2022 ኦክቶበር 13, ሐሙስ

ባሕረኛ፣ ጋዜጠኛና ኃይማኖተኛው ዓለማየሁ

 


ዳሰሳ

በመዘምር ግርማ

ጥቅምት 3፣ 2015 ዓ.ም.

ራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት፣ ደብረብርሃን

 

‹‹የሕይወቴ ፈርጦች፣ እንደ መርከበኛ በባሕር፣ እንደ ጋዜጠኛ በምድር›› የሚል ርዕስ ያለውን መጽሐፍ በተጉለት ጉዞዬ ወቅት ከሳምንት በፊት ጀመርኩት፡፡ ማንበብ እንደጀመርኩ ከአጠገቤ የተቀመጡት መነኩሴም የራሳቸውን ዳዊት አውጥተው መድገም ጀመሩ፡፡ የተወሰነ ስናነብ ቆይተን ወግ ጀመርን፡፡ ምን እያነበብኩ እንደሆነ ለጠየቁኝ ጥያቄ መልስ ስሰጥ ‹‹እያንዳንዱ ሰው የራሱ ታሪክ አለው›› በማለት ወደ ሌሎች ወጎች አመሩ፡፡ በወለጋ በተለይም በደምቢዶሎ ስለሚያውቋቸው ትጉህ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችና የአሁኑ ሁኔታቸው፣ በጻድቃኔ ማርያም ገዳም ስላሳለፉት የዓመታት ጊዜ፣ ስለ ቤተክርስቲያን አስተዳደር ወዘተ.፡፡ እኔም ፀሐፊና የግል ቤተመጻሕፍት ስራ አራማጅ መሆኔን፣ በወቅቱም አዲስ የመጻሕፍት የውይይት ክበብ ለመክፈት እየሄድኩ መሆኑን አሳውቄ አውግተን ተለያየን፡፡  

የያዝኩት መጽሐፍ በቋንቋም ሆነ በይዘት ሳቢ መሆኑን በየገጹ ለመታዘብ ችያለሁ፡፡ ‹‹ከየት አምጥቶ ይህን አገላለጽ ጨመረው? ምን ቢያስብ እንዲህ ቃላትን አቀናጀ? ጽሑፍና ጸሐፊ ተገናኙ ማለት ይህ ነው!›› አስብሎኛል፡፡ በኪራይ ቤትና በገላማጭ አከራይ ፊት ተወልዶ ያደገው፣ ከልጅነቱ ጀምሮ በተደጋጋሚ ከሞት አፋፍ ያመለጠው፣ እንደ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ከባድ ሕይወትን ያሳለፈው ባለታሪኩ ደጋግሞ ‹ሰው የለኝማ› እያለ የበደሉን ሁኔታ ያወሳል፡፡ እኔማ የመጽሐፉ ርዕስ ስለምን ‹ሰው የለኝም› አልሆነም አልኩ፡፡ በስተመጨረሻ ሰው አገኘሁ የሚል ቃል አስፍሮና ያም ሰው የዋለለትን ውለታ ጠቃቅሶ ሳነብ እስኪ ይሁን ብዬ ዝምታን መርጫለሁ፡፡ ሳሲት ማምየለኝ ማርያም ለአስተርዮ ንግሥ

‹‹አንድ መልዳ ስሙን አበዛችው፣ አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው፣ አንዱ አገር ስትሄድ አማኑኤል አለችው፣ ሌላ አገር ስትሄድ ባለወልድ አለችው … ››

እንዲሉ በኦርቶዶክስ ውስጥ ስሙ የሚበዛው ኢየሱስ ከኃይማኖት ወደ ኃይማኖት ሲሄዱም አንዴ አምላክ፣ አንዴ ሰው፣ አንዴ ራስ ይሆናል የሚሉትን ነገር ቀድሜ ጫፍ ጫፉን ስለሰማሁ ዝም ብዬ ከማንበብ ሌላ የምሞግት እኔ ማነኝ!   ለአንባቢ ግርታን ለመቀነስ ዓለማየሁ ሰው አገኘሁ ያለው ኢየሱስን እንደ ግል አዳኙ ተቀብሎ ወይም ባጭሩ ጴንጤ ሆኖ ነው፡፡

መጽሐፉን ከገዛሁበት ከስምንት ዓመታት በፊት እስካሁን ባለው ጊዜ እንደ መርከበኛ የሚለውን ንዑስ ርዕስ ሳይ የሥነጽሑፍ ትምህርቴ ትዝ ብሎኝ ሳይሆን አይቀርም እውነት መርከበኛ ሆኖ ነው ወይንስ መርከበኛ ይመስል ማለቱ ይሆን ስል ቆይቻለሁ፡፡ ለካ ባህር ኃይልን ተቀላቅሎ ኖሯል፡፡ የወጣና የወረደበት የወታደር ሕይወት አንባቢን ቁጭ ብድግ ያደርጋል፡፡ የቀይ ባህርን ቀጣና ከሰላሙ እስከ ጦርነቱ ጊዜ ያስቃኘናል፡፡ የሳሲቱ መንገሽ ኪዳኔ ባጭር ስለተቀጨው ስለ ባህር ኃይል ሕይወቱ የነገረኝን ከዚህ መጽሐፍ አነበብኩት፡፡ ‹አይ ምፅዋ› ላይ ያነበብኩትንም አስታወሰኝ፡፡ ለአስመራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዋ የሚጽፍላት ደብዳቤ በግሏ ሳይሆን ከአምስት የዶርሟ ልጆች ጋር በምርጡ ደብዳቤ ዝግጅት እየተነበበ የአንደኝነትን ደረጃ ደጋግሞ መያዙን ከልጅቱ መስማቱ ሲጽፍ በቅርቡ በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ላውንጅ ከጀርባዬ ተቀምጠው ጓደኞቻቸው የጻፉላቸውን የፍቅር መልዕክቶች እያነበቡ የሚሳሳቁ ሁለት ሴቶችን አስታውሼ የአንዳንድ ሴቶች ፀባይ በሰላሳ ዓመትም ያልተለወጠ መሆኑን ታዘብኩ፡፡ ይህን ዓይነት ብዙ ታሪክ አለው፡፡ የጓደኛው የዘነበ ወላ ‹መልህቅ› እንዲሁ ሳቢ ሊሆን ስለሚችል ማንበቤ አይቀርም፤ መጽሐፍ ሲበዛብኝ ያነበብኩት እየመሰለኝ ተዘናጋሁ እንጂ!

የደራሲው ሕይወት በተደጋጋሚ ያልተጠበቁ አቅጣጨዎችን ሲይዝ እናያለን፡፡ ‹‹ጉልበቴ ላይ እያስደገፍኩ መጻፌ ቀረና ተሸከርካሪ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ›› ሲል የገለጸውን የጋዜጠኝነት ቅጥር ብዙ አይቶበታል፡፡ የፕሬስን ጓዳ ጎድጓዳ ባየው ልክ አስቃኝቶናል፡፡ ጋዜጠኝነትን ከፕሬስ ወደ እፎይታ ሲቀይር አለቃው ተስፋዬ ገብረአብ ነበር፡፡ ከዚያም ፊታቸውን ሲያዞሩበት ወደ ድርሰትና ትርጉም ሥራ ገብቶ መንፈሳዊ ጽሑፎች ላይ አተኮረ፡፡ ከዚያ በኋላ ያለውን ለማንበብ ለመንፈሳዊም ሆነ ኃይማኖታዊ ጽሑፍ ቅርብነት ወይም ቀናኢነትን ይጠይቃል፡፡ ይሁን እንጂ የተለያዩ የሥልጠና ገጠመኞቹ፣ የውጪ ጉዞ ታሪኮቹና ትዝብቶቹ ሁሉ አስተማሪና አዝናኝም ናቸው፡፡ ራይንሃርድ ቦንኬን ጨምሮ በዕምነቱ እንደ አርአያ የሚያያቸውን ሰባኪያን አግኝቷል፡፡ ዕምነትና ዕውቀት ወይም ልምድና ኃይማኖት የተደበላለቁበትን ይህን መጽሐፍ እንዳነብ ምክንያት የሆነኝ በቅርቡ በንባብ መስፋፋት ምክንያት ደራሲውን ጨምሮ 25 ሰዎች የተሳተፉበትን የዙም ስብሰባ በደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ጋባዥነት ስለተሳተፍኩ ነው፡፡ ምክንያት ሆነኝ፡፡ ያው አልፎ አልፎ ብቅ የሚል አጋጣሚ ነው፡፡ የአምባሳደር አማኑኤል አብርሃም የሕይወት ታሪክም እንዲሁ ነው፡፡ ሙሉ በሙሉ ክርስቲያናዊ የሆነ የሕይወት ታሪክ ግን አላነብም ብዬ መልሻለሁ፡፡ የትዕግስት አማት የጻፉት አንድ ምሳሌ ነው፡፡ በመሰረቱ የኢትዮጵያ ሥነጽሑፍም ሆነ ታሪክ የኦርቶዶክስ ተጽዕኖ በእጅጉ የጎላበት ስለሆነ ከዚያ ላመልጥ አልችልም፡፡ የተለያዩ ኃይማኖቶች መኖራቸው አይደንቀኝም፡፡ ሰው እንደ ፍላጎቱ ነው፡፡  በአጋጣሚ ግን ለማንበብ ትገደዳላችሁ፡፡ በ2007 ዓ.ም. የተረጎምኩትና ‹ሁቱትሲ› የሚል ርዕስ የሰጠሁት የሩዋንዳዊቷ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ መጽሐፍ ንዑስ ርዕሱ ‹በሩዋንዳው ጭርጨፋ ውስጥ እግዚአብሔር ሲገለጥልኝ› የሚል ነው፡፡ ክርስትናን እንደሚሰብክም እሙን ነው፡፡ ይህንን መጽሐፍ ስተረጉምና ለንባብ ሳቀርብ፣ ሲወደደልኝም የታዘበው አንድ መምህር ወዳጄ ‹የኛ አምላክ ባንተ ውስጥ አድሮ ተዓምር ሰራ› ብሎኛል፡፡ ያ ሌሎች ወንጌላውያን ጓደኞቹ ጸልየው ቀና እስኪሉ ድረስ ምግባቸው ላይ ጨው የመነስነሱን ሃሰብ ያነሳውና የተገበረው ባሕረኛ አሁን የኃይማኖት ሰው ሆኗል፡፡ ቆንጆ ፍለጋ የገባባት ቸርች አጥምዳ አስቀርታዋለች፡፡ ኦርቶዶክስንና አዲሲቱን ቤቱን በንጽጽር የሚያይ ብዕርም አለው፡፡ ያቺን ጣል ጣል፤ ይቺን ከፍ ከፍ፡፡ አንዲት እናት በዘመናቸው ስለታዘቧቸው ወጣቶች ሲነግሩኝ፣ ‹‹በጉብኝቱ ጊዜ ወጣቶቹ ሻርል ደጎልን ከፍ ከፍ፣ ጃንሆይን ጣል ጣል አደረጉ›› ያሉትን መሰል ብሎኛል፡፡ ዓለማየሁ 29 መጻሕፍት ያሉት ደራሲና ትጉህ የብዕር ሰው ነው፡፡ በብዕሩ ምን እንዳስተላለፈ ግን ሳናነብ ማወቅ አይቻለንም፡፡ ለሦስት ወራት ያህል ጊዜ ቀን ሙሉ ጻፍኩ ብሎ ስለመጀመሪያ ስራው ሳነብ እኔስ እንዲሁ አይደል ያደረኩት ብዬዋለሁ፡፡ ለመተዋወቂያ የሆነችኝን ይህችን መጽሐፉን ካነበብኩ ዘንዳ ወደፊት ሌሎች ዓለማዊ መጻሕፍት ካሉት ባነብ ደስታዬ ነው፡፡ እናንተም ይህንን መጽሐፍ እንድታነቡት ስጠቁም እንደ ሕይወት ታሪክ አፍቃሪነቴና ዳሳሽነቴ እንደምታተርፉበት በመተማመን ነው፡፡ የቋንቋውን ውበት ወዳጄ ይድነቃቸው ሰለሞን ለኔው ‹ያንተን ጽሑፎች እወዳቸዋለሁ፤ ምክንያቱን ግን እንጃ› እንደሚለኝ ሁሉ እኔም የዓለማየሁን አጻጻፍ የብዙ ነገሮች ጥርቅም ሳይሆን ባልቀረ ምክንያት እወደዋለሁ፡፡ አጫጭር ክፍሎቹም እንዳይሰለች ያደርጉታል፡፡  

 

2022 ኦክቶበር 12, ረቡዕ

ሳሲት በዕውቀት ጎዳና

 ሳሲት በዕውቀት ጎዳና

የጉዞ ማስታወሻ

በመዘምር ግርማ

ጥቅምት 2፣ 2015 ዓ.ም. 

 

ቅዳሜ መስከረም 28፣ 2015 ዓ.ም. ከደብረ ብርሃን ተነሳሁ፤ ወደ ሳሲትም ለመሄድ ወደ መናኸሪያ አቀናሁ፡፡ ‹የሕይወቴ ፈርጦች፣ እንደ መርከበኛ በባሕር፣ እንደ ጋዜጠኛ በምድር› የሚል ርዕስ ያለውን የዓለማየሁ ማሞን መጽሐፍ መኪና ውስጥ እያነበበብኩ ነው፡፡ ከሁለት ወራት በፊት መጽሐፍ እያነበበ እንዲሄድ ሃሳብ ያቀረብኩለትና መጽሐፍ ሰጥቼ የላክሁት ግሩም አስናቀ በሞላና በተጨናነቀ መኪና ውስጥ ስለተሳፈረ አለመቻሉን ስለነበረኝ ሰግቼ ነበር፡፡  የጃፓንን ምቹ የመንገደኞች ባቡሮች ሁኔታ አይቼም በእኛ ሁኔታ ተበሳጭቼ ነበር፡፡ ቀለል ባለው የተሳፋሪ ቁጥር ምክንያት ሳነብ የነበረበትን ሁኔታ በሚከተለው መልኩ ለፌስቡክ ህብረተሰብ አስተላለፍኩ፡፡ ‹‹የሁለት አንባቢያን ወግ - እኔ የአማርኛ የሕይወት ታሪክ መጽሐፍ ስከፍት እርሳቸው የግእዝ የፀሎት መጽሐፍ መዝሙረ-ዳዊት አወጡ፡፡ ጮክ ብለው እያነበቡ ነው፡፡ በፀጥታ አነባለሁ፡፡ ዘግይተው ምን እያነበብኩ እንደሆነ ጠየቁኝ፡፡ ስነግራቸው ‹እያንዳንዱ ሰው የሕይወት ታሪክ አለው› በማለት ጀመሩ፡፡ ለማናቸውም በሠላድንጋዩ መኪና ውስጥ እየተነበበ ነው፡፡ የዓለማየሁ ማሞ መጽሐፍ እጄ ከገባ ስምንት ዓመት ቢሆነውም በቅርቡ ደራሲውን ስለተዋወቅሁ አንስቼ ለማንበብ ቻልኩ፡፡›› መነኩሴው በጻድቃኔ ማርያም የሚኖሩ ሲሆኑ፤ ስለቤተክርስቲያን ህንጻና አስተዳደር ሁኔታ ብዙ አጫወቱኝ፡፡ እኔም ስለስራዬ ነገርኳቸው፡፡ በወለጋ መኖራቸውንና እዚያ ስላሉት ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ሁኔታም አውግተዋል፡፡

ሠላድንጋይ ከተማ ደርሼ ያየሁትን የልማት ጅማሮም ለወዳጆቼ በፎቶ አጅቤ አጋራሁ፡፡ እንዲህ በማለት ‹‹የሠላድንጋይ የልማት እርምጃ - ዛሬ በሞጃ ቆይታዬ ከሰዓት በፊት በዘመድ ጥየቃና የከተማዋን ለውጥ በማገናዘብ ቆይቻለሁ፡፡ በከተማዋ ያሉት ባንኮች ሰባት እየደረሱ ነው፡፡ የሞጃ ህዝብ ትጋት እየጨመረ መሆኑ በግልጽ ይታያል፡፡ በሰብዓዊ መብት፣ በጦርነት ትውስታ፣ በኪነጥበብና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂጃለሁ፡፡››

ከአፍታ ቆይታ በኋላ የሞጃ ዘነበወርቅ ባህል ቡድን አባል የሆነው ይበል ወርቁ ወደ ቤቱ ይዞኝ ሄደ፡፡ በዚያም ያገኘኋቸውን ግለሰብ ጉዳይ እንደሚከተለው በማስታወሻዬ ያዝኩ፡፡ ‹‹የፍትሕ ያለህ- ወይዘሮ አዛለች ይባላሉ፡፡ በሀሰት ሰው መግደል ወንጀል ተፈረደባቸው፡፡ ሞተች የተባለችውና በሀሰት የተመሰከረላት ጠፍታ ቆይታ ስለመጣች በይቅርታ ተፈቱ፡፡ ሲፈቱ ሀብት ንብረታቸው በሃራጅ ተሸጦ አገኙት፡፡ የአገራችን ፍትሕ ከምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ ማሳያ ናቸው፡፡ በሠላድንጋይ ከተማ አግኝቻቸዋለሁ፡፡ በቤታቸው ስደርስ ያገኘኋቸው ስልክ ሲደዋወሉ ነበር፡፡ የሚያወሩትም የሚኖሩበት የቀበሌ ቤት ኪራይ ስለመጨመሩና መክፈል እንደማይችሉ ነበር፡፡ ከእማወራነት ወደ ጉልበት ሰራተኛነት እንዳወረዷቸው ነገሩኝ፡፡ ሕዝቡ በሰልፍ ወጥቶ ትገደል ሲል እንዳልነበር አሁን ንፁህ ሲሆኑ ምንም አላላቸውም፡፡ ያሳዝኗችኋል፡፡ ያላናገራቸው ሚዲያ የለም፡፡ ያገኙት ነገር ያለመኖሩን ግን ነገሩኝ፡፡ እንዳናግራቸው ለጠቆመችኝ አንዲት ወጣት ምስጋና አቀርባለሁ፡፡ መፍትሔ ብንፈልግላቸው ጥሩ ነው፡፡ በተለይ የሕግ ባለሙያዎች፡፡››

ከወይዘሮ አዛለችና ከጌጤ ቤተሰብ ጋር ባለፈው ዓመት ስላሳለፉት የጦርነት ጊዜ ሁኔታም አውግተናል፡፡ እኔ ደብረብርሃን ሆኜ የጦርነት ስጋት ቢኖርብኝም እንደነሱ ለቀናት የመድፍ ጥይት ስላልተተኮሰብኝ የነሱን ታሪክ ፀጥ ብዬ ማዳመጥ ተገቢ ነው፡፡ ሠላድንጋይ ማርቆስ አካባቢ ከሚገኘው ከእርሳቸው ቤት ወጥቼ ወደ ከተማዋ ስወርድ አንድ ባለ ግርማ ሞገስ አባት አየሁ፡፡ ይህንንም ጻፍኩ፡፡ ‹‹የሞጃው መስፍን - ሠላድንጋይ ማርቆስ አካባቢ ጌጤን ጠይቄ ወደ ከተማው ስወርድ እኝህን አዛውንት አየሁ፡፡ በራቸው ላይ ተቀምጠው ሲያስቡ ሳይ ባላባት መሰሉኝ፡፡ ይህን ገልጬ ስለፎቶ ሳወራ ይበል አስፈቀደልኝ፡፡ የተሰማኝን ነገርኳቸው፡፡

‹ጃንሆይ እኮ ዘመዴ ናቸው› አሉኝ፡፡

ጃንሆይ አጤ ምኒልክ?› ስል ጠየኳቸው፡፡

‹አጤ ኃይለሥላሴ› በማለት መለሱ፡፡

ተገረምኩ፡፡ ያቺን ለመጀመሪያ ጊዜ ሳያቸው የነበሩባትን ቅጽበት መልሰን ባናገኝም ፎቶ አነሣናቸው፡፡ የታሪክ ዕውቀታቸውን ያካፍሉን ያዙ፡፡ ያነበቡት ብዙ መሆኑን ነገሩን፡፡ ከእርሳቸው በዕድሜ የሚበልጡም መኖራቸውን ነገሩን፡፡ እርሳቸውንም ሌሎቹንም የመጠየቁንና የመጻፉን ሥራ አብረውኝ ለሚዞሩት የሞጀ ዘነበወርቅ የባህል ቡድን ሰጥቼ መንገዴን ቀጠልኩ፡፡››

የሞጃና ወደራ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆነችውን ሙሉጌጥ ጎርፉን ከቤቷ ጠርተን በእረፍት ቀኗ ቅዳሜ ቢሮ ገባችልን፡፡ በቢሮዋም ስለጀመሩት የማስነበብ ስራና ወደፊት በመስሪያቤቱ ግቢ ለመክፈት ስለታሰበው አነስተኛ የንባብ ቦታ ነገረችን፡፡ የባህል ቡድኑ ተጠናክሮ የሚቀጥልበትንም ሁኔታ እንደሚነጋገሩ አሳወቁኝ፡፡ የባህል ቡድኑ አባላት ድጋፍ እንደሚፈልጉ፣ የአባላት መመናመን እንዳለባቸውና የቦታ እጥረት እንዳስቸገራቸው ነግረውኛል፡፡ የሥልጠናና ድጋፍ ዕድል ቢያገኙ እንደሚሹና አቅም ከተገኘ የባህል ቤት መክፈት እንደሚፈልጉ አጫውተውኛል፡፡ በቅርቡ ወረዳው በዞን ደረጃ የተከበረውን የዓለም የቱሪዝም ቀን እንዳስተናገደ አስታውሰው በወቅቱ የሸለሙኝንና መገኘት ባለመቻሌ ያልወሰድኩትን ጋቢ አበረከተችልኝ፡፡ ከምስጋናና ውለታ በዛብኝ ከሚል አስተያየት ጋር ተቀበልኩ፡፡

ወደ ሳሲት ከሰዓት አቀናሁ፡፡ ወዳጅ ዘመድን ጠያየቅሁ፡፡ ቅዳሜ ስለሆነ ደማምቃለች፡፡ የገበያ ቀን ከሌሎቹ በላይ የደመቀ ነው፡፡ በየቦታው የሚወራው ገንዘብ መሆኑ የመጀመሪያው ምልከታዬ ነበር፡፡ በየቤቱ እየዞሩ መጋበዝ (ጋ ይጠብቃል)፣ ቡና፣ አረቄና ቢራ መጋበዝ (ጋ ይጠብቃል) ስራዬ ሆኗል፡፡ እሁድ ጠዋት ቀበሌው ከወረዳ የመጡ ኃላፊዎች የሚሳተፉበት ስብሰባ መኖሩን በማሳወቁ ለከሰዓት ያሰብነው ስብሰባ ምን ያህል ሰው እንደሚመጣበት መጨነቃችን አልቀረም፡፡ ጋቢውን ለእናቴ አሳይቻት መቋጨት እንዳለበት ነገረችኝ፡፡ በእውቅ የተሰራ እንደሚመስልና ቆንጆ መሆኑን ነገረችኝ፡፡ ተቋጭቶ ወፍ እግር እንደሚሰፋ ስትነግረኝ እኔ እስከዛሬ ጋቢ ውሰድ ስባል ስለማልወስድ ነገሩ ብዙም አልገባኝም፡፡ ጋቢ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ስትነግረኝ አንድ ሰው ሲሞት አራት ጋቢ እንደሚያስፈልገው በማስረዳት ነው፡፡ ሁለቱ አስከሬኑ የሚሸፈንበት ሲሆን ሁለቱ የሚጋረድ ነው፡፡ በአሁኑ የገበያ ዋጋ አንድ ሰው ሲሞት አራት ጋቢ ማለትም የ6000 ብር ሀብት ያስፈልገዋል ማለት ነው፡፡

እሁድ ጠዋት የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር የሞጃና ወደራ አባላት ወርሃዊ ስብሰባቸውን በህብረት ሱቁ ደጅ ተቀምጠው ሲያካሂዱ አየኋቸው፡፡ ሰላምታ አቀረብኩላቸው፡፡ ንግግርም እንዳደርግ ጋብዘውኝ ተናገርኩ፡፡ ያለ ሥራ የተቀመጠውን የቀበሌውን አዳራሽ ተንከባክበው ለመያዝና ለስብሰባና ስራቸው ለማዋል ጥያቄ እየጠየቁ መሆኑን ነገሩኝ፡፡ አዳራሹንም ጎበኘሁት፡፡ በጣም ቆሽሿል፡፡ እኔም ምናልባት ለነሱ ቢሰጥ ለኛ የመጻሕፍት ውይይት ክበብም መወያያ ይፈቅዱልናል ብዬ አሰብኩ፡፡ በኋላ እንደተረዳሁት ግን ቀበሌው ራሱ የስብሰባ አዳራሽ ስለሌለው ይህንኑ መንከባከብ ይኖርበታል፡፡           

ለከሰዓቱ ስብሰባ ሰዎችን በአካል፣ በፌስቡክ፣ በስልክና በመልዕክት ስናስታውስ ቆየን፡፡ ሰዓቱም ሲደርስ እንደተሰጋው የቀበሌው ስብሰባ ስለነበር ሰዎች አልወጡም ነበር፡፡ ትምህርት ቤት ሄደን ተማሪዎች ስለመጡ ስራ ከመፍታት በማለት ‹ከገንዘብና ከዕውቀት› በሚል ርዕስ ክርክር አደረጉ፡፡ ይህን ርዕስ እኔም ያሰብኩት ሲሆን ተማሪዎች ሳልጠይቃቸው እሱኑ መምረጣቸው አስደስቶኛል፡፡ ስለ ሳሲት ቡክ ክለብ ሁለት ጊዜ በፌስቡክ ላይቭ ቃለመጠይቅ ያደረኩለት ዮርዳኖስ ግሩም በክርክሩ ተሳትፏል፡፡

መምህራንና ተጋባዥ እንግዶች በአጠቃላይ 22 ሰዎች ተገኝተው ውይይቱ ተጀመረ፡፡ በመጀመሪያ ስለ መጻሕፍት ውይይት ክበብ ምንነትና አሰራር የሳሲት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ-መምህር ፀጋ ገለጻ አደረጉ፡፡ በመቀጠል ግሩም አስናቀ ስለ ሳሲት ቡክ ክለብ አጀማመር ሃሳቡን አቀረበ፡፡ በሁለቱም ሃሳቦች ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡ ቀጥሎ ለዕለቱ መወያያ በተመረጠው ‹ብዕረኛው የሞጃ ልጅ› በተባለው የኔ መጽሐፍ ላይ ተወያያን፡፡ ለውይይቱ መነሻ ሃሳብ ያቀረበው ክብሩ ማሞ ሲሆን እርሱም ከንባቡ ያቀረበውን ከማጋራት በዘለለ ከእኔ ጋር በጥያቄና መልስ መልኩ ውይይት አድርጓል፡፡ ከዚያም ለቤቱ ክፍት ተደርጎ ተወያይተናል፡፡ በመቀጠል በዝግጅቱ ተሳታፊ የሆኑት አብዛኞቹ ተማሪዎች በቅርቡ የደብተር እገዛ ያገኙት በመሆናቸው ከሠው ለሠው በጎ አድራጎት ክበብ ተጠሪ  መምህር አበበ ሃሳብ ቀርቦ ለወደፊቱ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን የሚሰሩበትንና ራሳቸውን የሚደግፉበትን መንገድ እንዲሁም በትምህርታቸው ጎበዞች የሚሆኑበትን ጉዳይ ተነጋግረናል፡፡ ዕድሎች ውሱን በሆኑባቸው እንደ ሳሲት ያሉ ቦታዎች ተስፋ ያላቸው ልጆች መኖራቸውን ከተረዳሁባቸው ሁኔታዎች አንዱ በዕለቱ ተሳታፊ የነበረው ተማሪ ቶማስ ብርቅነህ በፈጠራ ስራ ከዞን አንደኛ፣ ከክልል ሦስተኛ ወጥቷል መባሉ ነው፡፡ የዕለቱ ዝግጅትም በአጠቃላይ አስደሳች በሆነ መልኩ የተጠናቀቀ ነበር፡፡

በማግስቱ ሰኞ ጠዋት ወደ ሳሲት ሙሉ ሳይክል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሄጄ ከአስተዳደሩና ከቋንቋ መምህራን ጋር እንግሊዝኛ ክበብ እንዲጀመር ሃሳብ አቅርቤ መተጋገዝ በምንችልባቸው ሁኔታዎች ላይ ተነጋግረናል፡፡ የተማርኩበትን ትምህርት ቤት መጎብኘቱ፣ ተማሪዎችን ማየቱ፣ ስለትምህርት ቤቱ አጠቃላይ ወቅታዊ ሁኔታ ማየቱ ለኔ ትልቅ ትርጉም አለው፡፡ ወደ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱም በመሄድ ተመሳሳይ ውይይት ከእንግሊዝኛ መምህር ጋር አድርጌያለሁ፡፡

ሰኞ ከሰዓት ብዙ ሰዎች ወደ ለቅሶ የሄዱበት ስለነበር ከተማው ለተወሰነ ጊዜ ጭር ብሎ ነበር፡፡ ሲመለሱ በዘመዶቼና ወዳጆቼ ጋር ስለምሰራቸው የበጎፈቃደኝነት ስራዎች በግል ለመወያየትና ሃሳብ ለመቀያየር ችያለሁ፡፡ ማክሰኞ ወደ ደብረብርሃን ተመለስኩ፡፡ የሳሲት ቡክ ክለብ ውይይት በየወሩ መጨረሻ እሁድ ስለሚቀጥል እገኛለሁ፡፡  

በአማራ ክልል ከተሞች ንባብን፣ ዕውቀትንና የበጎፈቃደኝነትን  የማስፋፋት ሙከራችን ላይ የሞጃ/ሳሲት የሦስት ቀናት ቆይታዬን አስመልክቼ የጻፍኩት ይህ ጽሑፍ ዋና ዋና ነጥቦችን የሚነካካ እንጂ ሁሉንም የሳሲት ትዝብቶቼን የያዘ አይደለም፡፡ 

 

 













2022 ሴፕቴምበር 25, እሑድ

My Sister’s Keeper?

 

My Sister’s Keeper?

A Story

Mezemir Girma

I think it could be the hundredth time we laughed on this matter. Shawel asks Gashahun to narrate to us that story. We shared each other’s funny stories from our respective villages and laughed heartily. The story of that old man who enjoyed bones that every household gave him, the tale of the old man with mental illness who put dead chicken from the market on fire on the road and ate them, and the tale of that man who sent his naughty son to study with clever Gashahun. Gashahun kept avoiding the boy because the boy disturbs him laughing at academic issues. Exponents or the little numbers or letters above the base number makes him laugh. “How do they make them such small? Won’t they tumble down?” he remarked. The boy also laughed at the double had as in the sentence “She had had dinner”. He even goes as far as canceling one of the hads from the textbook. Gashahun, nicknamed Gash, tells us how he avoided the boy, how the boy’s father got mad at him and how the boy ended up a truck driver. And we keep comparing our poverty with the boy who got rich fast.

Shawel asks him to tell us the story of one boy I admired after I heard his deed. Gashahun didn’t hesitate when he started the story as if we didn’t hear it at all. We expect the laughter our eyes meet his small eyes glittering in the sunny outdoor place we enjoyed at this beautiful neighborhood of Tebase in Debre Birhan. We were having our second glasses of Tela. I was getting tipsy faster than before.   

“In Dese,” he started the story by smiling. You know, as young people we enjoyed such stories about the relationships and encounters of opposite sexes. “In Agergizat, Dese, our area, there was a young man called Shambel, who was really bad mannered. He was well-known for his rudeness. People feared to talk to this infamous boy. Even people older than him didn’t want him to meddle in their businesses. He fought with his friends and he threw and hit older people with stones and run. No one wanted to be friends with him. He is known for doing strange things. One day he was walking with Ali, a friend who is his neighbor. Ali told him that he was spending the night with his sister because their parents went to a place far away to a funeral. That boy asked his friend to spend the night with them. Then, Ali agreed and they went home. Ali knew the naughty behavior of the boy, but he liked the idea because he feared to spend the night with his sister in the absence of his parents. While eating dinner, the guest’s eyes were moving here and there. He had something in mind.

They went to the bed and the two young men slept together. The girl slept alone in another bed. At midnight the guest stood up from the bed and started walking to the girl’s bed. Ali, the girl’s brother, was listening to every move of the boy. For this reason, immediately he switched the light on. The boy who was walking started snoring while he was standing. He acted as though he was sleepwalking. Afterwards, the other boy sent him out and the brother and sister spent the night peacefully.” We laughed more than before and discussed a few scenarios. As it was Saturday, we had to go home, spend a short time and meet in the evening to go to the night clubs.  

Many anecdotes he shares with us and we shared with him in turn. We heard them all because we spent many years wandering and telling such stories. We also share each other’s memories and anecdotes from the villages and small towns we came from. The story of the drunkard woman who pied standing like men, the strength of the bandit who defeated government soldiers who fought with him for three days in row and my description of how I wore as a green scarf as a ninth grader when I came to town as a country boy to learn for the first time.  Young university lecturers as we were, we spent our times walking, sitting at cafes and stores. Entertainment outweighed. Teaching, research, networking was at its infancy. The country was experimenting with the issue of university and we were enjoying the job opportunities we got. There was no one to mentor us. Our job was keeping the youth silent by giving degrees. We disliked the system, but we didn’t know how to curb Meles’ plans. We knew that after rigging the ballots and jailing opposition leaders the party was trying to silence the public by opening universities every here and there. Without proper mentorship and training, we had none other than chatting like that in our free time.

Years after my friends were transferred to universities in their places of birth as is the trend, I still remember the stories they used to tell me. They were stories of the common people. This one reverberates in my mind because I relate it to the phrase my sister’s keeper. I always feel sad at the abuse of the phrase when I hear it being misused by politicians and fake people. The people who are their sister’s killers and abusers misuse it. Those who kill their sisters in their sleep misuse it. By sister, I mean every girl and woman. As to me the real sister’s keeper is Ali, the young man of Dese who saved his sister from rape, isn’t he? There could be a few like him.

 


በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...