንክ ቅርንጫፍም አለ፡፡ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመሰየም ፍላጎት እንዳለም ሰምቻለሁ፡፡ ወደፊት ዩኒቨርሲቲያችን ባለው ተጽዕኖና የሥራ ግንኙነት መሠረት  በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣ በሌሎች ክልሎችም ሆነ በፌደራል ደረጃ ለራስ አበበ አረጋይ ውለታ የሚመጥን ወታደራዊ አካዳሚ ቢሰየም ከእርሳቸው ትክክለኛ ወታደራዊ ጀብዱ ጋር የሚስተካከል ማስታወሻ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ሌሎችም ጀግናውን የሚያስታውሱ ስራዎች ቢሰሩ ለውለታቸው ሲያንስ አንጂ አይበዘባቸውም፡፡

 

መዘምር ግርማ

የራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት ሥራ አስኪያጅ

ሰኞ የካቲት 22፣ 2013 ዓ.ም.

ደብረብርሃን 



 

 

2021 ፌብሩዋሪ 28, እሑድ

የመጽሐፍ ዳሰሳ

 የመጽሐፍ ዳሰሳ

(በዚህ ገጽ የተከፈለበት)



የመጽሐፉ ርዕስ - Marcus GARVEY፣ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አፍሪካ

 ደራሲ - ማርከስ ጋርቪ

 የመጽሐፉ ተርጓሚ - አሊሹ ሙሜ

 ዘውግ - ግጥሞች 

 የገጽ ብዛት - 142

ዋጋ - 69

የታተመበት ጊዜ - 2007 ዓ.ም.

ዳሰሳ ጸሃፊ - ሃይማኖት ክንፈ

የተከበራችሁ ውድ የመጽሐፍ አፍቃሪያን እንደምን ሰንብታችኋል?ሰላም እና ጤና እንዲሁም  ፍቅር ከሁላችሁ ጋር እንዲሆን እየተመኘሁ! ወደ መጸሐፍ ዳሰሳዉ ስገባ:-

ማርከስ ጋርቪ ይባላል የመጽሐፉ ደራሲ ሲሆን በትውልድ የጃማይካዊ ነው። ጋርቪ የጥቁር ዘር መሪ፣ጋዜጠኛ፣ተነግሮ አሳማኝ እንዲሁም ርእዮተ አለማዊ ሰው ነበር። ከዚህም በተጨማሪ ማርከስ ጋርቪ ገጣሚ ሲሆን የደቡብ እና የመካከለኛውን አሜሪካ ግዛቶች ተንቀሳቅሶ ከጎበኘ በኹዋላ በ1912 ወደ እንግሊዝ ሀገር ተጓዘ።በእንግሊዝ ሎንደን ከተማ ሳለ ለአፍሪካ ታሪክ እና ባህል ልዩ ትኩረትን ሰጥቶ የግል ጥናቱን አከናወነ።

 አንደበተ ርቱእ የሆነው ማርከስ ጋርቪ በአሜሪካ የሚኖሩ ጥቁሮችን "በዝርያችሁ ኩሩ፤"ብሎም "ወደ አያት ቅድመ አያቶቻችሁ ምድር ወደ ቅድስት አፍሪካ ተመልከቱ!"እያለ መስበኩን ቀጠለ።

በፓን አፍሪካኒዝም እንዲሁም በፈረንሳይ ሀገር የአፍሪካውያን "ኔግሪቱድ"ንቅናቄና የለንደኑ የምእራብ አፍሪካ ተማሪዎች ህብረት እና ሌሎችም የጥቁር ነፃነት ትግሎች በተነሱ ቁጥር ከነ ኤድዋርድ ዊልመንት፣ክዋሜ ንክሩማ፣ጁሙ ኬንያታ፣ማልኮም ኤክስ እና ሌሎችም ስሞች ጋር ማርከስ ጋርቪ መወሳቱ አይቀሬ ነው።

 ማርከስ ጋርቪ ገና የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ አገዛዝ ቀንበር ባልተላቀቁበት ጊዜ እንኳን "ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አፍሪካ "የሚለውን መሪ ህልም ከአእምሮው አመንጭቶ ታግሎ ያታገለ ጀግና ነው። ጋርቪ የአፍሪካ ዝርያዎችን ወደ አፍሪካ እንዲመለሱ ሆኖ የበለፀገች በራሷ ህዝብ የምትተዳደር ጠንካራና ነፃ የሆነች አንዲት አዲስ አፍሪካን መፍጠር ነበር አላማው።

 በጥሞናዊ የስነግጥም ስራዎቹ ውስጥ የመጀመሪያውን የኢንፔሪያሊስቶች ሽንፈት ከዋኝ የሆኑትን የአድዋ መሪ የሆኑትን አጤ ሚኒሊክ፣ከዚህ ሽንፈት በኹላም በኦጋዴን በኩል የጣሊያን ወረራ ያርበደበዱትን ራስ ነሲቡ ዛማኔልን እና ለኢትዮጵያ የተዋጋው ቱርካዊ ውሂብ ፓሻ አንዲሁም የደቡብ ክንፍ ተዋጊ የነበሩትና ቡታጅራ የተሰውትን ራስ ደስታ ዳምጠዉ የመሳሰሉትን የነፃነት ታጋዮች በስም ለመጥቀስ የመታሰቢያ ግጥሞችን አበርክቶላቸዋል።



 በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን በዘመናዊው ባርነት እየተገዛን ላለነው አፍሪካውያን ራሳችንን እንድንመለከት ያደርገናል። እንዴት? ብትሉ ዛሬም በዲቪ ሰበብ እነሱ የናቁትን የስራ አይነት ወይም ምርጫ በማጣት ሳቢያ ዛሬም በአውሮፕላን ተሳፍሮ፣በመኪና ተሽከርክሮ፣በመርከብ፣በታንኳ፣በጀልባ፣በበቅሎ፣በግመል እንዲያም ሲል በእግሩ ኳትኖ እዚያዉ ስፍራው ድረስ በመሄድ የሁነቱ ሰለባ መሆን እጅግ የሚያሳዝን እውነታ ነው።ይህ መጸሐፍ አይናችንን ገልጠን እውነታውን እንድናይ አመላካች ሲሆን እንደ እንደ አፍሪካዊ ምን ማድረግ አለብን የሚለውን በግጥሞቹ እያነሳሳ ፣እየመከረ እና እየኮረኮመም ያስተምረናል።

 ይህን መፅሃፍ ማን ሊያነበው ይገባል? ይህ የማርከሰ ጋርቪ ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አፍሪካ መፅሐፍ በታሪክም ሆነ በምርምር ተግባር ለተሰማሩ የኢትዮጵያ ወጣቶች ለሀገራቸውና ለህዝባቸው ተቆርቋሪና ታጋይ ዜጋ እንዲሆኑ ከማገዝም ባሻገር ለአንባብያን የንባብ ፍጆ ወይም የዚያን ዘመን ከዚህኛው ጋር በማጣቀስ ምርምር ማድረግ ለሚሹ ሁሉ የጠብታንም ያህል አስተዋፅኦ ያደርጋል።


2021 ጃንዋሪ 21, ሐሙስ

የግል ቤተመጻሕፍት ለመክፈትና ለማንቀሳቀስ ስላደረኴቸው ነገሮች

 


(ፍላጎቱ ያላቸው እንዲጀምሩት በማሰብ የተጻፈ)

1.       መጻሕፍት በሽያጭ የማገኝባቸውን ቦታዎች አወቅሁ፡፡ እነዚህ ቦታዎች በአዲስ አበባ ያሉ የመጻሕፍት ማከፋፈያ መደብሮች ናቸው፡፡ መጀመሪያ ላይ ያገለገሉ መጻሕፍትንም እገዛ ነበር፡፡ በኋላ ግን ሻጩ ከየት አምጥቶ እንደሚሸጥልኝ ስለማላውቅ ትቻለሁ፡፡ ግለሰቦች ሲለግሱም እቀበላለሁ፡፡

2.       ሰፋ ያለ ቤት ተከራየሁ፡፡ ወንበር፣ ጠረጴዛ፣ መደርደሪያና መጻሕፍት አሟላሁ፡፡

3.       ሰራተኛ ቀጠርኩ፡፡ እኔም እሰራለሁ፡፡

4.       ንግድ ፈቃድ ‹‹የጽሕፈት መሳሪያና መጻሕፍት ችርቻሮ ንግድ›› በሚል ዘርፍ አወጣሁ፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ በንግድ ሕጉ ቤተመጻሕፍት የሚል ስለሌለ ይህን ዘርፍ መምረጥ ግድ ይላል፡፡ ግብር የሚተምኑ ሰዎች ሲመጡ የምሰራውን ስራ አይተው ግብር መተመን እንጂ ሌላ ይህን አትስራ የሚሉት ነገር የለም፡፡

5.       ስለቤተመጻሕፍት አሰራር ለማንበብ ሞከርኩ፡፡ በአማርኛ በዚህ ዘርፍ የተጻፈ ነገር ያለው ኮድ ኢትዮጵያ ያዘጋጀው ያልታተመ ሞጁል ነው፡፡

6.       ለቤተመጻሕፍቱ መጀመሪያ ሥራ ማስኬጃ የተወሰኑ አስርት ሺዎች ብር ተጠቅሜያለሁ፡፡ 

7.       የተለያዩ የቤተመጻሕፍት መርሃግብሮችን ጀምሬያለሁ፡፡ ለምሳሌ የውይይትና ሥነጽሑፍ ምሽት፣ የጉዞ መርሐግብር፣ ሥልጠና ወዘተ፡፡

8.       ሥራውን ልጀምር አካባቢ የጠየኳቸው ሰዎች ቢዝነስ ፕላን እንዳለኝ ጠይቀውኝ የነበረ ቢሆንም እኔ ስለቢዝነስ ፕላን የማውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ለማዘጋጀትም አልሞከርኩም፡፡ ይህ ትልቅ ድክመቴ ነው፡፡ የሚጀምር ሰው ቢያዘጋጅ መልካም ነው፡፡

9.       ‹‹ይህን ስራ ስትሰራ ዓላማህ ምንድነው? በትክክል ጥርት ያለ ዓላማ ሊኖርህ ይገባል!›› ያለኝ ሰው ነበር፡፡ ያንንም ጥርት አድርጌ አለማወቄን እንደ ድክመት አየዋለሁ፡፡ ዓላማችንን ካላወቅን ተስፋ መቁረጥ ሊከተልና ስራውም አደጋ ላይ ሊወድቅ ስለሚችል ከመጀመራችን በፊት ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ በእርግጥ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ማድረግ እንደማልፈልግ፣ በነጻ ማስነበብን፣ በቅናሽ ዋጋ ማከራየትንና መሸጥን ያካተተ ስራ እንደምሰራ አውቀው ነበር፡፡ አሁንም በዚያ እንደገፋሁበት ነኝ፡፡ አሁን ላይ ሆኜም ሳስበው ከኪራይ ቤት ብቆይ እመርጣለሁ፡፡ ቤት የመስራትን ጣጣ አልፈልገውም፡፡ የቤት ኪራይ ከከበደ መፍትሔ መፈለግ ነው፡፡ ገንዘብ የማመነጭበትን መንገድ እፈልጋሁ፡፡

10.   መጽሐፍ ስለማከራየት መግለጽ ያለብኝ ነገር ቢኖር በመታወቂያ ማከራየት አክሳሪ መሆኑን ነው፡፡ በቤተመጻሕፍታችን ከ200 በላይ ያልተመለሱ መጻሕፍት አሉ፡፡ በመሆኑም ከሁለት ዓመት አገልግሎት በኋላ ገንዘብ በማስያዝ እንዲከራዩ አድርገናል፡፡ ይህ አሰራር በእርግጥ ገንዘብ የሌላቸው ሰዎች እንዳይከራዩ ያደርጋል፡፡ ይሁን እንጂ ከሚያስከትለው ችግር አንጻር ሁነኛ መፍትሔ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡ መከራየት የማይችል ሰው ቤተመጻሕፍቱ ባቀረበለት በነጻ የማንበብ ዕድል ይጠቀማል፡፡

11.   ‹‹ስራው አትራፊ ነው ወይ?›› ብሎ ለሚጠይቅ ሰው ‹‹አንባቢ ባለበት ከተማ ሊያተርፍ ይችላል›› የሚል መልስ እሰጣለሁ፡፡ ወይም ከአትራፊ ቢዝነስ ጋር በጥምረት ሊሰራ ይችላል፡፡ ስራው የንባብ ጉዳይ ለሚስበውና ቤተመጻሕፍት ኖሮት ለማየት ለሚፈልግ ሰው ጥሩ ጊዜ ማሳለፊያና ህብረተሰብን ማገልገያ መንገድ ነው፡፡

12.   ለተጨማሪ መረጃ ቢጠይቁኝ ለማገዝ ዝግጁ ነኝ፡፡ ምናልባት ስለ ቤተመጻሕፍቱ መረጃ ለሌላችሁ ሰዎች ራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት ይባላል፡፡ መገኛው ደብረ ብርሃን ነው፡፡ መጋቢት 2008 ዓ.ም ተመሰረተ፡፡ ንብረትነቱም የግል ሲሆን፤ በቤተመጻሕፍቱ በነጻ ማንበብ፣ በቀን 1 ብር በመክፈል መከራየትና እንዲሁም መግዛት ይቻላል፡፡

2021 ጃንዋሪ 12, ማክሰኞ

ንባብ ተኮር የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ለሁላችሁም

ከመዘምር ግርማ (mezemirgirma@gmail.com)

ዛሬ ላስተዋውቃችሁ የፈለኩት ጉዳይ ማናቸውም ሰው መጽሐፍ ሻጭ እንዲሆን ለማድረግ የሚቻልበት ዕድል መኖሩን ነው፡፡ ማንም ሰው ከቤቱ፣ ከመስሪያ ቤቱ ወይም ከተመቸው ቦታ ሁሉ ሊሰራው የሚችለው ይህ ሥራ ብዙ መነሻ ገንዘብ የማይጠይቅና የጊዜ ነጻነትም ያለው ነው፡፡ መጻሕፍትን ከደራስያን፣ ከአሳታሚዎች፣ ከሻጮችና አንብበወው ከሚሸጡ ግለሰቦች በመውሰድ ለተጠቃሚዎች ማድረስ ይቻላል፡፡ ይህን ሥራ በሚገባ ለመስራት አዳዲስና ያገለገሉ መጻሕፍት የሚገኙባቸውን ቦታዎች ማጥናት፣ ተፈላጊ መጻሕፍትን ማወቅና አንባቢ መሆን ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ የመጻሕፍትን መገኛ ካወቅንና መጻሕፍቱንም ካነበብናቸው ዳሰሳ መጻፍ፣ ተናግረን ማሳመንና መሸጥ እንችላለን፡፡  ይህ ብቻ ሳይሆን በደንብ ባለመተዋወቃቸው ምክንያት ያልተሸጡ መጻሕፍትን አንብቦ ጥሩ ይዘታቸውን ለማስተዋወቅ ለአንባቢ ማድረስ ይቻላል፡፡  የዚህኛው ዓይነት ሥራ ጠቀሜታው ብዙ ቁጥር ያለውን መጽሐፍ በአንድ ጊዜ ለማግኘትና ከፍተኛ ትርፍ ለማግኘት መቻሉ ነው፡፡ ለምሳሌ ዘአልኬሚስት የተባለው የፓውሎ ኮሊዮ መጽሐፍ በስድስት ወራት ሁለት ኮፒዎች ብቻ ተሸጦ ከብዙ ጊዜያት በኋላ በአንድ አጋጣሚ በሚሊዮኖች ቅጂዎች የተሸጠ መሆኑን ማስታወስ ግድ ይላል፡፡

መጻሕፍትን ለማን እሸጣለሁ የሚለው አንድ አሳሳቢ ጉዳይ ሊሆንብዎት ይችላል፡፡ ይህን እርስዎ እንደ አንድ የቤት ስራ ወስደው እነማን ማንበብ ይችላሉ ብለው እንዲያስቡ ያስፈልጋል፡፡ ማንበብ የሚችሉ ሰዎችን ወደ አእምሮዎ ማምጣት ከቻሉ እንዴት ላስነብባቸው የሚለው ይከተላል፡፡ ማንበብ ጀምረው ከሆነ በዚያው እንዲቀጥሉ የፈለጉትን መጻሕፍት ያቅርቡላቸው፡፡ በየመስሪያ ቤቱና በየሰፈሩ የመጻሕፍት ዕቁብ መስርተውም ለመጻሕፍት ዕቁቡ መጽሐፍ ያቅርቡ፡፡ የማንበብ ልምድ የሌላቸው ከሆኑም ልምዱን እንዲያጎለብቱ አድርገው ወደ ንባብ ዓለም ያስገቧቸው፡፡ ሰዎች በሚፈልጉት ነገር ማንበብ ቢጀምሩ ጥሩ ነው፡፡ ከሚፈልጉት ጋር ማያያዝ ያስፈልጋል፡፡ ወደ ኃይማኖት ዝንባሌ ላላቸው ደንበኞችዎ ከአንድ የመጻሕፍት መደብር የኃይማኖት ማጻሕፍት ስብስብ ያሉ መጻሕፍትን ፎቶ አንስተው ያስመርጧቸው፡፡ የመረጡትንም ያቅርቡ፡፡ የሥራ ፈጠራ ዝንባሌ ላላቸው፣ የስነልቦና መጻሕፍት ለሚወዱ፣ የቴክኖሎጂ ለሚያዘወትሩ ወዘተ እያጠኑ ያቅርቡ፡፡ ለስራዎም ሃያ አምስት በመቶና ከዚያ በላይ ኮሚሽን ያገኛሉ፡፡ በቅርብዎ ያሉትን አንባቢያን ካካለሉ በኋላ በማህበራዊ ሚዲያ፣ በቢዝነስ ካርድ ወይም በሌላ ሁነኛ መንገድ ስለስራዎት ማስታወቂያ ይስሩ፡፡ ይህም ማስታወቂያ ወደ ክፍለሃገርና ወደ ውጪ ሃገር መጻሕፍትን መላክ ያስችልዎታል፡፡ መጻሕፍት ተቀባዮች ያምኑዎት ዘንድ ግድ ስለሚል እምነትን የሚገነቡ ነገሮችን ይመርምሩ፡፡

ሌላው ወሳኝ ነገር የእርስዎ አንባቢት በመሆኑ እርስዎ በቤትዎ የመጻሕፍት ስብስብ ይኑርዎ፡፡ ያንን ስብስብ ለማንበብም ሆነ ድንገት ሲታዘዙ ለመሸጥ ይጠቀሙበት፡፡ በሃገራችን ንባብ ገና ያልተነካና የማደግ እድሉ ሰፊ የሆነ ዘርፍ በመሆኑ ለብዙ ሺ ሰዎች የስራ ዕድል ይፈጥራል፡፡ በትንሹ አዟሪዎችንና አነስተኛ ሱቅ ያላቸውን ወገኖች ይመልከቱ፡፡ ለውጣቸው በየቀኑ የሚታይ ነው፡፡ ከማናቸውም ስራ ጋር የሚያስኬዱትና ትውልድን በማነጽ ላይ ትልቅ ሚና እንዲጫወቱ የሚያስችልዎትን ይህን ዘርፍ ቢቀላቀሉ እንኳን ደህና መጡ ብለን እጃችንን ዘርግተን እንቀበልዎታለን፡፡ ከምረቃ በኋላ ሥራ አጥ ሆነው ቀን በቀን ገንዘባቸውን በመከስከስ ላይ ያሉ ወጣቶች የማንበብ ችሎታ እያላቸው ያንን ኢንቬስትመንት ለምን እንደማይጠቀሙት አይገባኝም! እነዚህ ወጣቶች ዕድሜያቸውን ያሳለፉት በመማር ስለሆነ ያንን ትምህርት ቢያንስ የአንባቢያንን ፍላጎት የሚያረካ መጽሐፍ በመምረጥ መጠቀምና መጽሐፉን ሸጠው ኮሚሽን ማግኘት ይቻላቸዋል፡፡

የኦንላይን ገበያ ወደሃገራችን እየገባ ስለሆነ በቅርብ ጊዜ መጻሕፍትን ማናቸውም ሰው መሸጥ እንደሚችል ከሌሎች ሃገራት ልምድ ማየት ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ አሁኑኑ መጀመር ለወደፊቱ ልምድ እንዲኖርዎ ያስችላል፡፡

ጥያቄ ካላችሁ በአስተያየት መስጫው ላይ ብቻ ጻፉልኝ፡፡ ይህም የጥያቄዎችን መደጋገም ለማስቀረትና ምልልሱን ሁሉም አባል እንዲያየው ማለት ነው፡፡

መልካም ስራ!


2020 ዲሴምበር 24, ሐሙስ

ለታዳጊ ሃገራት የተመረጡ የሥራ ፈጠራ ሃሳቦች

 


አሰናጅ - መዘምር ግርማ

 

መግቢያ

በታዳጊ አገር እንደመገኘታችን ያለንበት ሁለንተናዊ ሁኔታ ከሌላው ዓለም የተለየ ነው፡፡ አዳዲስ ነገር የምንሞክር ሰዎች ለአካባቢያችን ተመራጭ የሆነ የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ያስፈልገን ይሆናል፡፡ ስለሆነም ላለንበት ዘመንና አካባቢያዊ ሁኔታ የሚስማሙ የሥራ ፈጠራ ሃሳቦችን ማወቅ ይኖርብናል፡፡ በዚህም መሠረት ከድረገጽ ያገኘነውን ጽሑፍ በአጭሩ ወደ አማርኛ መልሰነዋል፡፡ በየሥራ ዘርፉ ያለውን ዕድልና ዝርዝር ሁኔታ ለማወቅ ድረገጹን እንድታነቡት እንጋብዛለን፡፡ ምናልባትም እንግሊዝኛ ቋንቋ የሚቸግራችሁ አንባቢያን ከድረገጹ ጽሑፉን ገልብጠችሁ በመውሰድ በጉግል ትራንስሌት ተርጉማችሁ በአማርኛ ማንበብ የምትችሉ መሆኑን ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

 

ዝርዝር የሥራ ዓይቶቹን እነሆ፡-

1.     ደረቅ ቆሻሻ መሰብሰብ

2.     የሕጻናት ማዋያ

3.     ግብርና

4.     የቁጠባ ቤቶች አቅርቦት

5.     የውበት ሳሎን

6.     በድረገጽ ሙያን መሸጥ

7.     ብሎግ መጀመር

8.     የፀሐይ ኃይል ላይ የተመሰረተ ሥራ

9.     የስማርት ስልክ ሽያጭ

10.  ማስጠኛ ማዕከል

11.  ጭማቂ ቤት

12.  ልብስ ስፌት

13.  ሥዕልና ቅርጻቅርጽ

14.  አፕሊኬሽንና የኦንላይን ስራዎች

15.  ዘመናዊ የክፍያ መንገዶች

16.  አነስተኛ ብድርና ቁጠባ

17.  የጉዞ ወኪል

18.  የሞባይል ካርድ መሸጥ

19.  የዩቱብ ቻነል መጀመር

20.  ዕደ ጥበብ ማስተማር

21.  የሙዚቃ መምህርነት

22.  የስፖርት አሰልጣኝነት

23.  አስጎብኚነት

24.  የበይነመረብ የምግብ አሰራር ትምህርት

25.  ቁርስ ቤት

26.  አማራጭ የኃይል ምንጭ

27.  ነዳጅ ቆጣቢ ፈጠራ

28.  አስመጪና ላኪ

29.  ያገለገሉ ዕቃዎች ሱቅ

30.  ሥጋ ቤት

31.  ጥበቃና ደህንነት

32.  የሰራተኛ አገናኝ

33.  የኤሌክትሮኒክ ንግድ

34.  የዳሰሳ ጥናትና መረጃ ስብሰባ

35.  አማራጭ የኃይል ምንጭ

36.  የዕቃ ግዢ አገልግሎት

37.  የማጓጓዝ ሥራ

38.  የኮምፒውር ነክ መረጃ ጥበቃ

39.  የትምህርት ማማከር

40.  የእጥበት አገልግሎት

41.  ጥገና

42.  የጤና አገልግሎት

43.  የኮምፒውተር አገልግሎት ማዕከል

44.  የሂሳብ ሥራ

45.  የቢዝነስ ዕቅድ ሥራ

46.  የመኪና እጥበት

47.  የኮምፒውተር አሰልጣኝነት

48.  የግል የአካልብቃት አሰልጣኝነት

49.  የትርጉም አገልግሎት

50.  ቤት ለሚለቁ ዕቃ ማጓጓዝ

ማጠቃለያ

እስኪ ከእነዚህ ከላይ ከተጠቀሱት የምርትና አገልግሎት ዓይነቶች የትኞቹን ለመሞከር አሰቡ? የትኞቹስ በአካባቢዎ ተጀምረዋል? የትኞቹስ አዳዲስ ናቸው? ለመጀመር የሚያስፈልጉዎትን ነገሮች ያስቡባቸው፡፡ መሬት ወይም ቦታ፣ ገንዘብ፣ ሥልጠና፣ የሠለጠነ ሠራተኛ ወይስ ሌላ? ለእነዚህና ሌሎች ጥያቄዎች የሚመጡልዎትን መልሶች በመጻፍ ያቅዱ፡፡ ሌላ የማንክደው ነገር ከላይ የተገለጹት የሥራ ዘርፎች ላይ አልፎ አልፎ ተመሳሳይነትና ብዥታ ሊኖር ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ እያንዳንዳቸው የየራሳቸው ልዩ ባህርያት አሏቸው፡፡ ከኛ አገር ሁኔታም ጋር አጣጥሞ በማሻሻል በግልም ሆነ በቡድን መስራት ይቻላል፡፡ በቀጣይ ተከታታይ ዕትሞቻችን ሥራ ፈጠራን አስመልክቶ ተከታታይ ጽሑፎችን እንደምናወጣ እየገለጽን ለማናከውም ጥያቄዎ እንዲጽፉልን እንጋብዛለን፡፡

      በሸዋጸሐይ ዝግጅት ክፍል አድራሻ ወይም በ mezemirgirma@gmail.com    

ውድ አንባቢያችን፡- እርስዎም በጉዳዩ ላይ በደንብ አስበውበት በኛ ሁኔታ ሊሰሩ የሚችሉ አስር የሥራ ፈጠራ ሃሳቦችን ከላኩልን ጥሩ የምንላቸውን በቀጣይ ዕትሞች የምናወጣ ይሆናል፡፡

2020 ሴፕቴምበር 2, ረቡዕ

ዘጠና ቀናት በአዲስ አበባ፣ ተጻፈ በመዘምር ግርማ

 ዘጠና ቀናት በአዲስ አበባ

ተጻፈ በመዘምር ግርማ

ከሰኔ 1፣  2012 እስከ ነሐሴ 30፣ 2012 በአዲስ አበባ ስላደረኩት ቆይታ አንዳንድ ነገሮች

ሀ. ሰኔ 1፣ 2012 ዓ.ም. ከደብረ ብርሃን ከሞቀ ቤቴ ወደ አዲስ አበባ መጥቼ አነስተኛ የመኖሪያ ቤት ተከራይቼ ሁቱትሲን አሳትሜ ማከፋፈል ጀመርኩ።

ለ. ሁቱትሲ የሩዋንዳዊቷ የኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ የዘር ማጥፋት ወቅት ማስታወሻ የ Left to Tell የአማርኛ ትርጉም ነች። 

ሐ. በ2008 ዓ.ም. የመጀመሪያ ዕትሟን ሳወጣ 62,000 ብር ለማተሚያ ቤት ከፍዬ ነበር። መጽሐፉ ተከፋፍሎ ገንዘቡ በወቅቱ ስላልተሰበሰበ ደግሜ ለማሳተም የሚሆን ገንዘብ ለማግኘት አራት ዓመታት ፈጅቶብኛል።

መ. ይህም የሆነው ከመጽሐፉ ሕትመት በኋላ በደብረብርሃን የከፈትኩት ራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት ወጪ ስለሚያስወጣኝ ነው።

ሠ. እንደ መምህርነቴ ከመጋቢት መጀመሪያ እስከ ግንቦት መጨረሻ በኮቪድ ምክንያት እረፍት ላይ ስለነበርኩ በራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት በአስነባቢነት ሰርቻለሁ። ይህም የሆነው አስነባቢዎቹ በበሽታው ምክንያት ከስራቸው ስለለቀቁና ገጠር ስለገቡ ነው። ከሰኔ እስከአሁን አዲስ አስነባቢ ስላገኘሁ በሷ መኖር ምክንያት ነው አዲስ አበባ ልቀመጥ መቻሌ።

ረ. በጥቅሉ መጽሐፏ ከሁለተኛ እስከ አራተኛ ዕትም 20,000 ኮፒ የተሸጠች ሲሆን፤ ይህም በቀን በአማካይ 222 መጽሐፍ እንደተሸጠ ያሳያል።

ሰ. መጀመሪያውኑ በክረምትና በኮቪድን መምጣት ምክንያት አንባቢያን መጽሐፏን ይፈልጋሉ የሚል ሐሳብ ስለመጣልኝ ወደ ህትመቱ ሥራ ገብቻለሁ። 

ሸ. ሥራው ብዙ ውጣውረድ ያለው ሲሆን ወደ ተስፋ ማስቆረጥ ደጅም አድርሶ ይመልሳል። ቢሆንም የመጻሕፍት ማሳተምና ማከፋፈልን ሥራ ከታች በመጀመር ላውቅበት ችያለሁ። በአሁኑ ወቅት ሁለት የሌሎች ደራሲያንን ሥራዎች በአሳታሚነት ወደ ማተሚያ ቤት አስገብቻለሁ። ይህም እነዚህ ሦስት ወራት የሥራ ፈጠራ ሕይወቴን እንዴት እንደቀየሩት ለማየት ይቻላል።

ቀ. ማህበራዊ ሚዲያ፣ ዋናው ሚዲያና ብዙ ወዳጆቼ ለመጽሐፏ መሰራጨት ትልቅ ሚና ተጫውተዋል። ከነዚህም ውስጥ አማራ ቴሌቪዥን፣ ሠይፉ በኢቢኤስ፣ አልዐይን አማርኛ፣ ፀደይ ኤፍኤም 102.9፣ የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ፣ Meet EBC (ተፈራ ገዳሙ) እና ሌሎችም ተጠቃሾች ናቸው።

በ. አሁን የሚቀረን በመጽሐፉ ላይ መወያየትና ለሃገራችን የዘር ተኮር ችግሮች የጋራ መፍትሔ ለመፈለግ መሞከር ነው።

ተ. ከመጽሐፉ ሽያጭ ከተገኘው ትርፍ ባለፈው ወር ለሦስት የሰኔ 2012 የዘርና የኃይማኖት ጥቃት ሰለባዎች 30,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል። ከሰሞኑም ለአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ትምህርት ቢሮዎች በስራቸው ለሚገኙ አብያተ መጻሕፍት የ60,000 ብር የሁቱትሲ መጻሕፍት ድጋፍ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል። 

ቸ. ከሚያዝያ 27፣ 2012 ዓ.ም. ጀምሮ በቀን አንድ ጊዜ (ጠዋት ብቻ) ተመጋቢ በመሆኔ በረሃብ አንጀቴ እንደምሰራ ሊታሰብም ይችላል። ክብደቴ አስር ኪሎግራም ያህል ቀንሷል። 

እስኪ የጋራ ጉዟችንን እንወያይበት።

ሁላችሁንም አመሠግናለሁ።

አንዲት ነገር ይፈቀድልኝ።

ደብረብርሃንን በጣም እንደምወዳት ስርቃት ገባኝ። እናም ከመስከረም 2013 ጀምሮ ወደ ደብረብርሃኑ ቤቴ በመመለስ የማሳተምና የማከፋፈል ሥራውን ከዚያ እየተመላለስኩ ወይም ሥራ አስኪያጅ ቀጥሬ እሠራለሁ/አሰራለሁ።

ሌላ ዋና ነገር

ሞትን ንቄው እንደከረምኩ ይሰማኛል። አዲስ አበባን ሲዞር የዋለ ብር ከየመጻሕፍት አዟሪውና መደብሩ እኔ ጋ ቢመጣም ለኮቪድ የነበረኝ ጥንቃቄ ዜሮ ነበር። ሰኔ አንድ የገዛሁት ሳኒታይዘር አሁንም አለ። ይህ ከኔ የሚጠበቅ ነገር ባይሆንም መጠንቀቁ ስለሰለቸኝ ነው።  በማናቸውም ደቂቃ ልወድቅና በዚያው ልቀር እንደምንችል ወይም በተኛሁበት ላሸልብ እንደምችል እየተሰማኝ ሦስት ወር ቆየሁ። ዘጠና ቀናት በሩዋንዳ የነገሰው ሞት በአዲስ አበባም በኮሮና ወረርሽኝ መልክ ማንዣበቡን እሰማለሁ። ይሁን እንጂ ሳይነካኝ ወደ ደብረብርሃን ልመለስ እንደሆነ ይመስለኛል።

አምስተኛው ዕትምስ?

አይ ቆይ፣ ለማተሚያ ቤት ልጆችም እናስብ! ዓመት በዓሉን አረፍ ይበሉና ከበዓል በኋላ ያትሙታል። እስከዚያው መጽሐፉን የገዛን ሰዎች እየተዋዋስን እናንብብ።

2020 ጁላይ 15, ረቡዕ

My Eyewitness Account of the Riot in Addis Ababa

Mezemir Girma, translator of "Left to Tell, Discovering God Amidst the Rwandan Holocaust" to Amharic

June 30 - July 15 2020
Email: mezemirgirma@gmail.com

"Kan nama nyaatu nu keessa jiraa. = The cannibal is among us." Hachalu Hundessa

"Oh, genocide! In Rwanda they were just two ethnic groups. If it comes to Ethiopia? Who knows who kills us? May God save us!" Professor Merera Gudina answering a question I asked him in 2017 on whether he thinks a genocide erupts in our country. I was one of the lecturers who visited him in his party's headquarters in Addis to console him about his expulsion from his teaching position at Addis Ababa University.

An ethnic Amhara mourner who gave an interview to the VoA a week after the current wave of attacks in Oromia Region
said that he suspects that there is a hidden government going operational in this country so as to orchestrate these systematic and selective attacks on his relatives who have been the targets of brutal killings.
This one is an extraordinary observation and awakening unlike some of the Tutsis of Rwanda who believed that the state and everyone in power was doing everything possible to curb genocidal plots.

My esteemed readers,
Instead of this bad news, I wish I announced a certain development program useful for the country. However, today is destined to be the day I sadly scribble what I observed in Addis Ababa.

Tuesday (June 30 - the day after the
assassination of Hachalu Hundesa):
I learned about the death of Afaan Oromo Artiste Hachalu Hundessa from Facebook at 4:00 AM on Tuesday morning. As usual, early in the morning, I walked to my place of work in Biherawi. A few shops and offices opened here and there at that time of the day. I went to the Post Office to mail a dozen copies of my translation of the memoir of a Rwandan woman to Ethiopians in the diaspora. A Post Office worker told me that they don't send to Dubai and Qatar at this time of the COVID 19 pandemic. I carried the books back and placed them at a nearby coffee shop. Customary as it has been during riots in the country, a little after 8:00 AM the internet connection was completely shut down. I couldn't surf the net nor take photos of the fearsome situations. At Biherawi, the financial hub of the nation where almost all bank headquarters are being built, rioters set up roadblocks, and jogged carrying sticks. Broken glass doors and window panes are also seen everywhere. The people who were working, buying and moving in the area were threatened and had to seek refuge in hideouts nearby. I went to the coffee shop and spent the time the raging rioters reigned at. The people hiding speculated that the rioters were heading to Emperor Minelik's statue, located near St. George's Church. This statue, a symbol of the unification of modern Ethiopia, remained a point of contention in the recent Ethiopian political strife. The youth who demonstrated filled the area from the Headquarters of the Ethiopian Broadcasting Corporation to the Black Lion High School, about a hundred metres long. They were encircled by armed security personnel. As the situation escalated, I went back to a place near my home in Lideta. I sat at the veranda of a cafe, on a second floor of a building opposite Lideta Park. In a motorway about a hundred metres from where I was the youth from the neighborhood were fighting with the rioting youth who were carrying sticks. Hurling stones at the stick-carrying youth, these boys who were not more than twenty in number, were receiving flying sticks in return. Police intercepted and the fighting stopped. While all this was unfolding, people at the cafe, some of whom old enough to be grandparents, were complaining about the time and situation God let them live to see. They reprimanded the boys from Addis to stop throwing rocks. They warned the defenseless people living outside of Addis Ababa would be victims of retaliatory measures the rioters may take when they go back home.

Wednesday (July 1):
On this day, I headed to my work place only to find all businesses closed. There were few cars on the road. One of the very busy traffic-light stops at Lagare had only one car from each of the four directions. Security got tighter. Armoured personnel carriers (APCs) were seen here and there. The military also went out of their barracks to calm the nation down. Ethnic-based attacks, the burning down of properties and other forms of violence in parts of Addis Ababa and its outskirts were said to take place. Towns within the Oromia Regional State were also said to have entertained similar incidents. Top government officials gave briefings and press releases. Opposition politicians, journalists and people suspected of plotting to create havoc were reported to have been imprisoned. At a cafe, I saw Aljazeera's news coverage on the incident. They concluded the report by reminding their viewers that the Oromo were the largest ethnic group deprived of political and economic rights in the country.

Thursday: (July 2)
Artiste Hachalu Hundesa's remains have been buried in the morning. I heard the program live from Ambo Stadium and the funeral site from the radio on my phone. My cute memories of a week I spent in the beautiful Ambo town started to recollect. I had no radio receiver or TV set in the week the riot took place to comfortably check from foreign media. I sat at Wabe Shebele Hotel in the afternoon when I learned with difficulty from the low sound of the TV an Aljazeera broadcast. They reported about the burial of the artiste. On this very day, local FM stations reported that certain political parties and their agents were held responsible by authorities for the incidents in the metropolis. The government gave briefings and releases through the Public Prosecutor, the PM, his deputy, the Mayor of Addis, and Oromia's President among others.
Many of my friends and relatives called to check my well-being and I also did the same to those living in Addis in return. People I met on this day asked me if the rioters came to our house at night and I told them that they didn't. Rain played key roles in preventing demonstrators from accessing the in and outs of the city. As far as I am concerned, nothing is heard in the compound I live in or nearby. The people who asked me, on the contrary, told me that there were such tough cases.

Friday (July 3):
As the Mayor of Addis Ababa Engineer Takele Uma had ordered the day before, normal business resumed. Those who lost their loved ones, who were enjured and those who lost their properties need a long time to recover. Internet connection is not yet back. The net surely helps businesses, but its negative sides of serving as a means of disseminating hateful messages to masses surely continues. It took me more than 15 days to air this observation due to the internet shutdown.

My take:
The assassination of celebrities is a major initial action that planners of attacks take. Even the First World War had the assassination of a member of a royal family as an immediate cause. Immediate causes could help ignite, however, in most cases bloodshed, civil wars, genocides or any other forms of public unrest happen as a result of carefully-planned plots. Strict proactive measures must be taken to prevent bloodshed and the massacre of innocent civilians of whatever background. The incidence of the assassination of Juvenile Habyarimana, the president who ruled Rwanda before the genocide, was planned to take place on March 23, 1994. Nonetheless, for their convenience the plotters of the genocide decided to execute it at midnight on the 6th of April 1994. Innocent Tutsis and moderate Hutus were wiped out afterwards. The then exiled Rwandan Patriotic Front, which had no means to  fire rockets from near the airport in Kigali, was held responsible for the shooting down of the plane carrying Habyarimana and his Brundian counterpart. This fabricated pretext was used to resume the genocide the world watched indifferently.
I was in Addis Ababa last October when a more or less similar riot to the current one broke out. At that time, it happened mostly in the outskirts. More than eighty people were reportedly killed in Oromia. By sheer coincidence, I followed the inception and immediate cause of the October violence from social media at night. The current one also started at night. I really feel deeply worried when by coincidence I happen to learn about such protests that are waged at night because the starting of the Rwandan genocide by midnight reverberates in my mind. As the October incidence began, I disclosed on Facebook that I was leaving for a week-long wokshop in Ghana. A friend messaged, "Are you leaving us for death?" The current one has grown quite intense and threatened everyone. It reminds one of the fable about the frog that thought her hideout of a pond was safe when a wildfire set a nearby jungle ablaze. The scope and scale of this week's youthful outrage was larger as it battered even downtown Addis Ababa. On the other hand, in October, security was loose, yet this week authorities are seen making it tighter than before! Who can tell where our country is heading? Leave alone the defenseless mass like me, celebrities, rich people and Ethiopian holders of other passports cannnot escape such sudden situations. Travel restrictions the COVID 19 pandemic caused made every Ethiopian national staying currently in their home country more vulnerable. We are all locked in to seek together workable solutions to the most pressing of problems this country of 3000 (or as some politicians claim, 100) years  is facing - ethnically-motivated plots, riots and attacks. Who knows how intense the next rage or riot may be?
I should take this opportunity to express my heartfelt grievances for all those Ethiopians of all backgrounds who lost their precious lives due to the well planned and ethnically motivated assaults. Not only this, I also really feel very sad for the plotters and their accomplices for going very cruel in as far as setting this trap for their country in an attempt to quench their lust for power and money!
Whether Ethiopians will open their hearts to the unifiers or cessationists in the upcoming elections remains the million dollar question!
P.S. The detailed reports that I heard on the days after the hateful and tragic occurrences from the informants of the Voice of America and Deutsche Welle from the butchering sites were really heartbreaking! People were singled out and attacked because of their ethnic and religious backgrounds. Lists of targets were made ready before the attacks. The attacks systematically orchestrated and made innocent civilians their victims! Meanwhile in Addis Ababa people organized themselves to defend their neighborhoods irrespective of their ethnic backgrounds.

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...