2022 ኦክቶበር 12, ረቡዕ

ሳሲት በዕውቀት ጎዳና

 ሳሲት በዕውቀት ጎዳና

የጉዞ ማስታወሻ

በመዘምር ግርማ

ጥቅምት 2፣ 2015 ዓ.ም. 

 

ቅዳሜ መስከረም 28፣ 2015 ዓ.ም. ከደብረ ብርሃን ተነሳሁ፤ ወደ ሳሲትም ለመሄድ ወደ መናኸሪያ አቀናሁ፡፡ ‹የሕይወቴ ፈርጦች፣ እንደ መርከበኛ በባሕር፣ እንደ ጋዜጠኛ በምድር› የሚል ርዕስ ያለውን የዓለማየሁ ማሞን መጽሐፍ መኪና ውስጥ እያነበበብኩ ነው፡፡ ከሁለት ወራት በፊት መጽሐፍ እያነበበ እንዲሄድ ሃሳብ ያቀረብኩለትና መጽሐፍ ሰጥቼ የላክሁት ግሩም አስናቀ በሞላና በተጨናነቀ መኪና ውስጥ ስለተሳፈረ አለመቻሉን ስለነበረኝ ሰግቼ ነበር፡፡  የጃፓንን ምቹ የመንገደኞች ባቡሮች ሁኔታ አይቼም በእኛ ሁኔታ ተበሳጭቼ ነበር፡፡ ቀለል ባለው የተሳፋሪ ቁጥር ምክንያት ሳነብ የነበረበትን ሁኔታ በሚከተለው መልኩ ለፌስቡክ ህብረተሰብ አስተላለፍኩ፡፡ ‹‹የሁለት አንባቢያን ወግ - እኔ የአማርኛ የሕይወት ታሪክ መጽሐፍ ስከፍት እርሳቸው የግእዝ የፀሎት መጽሐፍ መዝሙረ-ዳዊት አወጡ፡፡ ጮክ ብለው እያነበቡ ነው፡፡ በፀጥታ አነባለሁ፡፡ ዘግይተው ምን እያነበብኩ እንደሆነ ጠየቁኝ፡፡ ስነግራቸው ‹እያንዳንዱ ሰው የሕይወት ታሪክ አለው› በማለት ጀመሩ፡፡ ለማናቸውም በሠላድንጋዩ መኪና ውስጥ እየተነበበ ነው፡፡ የዓለማየሁ ማሞ መጽሐፍ እጄ ከገባ ስምንት ዓመት ቢሆነውም በቅርቡ ደራሲውን ስለተዋወቅሁ አንስቼ ለማንበብ ቻልኩ፡፡›› መነኩሴው በጻድቃኔ ማርያም የሚኖሩ ሲሆኑ፤ ስለቤተክርስቲያን ህንጻና አስተዳደር ሁኔታ ብዙ አጫወቱኝ፡፡ እኔም ስለስራዬ ነገርኳቸው፡፡ በወለጋ መኖራቸውንና እዚያ ስላሉት ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ሁኔታም አውግተዋል፡፡

ሠላድንጋይ ከተማ ደርሼ ያየሁትን የልማት ጅማሮም ለወዳጆቼ በፎቶ አጅቤ አጋራሁ፡፡ እንዲህ በማለት ‹‹የሠላድንጋይ የልማት እርምጃ - ዛሬ በሞጃ ቆይታዬ ከሰዓት በፊት በዘመድ ጥየቃና የከተማዋን ለውጥ በማገናዘብ ቆይቻለሁ፡፡ በከተማዋ ያሉት ባንኮች ሰባት እየደረሱ ነው፡፡ የሞጃ ህዝብ ትጋት እየጨመረ መሆኑ በግልጽ ይታያል፡፡ በሰብዓዊ መብት፣ በጦርነት ትውስታ፣ በኪነጥበብና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂጃለሁ፡፡››

ከአፍታ ቆይታ በኋላ የሞጃ ዘነበወርቅ ባህል ቡድን አባል የሆነው ይበል ወርቁ ወደ ቤቱ ይዞኝ ሄደ፡፡ በዚያም ያገኘኋቸውን ግለሰብ ጉዳይ እንደሚከተለው በማስታወሻዬ ያዝኩ፡፡ ‹‹የፍትሕ ያለህ- ወይዘሮ አዛለች ይባላሉ፡፡ በሀሰት ሰው መግደል ወንጀል ተፈረደባቸው፡፡ ሞተች የተባለችውና በሀሰት የተመሰከረላት ጠፍታ ቆይታ ስለመጣች በይቅርታ ተፈቱ፡፡ ሲፈቱ ሀብት ንብረታቸው በሃራጅ ተሸጦ አገኙት፡፡ የአገራችን ፍትሕ ከምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ ማሳያ ናቸው፡፡ በሠላድንጋይ ከተማ አግኝቻቸዋለሁ፡፡ በቤታቸው ስደርስ ያገኘኋቸው ስልክ ሲደዋወሉ ነበር፡፡ የሚያወሩትም የሚኖሩበት የቀበሌ ቤት ኪራይ ስለመጨመሩና መክፈል እንደማይችሉ ነበር፡፡ ከእማወራነት ወደ ጉልበት ሰራተኛነት እንዳወረዷቸው ነገሩኝ፡፡ ሕዝቡ በሰልፍ ወጥቶ ትገደል ሲል እንዳልነበር አሁን ንፁህ ሲሆኑ ምንም አላላቸውም፡፡ ያሳዝኗችኋል፡፡ ያላናገራቸው ሚዲያ የለም፡፡ ያገኙት ነገር ያለመኖሩን ግን ነገሩኝ፡፡ እንዳናግራቸው ለጠቆመችኝ አንዲት ወጣት ምስጋና አቀርባለሁ፡፡ መፍትሔ ብንፈልግላቸው ጥሩ ነው፡፡ በተለይ የሕግ ባለሙያዎች፡፡››

ከወይዘሮ አዛለችና ከጌጤ ቤተሰብ ጋር ባለፈው ዓመት ስላሳለፉት የጦርነት ጊዜ ሁኔታም አውግተናል፡፡ እኔ ደብረብርሃን ሆኜ የጦርነት ስጋት ቢኖርብኝም እንደነሱ ለቀናት የመድፍ ጥይት ስላልተተኮሰብኝ የነሱን ታሪክ ፀጥ ብዬ ማዳመጥ ተገቢ ነው፡፡ ሠላድንጋይ ማርቆስ አካባቢ ከሚገኘው ከእርሳቸው ቤት ወጥቼ ወደ ከተማዋ ስወርድ አንድ ባለ ግርማ ሞገስ አባት አየሁ፡፡ ይህንንም ጻፍኩ፡፡ ‹‹የሞጃው መስፍን - ሠላድንጋይ ማርቆስ አካባቢ ጌጤን ጠይቄ ወደ ከተማው ስወርድ እኝህን አዛውንት አየሁ፡፡ በራቸው ላይ ተቀምጠው ሲያስቡ ሳይ ባላባት መሰሉኝ፡፡ ይህን ገልጬ ስለፎቶ ሳወራ ይበል አስፈቀደልኝ፡፡ የተሰማኝን ነገርኳቸው፡፡

‹ጃንሆይ እኮ ዘመዴ ናቸው› አሉኝ፡፡

ጃንሆይ አጤ ምኒልክ?› ስል ጠየኳቸው፡፡

‹አጤ ኃይለሥላሴ› በማለት መለሱ፡፡

ተገረምኩ፡፡ ያቺን ለመጀመሪያ ጊዜ ሳያቸው የነበሩባትን ቅጽበት መልሰን ባናገኝም ፎቶ አነሣናቸው፡፡ የታሪክ ዕውቀታቸውን ያካፍሉን ያዙ፡፡ ያነበቡት ብዙ መሆኑን ነገሩን፡፡ ከእርሳቸው በዕድሜ የሚበልጡም መኖራቸውን ነገሩን፡፡ እርሳቸውንም ሌሎቹንም የመጠየቁንና የመጻፉን ሥራ አብረውኝ ለሚዞሩት የሞጀ ዘነበወርቅ የባህል ቡድን ሰጥቼ መንገዴን ቀጠልኩ፡፡››

የሞጃና ወደራ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆነችውን ሙሉጌጥ ጎርፉን ከቤቷ ጠርተን በእረፍት ቀኗ ቅዳሜ ቢሮ ገባችልን፡፡ በቢሮዋም ስለጀመሩት የማስነበብ ስራና ወደፊት በመስሪያቤቱ ግቢ ለመክፈት ስለታሰበው አነስተኛ የንባብ ቦታ ነገረችን፡፡ የባህል ቡድኑ ተጠናክሮ የሚቀጥልበትንም ሁኔታ እንደሚነጋገሩ አሳወቁኝ፡፡ የባህል ቡድኑ አባላት ድጋፍ እንደሚፈልጉ፣ የአባላት መመናመን እንዳለባቸውና የቦታ እጥረት እንዳስቸገራቸው ነግረውኛል፡፡ የሥልጠናና ድጋፍ ዕድል ቢያገኙ እንደሚሹና አቅም ከተገኘ የባህል ቤት መክፈት እንደሚፈልጉ አጫውተውኛል፡፡ በቅርቡ ወረዳው በዞን ደረጃ የተከበረውን የዓለም የቱሪዝም ቀን እንዳስተናገደ አስታውሰው በወቅቱ የሸለሙኝንና መገኘት ባለመቻሌ ያልወሰድኩትን ጋቢ አበረከተችልኝ፡፡ ከምስጋናና ውለታ በዛብኝ ከሚል አስተያየት ጋር ተቀበልኩ፡፡

ወደ ሳሲት ከሰዓት አቀናሁ፡፡ ወዳጅ ዘመድን ጠያየቅሁ፡፡ ቅዳሜ ስለሆነ ደማምቃለች፡፡ የገበያ ቀን ከሌሎቹ በላይ የደመቀ ነው፡፡ በየቦታው የሚወራው ገንዘብ መሆኑ የመጀመሪያው ምልከታዬ ነበር፡፡ በየቤቱ እየዞሩ መጋበዝ (ጋ ይጠብቃል)፣ ቡና፣ አረቄና ቢራ መጋበዝ (ጋ ይጠብቃል) ስራዬ ሆኗል፡፡ እሁድ ጠዋት ቀበሌው ከወረዳ የመጡ ኃላፊዎች የሚሳተፉበት ስብሰባ መኖሩን በማሳወቁ ለከሰዓት ያሰብነው ስብሰባ ምን ያህል ሰው እንደሚመጣበት መጨነቃችን አልቀረም፡፡ ጋቢውን ለእናቴ አሳይቻት መቋጨት እንዳለበት ነገረችኝ፡፡ በእውቅ የተሰራ እንደሚመስልና ቆንጆ መሆኑን ነገረችኝ፡፡ ተቋጭቶ ወፍ እግር እንደሚሰፋ ስትነግረኝ እኔ እስከዛሬ ጋቢ ውሰድ ስባል ስለማልወስድ ነገሩ ብዙም አልገባኝም፡፡ ጋቢ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ስትነግረኝ አንድ ሰው ሲሞት አራት ጋቢ እንደሚያስፈልገው በማስረዳት ነው፡፡ ሁለቱ አስከሬኑ የሚሸፈንበት ሲሆን ሁለቱ የሚጋረድ ነው፡፡ በአሁኑ የገበያ ዋጋ አንድ ሰው ሲሞት አራት ጋቢ ማለትም የ6000 ብር ሀብት ያስፈልገዋል ማለት ነው፡፡

እሁድ ጠዋት የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር የሞጃና ወደራ አባላት ወርሃዊ ስብሰባቸውን በህብረት ሱቁ ደጅ ተቀምጠው ሲያካሂዱ አየኋቸው፡፡ ሰላምታ አቀረብኩላቸው፡፡ ንግግርም እንዳደርግ ጋብዘውኝ ተናገርኩ፡፡ ያለ ሥራ የተቀመጠውን የቀበሌውን አዳራሽ ተንከባክበው ለመያዝና ለስብሰባና ስራቸው ለማዋል ጥያቄ እየጠየቁ መሆኑን ነገሩኝ፡፡ አዳራሹንም ጎበኘሁት፡፡ በጣም ቆሽሿል፡፡ እኔም ምናልባት ለነሱ ቢሰጥ ለኛ የመጻሕፍት ውይይት ክበብም መወያያ ይፈቅዱልናል ብዬ አሰብኩ፡፡ በኋላ እንደተረዳሁት ግን ቀበሌው ራሱ የስብሰባ አዳራሽ ስለሌለው ይህንኑ መንከባከብ ይኖርበታል፡፡           

ለከሰዓቱ ስብሰባ ሰዎችን በአካል፣ በፌስቡክ፣ በስልክና በመልዕክት ስናስታውስ ቆየን፡፡ ሰዓቱም ሲደርስ እንደተሰጋው የቀበሌው ስብሰባ ስለነበር ሰዎች አልወጡም ነበር፡፡ ትምህርት ቤት ሄደን ተማሪዎች ስለመጡ ስራ ከመፍታት በማለት ‹ከገንዘብና ከዕውቀት› በሚል ርዕስ ክርክር አደረጉ፡፡ ይህን ርዕስ እኔም ያሰብኩት ሲሆን ተማሪዎች ሳልጠይቃቸው እሱኑ መምረጣቸው አስደስቶኛል፡፡ ስለ ሳሲት ቡክ ክለብ ሁለት ጊዜ በፌስቡክ ላይቭ ቃለመጠይቅ ያደረኩለት ዮርዳኖስ ግሩም በክርክሩ ተሳትፏል፡፡

መምህራንና ተጋባዥ እንግዶች በአጠቃላይ 22 ሰዎች ተገኝተው ውይይቱ ተጀመረ፡፡ በመጀመሪያ ስለ መጻሕፍት ውይይት ክበብ ምንነትና አሰራር የሳሲት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ-መምህር ፀጋ ገለጻ አደረጉ፡፡ በመቀጠል ግሩም አስናቀ ስለ ሳሲት ቡክ ክለብ አጀማመር ሃሳቡን አቀረበ፡፡ በሁለቱም ሃሳቦች ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡ ቀጥሎ ለዕለቱ መወያያ በተመረጠው ‹ብዕረኛው የሞጃ ልጅ› በተባለው የኔ መጽሐፍ ላይ ተወያያን፡፡ ለውይይቱ መነሻ ሃሳብ ያቀረበው ክብሩ ማሞ ሲሆን እርሱም ከንባቡ ያቀረበውን ከማጋራት በዘለለ ከእኔ ጋር በጥያቄና መልስ መልኩ ውይይት አድርጓል፡፡ ከዚያም ለቤቱ ክፍት ተደርጎ ተወያይተናል፡፡ በመቀጠል በዝግጅቱ ተሳታፊ የሆኑት አብዛኞቹ ተማሪዎች በቅርቡ የደብተር እገዛ ያገኙት በመሆናቸው ከሠው ለሠው በጎ አድራጎት ክበብ ተጠሪ  መምህር አበበ ሃሳብ ቀርቦ ለወደፊቱ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን የሚሰሩበትንና ራሳቸውን የሚደግፉበትን መንገድ እንዲሁም በትምህርታቸው ጎበዞች የሚሆኑበትን ጉዳይ ተነጋግረናል፡፡ ዕድሎች ውሱን በሆኑባቸው እንደ ሳሲት ያሉ ቦታዎች ተስፋ ያላቸው ልጆች መኖራቸውን ከተረዳሁባቸው ሁኔታዎች አንዱ በዕለቱ ተሳታፊ የነበረው ተማሪ ቶማስ ብርቅነህ በፈጠራ ስራ ከዞን አንደኛ፣ ከክልል ሦስተኛ ወጥቷል መባሉ ነው፡፡ የዕለቱ ዝግጅትም በአጠቃላይ አስደሳች በሆነ መልኩ የተጠናቀቀ ነበር፡፡

በማግስቱ ሰኞ ጠዋት ወደ ሳሲት ሙሉ ሳይክል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሄጄ ከአስተዳደሩና ከቋንቋ መምህራን ጋር እንግሊዝኛ ክበብ እንዲጀመር ሃሳብ አቅርቤ መተጋገዝ በምንችልባቸው ሁኔታዎች ላይ ተነጋግረናል፡፡ የተማርኩበትን ትምህርት ቤት መጎብኘቱ፣ ተማሪዎችን ማየቱ፣ ስለትምህርት ቤቱ አጠቃላይ ወቅታዊ ሁኔታ ማየቱ ለኔ ትልቅ ትርጉም አለው፡፡ ወደ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱም በመሄድ ተመሳሳይ ውይይት ከእንግሊዝኛ መምህር ጋር አድርጌያለሁ፡፡

ሰኞ ከሰዓት ብዙ ሰዎች ወደ ለቅሶ የሄዱበት ስለነበር ከተማው ለተወሰነ ጊዜ ጭር ብሎ ነበር፡፡ ሲመለሱ በዘመዶቼና ወዳጆቼ ጋር ስለምሰራቸው የበጎፈቃደኝነት ስራዎች በግል ለመወያየትና ሃሳብ ለመቀያየር ችያለሁ፡፡ ማክሰኞ ወደ ደብረብርሃን ተመለስኩ፡፡ የሳሲት ቡክ ክለብ ውይይት በየወሩ መጨረሻ እሁድ ስለሚቀጥል እገኛለሁ፡፡  

በአማራ ክልል ከተሞች ንባብን፣ ዕውቀትንና የበጎፈቃደኝነትን  የማስፋፋት ሙከራችን ላይ የሞጃ/ሳሲት የሦስት ቀናት ቆይታዬን አስመልክቼ የጻፍኩት ይህ ጽሑፍ ዋና ዋና ነጥቦችን የሚነካካ እንጂ ሁሉንም የሳሲት ትዝብቶቼን የያዘ አይደለም፡፡ 

 

 













2022 ሴፕቴምበር 25, እሑድ

My Sister’s Keeper?

 

My Sister’s Keeper?

A Story

Mezemir Girma

I think it could be the hundredth time we laughed on this matter. Shawel asks Gashahun to narrate to us that story. We shared each other’s funny stories from our respective villages and laughed heartily. The story of that old man who enjoyed bones that every household gave him, the tale of the old man with mental illness who put dead chicken from the market on fire on the road and ate them, and the tale of that man who sent his naughty son to study with clever Gashahun. Gashahun kept avoiding the boy because the boy disturbs him laughing at academic issues. Exponents or the little numbers or letters above the base number makes him laugh. “How do they make them such small? Won’t they tumble down?” he remarked. The boy also laughed at the double had as in the sentence “She had had dinner”. He even goes as far as canceling one of the hads from the textbook. Gashahun, nicknamed Gash, tells us how he avoided the boy, how the boy’s father got mad at him and how the boy ended up a truck driver. And we keep comparing our poverty with the boy who got rich fast.

Shawel asks him to tell us the story of one boy I admired after I heard his deed. Gashahun didn’t hesitate when he started the story as if we didn’t hear it at all. We expect the laughter our eyes meet his small eyes glittering in the sunny outdoor place we enjoyed at this beautiful neighborhood of Tebase in Debre Birhan. We were having our second glasses of Tela. I was getting tipsy faster than before.   

“In Dese,” he started the story by smiling. You know, as young people we enjoyed such stories about the relationships and encounters of opposite sexes. “In Agergizat, Dese, our area, there was a young man called Shambel, who was really bad mannered. He was well-known for his rudeness. People feared to talk to this infamous boy. Even people older than him didn’t want him to meddle in their businesses. He fought with his friends and he threw and hit older people with stones and run. No one wanted to be friends with him. He is known for doing strange things. One day he was walking with Ali, a friend who is his neighbor. Ali told him that he was spending the night with his sister because their parents went to a place far away to a funeral. That boy asked his friend to spend the night with them. Then, Ali agreed and they went home. Ali knew the naughty behavior of the boy, but he liked the idea because he feared to spend the night with his sister in the absence of his parents. While eating dinner, the guest’s eyes were moving here and there. He had something in mind.

They went to the bed and the two young men slept together. The girl slept alone in another bed. At midnight the guest stood up from the bed and started walking to the girl’s bed. Ali, the girl’s brother, was listening to every move of the boy. For this reason, immediately he switched the light on. The boy who was walking started snoring while he was standing. He acted as though he was sleepwalking. Afterwards, the other boy sent him out and the brother and sister spent the night peacefully.” We laughed more than before and discussed a few scenarios. As it was Saturday, we had to go home, spend a short time and meet in the evening to go to the night clubs.  

Many anecdotes he shares with us and we shared with him in turn. We heard them all because we spent many years wandering and telling such stories. We also share each other’s memories and anecdotes from the villages and small towns we came from. The story of the drunkard woman who pied standing like men, the strength of the bandit who defeated government soldiers who fought with him for three days in row and my description of how I wore as a green scarf as a ninth grader when I came to town as a country boy to learn for the first time.  Young university lecturers as we were, we spent our times walking, sitting at cafes and stores. Entertainment outweighed. Teaching, research, networking was at its infancy. The country was experimenting with the issue of university and we were enjoying the job opportunities we got. There was no one to mentor us. Our job was keeping the youth silent by giving degrees. We disliked the system, but we didn’t know how to curb Meles’ plans. We knew that after rigging the ballots and jailing opposition leaders the party was trying to silence the public by opening universities every here and there. Without proper mentorship and training, we had none other than chatting like that in our free time.

Years after my friends were transferred to universities in their places of birth as is the trend, I still remember the stories they used to tell me. They were stories of the common people. This one reverberates in my mind because I relate it to the phrase my sister’s keeper. I always feel sad at the abuse of the phrase when I hear it being misused by politicians and fake people. The people who are their sister’s killers and abusers misuse it. Those who kill their sisters in their sleep misuse it. By sister, I mean every girl and woman. As to me the real sister’s keeper is Ali, the young man of Dese who saved his sister from rape, isn’t he? There could be a few like him.

 


2022 ሴፕቴምበር 19, ሰኞ

አሻራ ከአዲስ አበባ እስከ አይኦዋ፣ አሜሪካ

ተጻፈ ሰኞ 9/1/2015 ዓ.ም. ማለዳ

(ተሳታፊዎች መልሰው ካነበቡት በኋላ የተስተካከለው ቅጂ)

መዘምር ግርማ፣ ደብረብርሃን

 


ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ በአይኦዋ ዩኒቨርሲቲ የአስር ሳምንታት ቆይታ ለማድረግ ወደ አሜሪካ መሄዱን ከማህበራዊ ሚዲያ አንብበናል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ ደራስያንን ከመላው ዓለም አወዳድሮና መርጦ መርሐግብር የማሰናዳት ልምድ አለው፡፡ እንዳለጌታ ከበደ በኢምባሲው በኩል ከአገር ውስጥ እንዲሁም ከዚያ በኋላ በውጪ በተደረገ ውድድር አሸንፎ ነው ወደዚያ ያቀናው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ትናንት ደራሲው በቴሌግራም መልዕክት ላከልኝ፡፡

በመልዕክቱም ‹‹መዘምር ከቻልክ ተሳተፍ፡፡ በተለይ ስለ ቡክ ባንካችን ›› በማለት የዙም ሊንኩን አያይዞ ነበር፡፡

‹‹በደስታ›› በማለት መለስኩ፡፡

ሰዓቱን 6:00 PM PST የሚለውን ወደ ኢትዮጵያ ሠዓት ስቀይረው ሌሊት 10፡00 ይላል፡፡ እሱም ሌሊት ላይ መሆኑን አላወቀም ነበርና ደንግጦ ‹‹እንቅልፍህን አጥተህ›› ሲል መለሰልኝ፡፡

 ‹‹ችግር የለውም፡፡ ብዙ ጊዜ ማላጅ ነኝ›› በማለት አስከተልኩ፡፡

‹‹ዛጎል የመጻሕፍት ባንክን ይደግፋሉና ታስፈልገናለህ፡፡ መጻሕፍት የሚሰጠን እያጣን ነው፡፡›› የሚል ሃሳብ ጨመረ፡፡

ዛጎል ቡክ ባንክ ከተመሰረተ ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ የሆነው ሲሆን ከበጎ አድራጊዎች የሚያገኛቸውን መጻሕፍት የንባብ ባህል ይስፋፋ ዘንድ ለማገዝ በመላው ኢትዮጵያ ለሚገኙ አብያተመጻሕፍት ያከፋፍላል፡፡ እስካሁንም ከ35 ሺህ በላይ መጻሕፍትን አዳርሷል፡፡ የተሻለ እንዲሰራ ከተፈለገ የሌሎችም ድጋፍ ስለሚያስፈለገው በባንኩ ዓላማ አፍቃሪዎች የተዘጋጀውን ይህን ዝግጅት ለመታደም በመጋበዜ ዕድለኝነት ተሰማኝ፡፡   

ከዚህ ምልልስና ሌሎች ስራዎች በኋላ ስተኛ ከሌሊቱ 7፡00 አልፎ ነበር፡፡ አላርም ሞልቼ የነበረ ቢሆንም ቢጠራም አጥፍቼው ሳይሆን አይቀርም አንድ ሰዓት አሳልፌ 11፡00 ላይ ነቃሁ፡፡ ወዲያውኑ በቁጭት እስኪ ካላለቀ በማለት ወደ ዙም ስብሰባው ገባሁ፡፡ ደግነቱ አላለቀም ነበር፡፡ ተሳታፊዎቹ ውይይቱን አጧጡፈውታል፡፡ አንባብያን መሆናቸው ያስታውቃል፡፡ በዕውቀት ኃይል የሚያምኑና አንዳንዶቹም የጽሑፍ ዝንባሌ ያላቸው ናቸው፡፡ ለወገን አሳቢዎችና ትሁቶች መሆናቸውን ታዘብኩ፡፡ የተነጋገርነው ብዙና ሰፊ ጉዳይ ላይ ቢሆንም ዋና ዋናውን በአጭሩ ታነቡት፣ እንደሁም ለዛጎል ቡክ ባንክም ሆነ ለሌላ የመጻሕፍት ፍላጎት ላለው አካል እገዛ ለማድረግ ትነሳሱበት ዘንድ ከያዝኩት ማስታወሻ በዚህ መልኩ አስፍሬያለሁ፡፡ መልካም የንባብና የማሰላሰል ቆይታ!

የዙም ስብሰባው መሪ ያሬድ ልሣነወርቅ ናቸው፡፡ በልጅነታቸው መንዝ እንደተማሩ በጨዋታ በጨዋታ ነግረውናል፡፡ የደራሲ ከበደ ሚካኤልን ግጥሞች ደጋግመው በማንሳት ለንግግሮቻቸው ማሳመሪያ ይጠቀማሉ፡፡ ከመጽሐፍ እየጠቀሰ የሚያወራ ሰው መስማት መታደል ነው መቼስ! የሰሩት ንባብና ዕውቀት ተኮር ስራ በእርሳቸውም ሆነ በሌሎች ተገልጧል፡፡ በሚኖሩበት ካውንቲ የአፍሪካ መጽሐፍ የለም፡፡ የአሜሪካ ብቻ ነው፡፡ እንዲኖር የሚመለከታቸውን አናግረዋል፡፡ ፊርማም ስለማሰባሰብ አስበዋል፡፡ በኢትዮጵያም መሰራት ስላለበት ስራ ሁሉ አገርቤት ያለነውን ‹‹ምሩን፣ መንገዱን አሳዩን›› ሲሉ ተማጽነዋል፡፡ እኛ ለብቻችን የምናደርገው መፍጨርጨርም ሰፋ እንዲል በማሰብ ‹‹አንድን መሪ ትልቁ ሊያደርገው የሚችለው ሊተካው የሚችለው ሰው ሲኖር ነው›› በማለት ተተኪ እንድናፈራ አበረታተውናል፡፡ የዘላቂነት ጥያቄ ለአሁኑ ዘመን አዳዲስ ሃሳብ ተግባሪዎች!

የበጎ አድራጎት ስራ አስተባበሪው ያሬድ አሜሪካ ቢሩም ኢትዮጵያዊ ዜግነታቸውን ጠብቀው ኖረዋል፡፡ ለዚህም የሚጠቅሱት በልጅነታቸው ያነበቡትንና የተማሩትን ነው፡፡ እኔ ከደብረብርሃን መሆኔን ሲያውቁ የአገር ሰዎችን እነ ፊታውራሪ ቅጣው አዘነና ልጆቻቸውን መዓዛ ቅጣውንና ፕሮፌሰር ዳንኤል ቅጣውን ጠቅሰውልኛል፡፡

‹‹ኃይለማርያም ማሞ የጦሩ ገበሬ፣

ፈረሱን እንደሰው አስታጠቀው ሱሬ››

የሚለውን ግጥምም በመጥቀስ የዛሬው ትውልድም እንደነ ልጅ ኃይለማርያም ማሞ ሁሉ በነገው ተተኪ ትውልድ የሚወሳ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸው አበረታተውናል፡፡ ብዙ የቤት ስራ አለብን አትሉልኝም!

‹‹‹ዱቢን ሃቡልቱ››  - ይደር ይቆይ - ይላል ያገሬ ኦሮሞ ሲተርት›› የሚሉት አቶ ያሬድ አጋፋሪነት ለወደፊቱም ተስፋ የሰነቀ ነው፡፡ ይህ ውይይት በየስቴቱ መሆን እንዳለበት ሃሳብ ተነስቷል፡፡ እውነት ነው፡፡ የአንድ ስቴት ሐበሻ በአንድ የኢትዮጵያ ዞን ውስጥ ያሉ አብያተመጻሕፍትን በመጻሕፍት ሊሞላ ይችላል፡፡ መጻሕፍትን ከአሜሪካም በጥንቃቄ መርጦ የማምጣት ስራ ከተሰራ ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡ ‹‹ጎፈሬ የሚኖረው የራስ ቅል ሲኖር ነው››ን በመሰሉ አባባሎች በመጠቀም መሰረቱ መረሳት እንደሌለበት የሚያስታውሱት አቶ ያሬድ እስከዛሬም በዛጎል ቡክ ክለብ በኩል መደርደሪያ በመግዛት፣ ለታዋቂው ደራሲ ሣህለሥላሴ ድጋፍ በማድረግ ማገዛቸውን ደራሲ እንዳለጌታ መስክሯል፡፡ እዚህ ላይ ሣህለሥላሴን የመሰለ ታዋቂ ደራሲና ተርጓሚ፣ በአፍሪካን ራይተርስ ሲሪስ ሳይቀር ያሳተሙ፣ የተማሩ ሰው የሚታገዙበት መንገድ አለመዘርጋታችን እንደ አገር ትልቅ ጉዳይ ነው፡፡ አሁንም ቢታሰብበት መልካም ነው፡፡ አንድ ድርጅትን ቢያማክሩ፣ ዕውቅና ቢሰጣቸው፣ ወይም በሆነ መንገድ ማበረታቻ ቢያገኙ መልካም ነው፡፡ የሚቀርብንና የምናፍረው እኛው የዛሬ ትውልድ አባላትና መሪዎች ነን!

ደርሰህ የተባሉ ተሳታፊ እንዲህ አሉን፡፡ ‹‹አባቴ የጳውሎስ ኞኞን ‹አንድ ጥያቄ አለኝ› በዚያ እልም ባለ ገጠር እያስነበቡ ከእርሳቸው የተሻለ ኑሮ እንድኖር አስችለውኛል፡፡ እኔም ለልጆቼ የተቻለኝን አድርጌያለሁ፡፡ አገራችን ይህ ሁሉ ችግር የሚደርስባት በማቴሪያል ላይ እንጂ በዕውቀት ላይ ስላልተሰራ ነው፡፡ ይህ ጅምር ትልቅ ተስፋ ነው፡፡››  

ዶክተር እንዳለጌታ ከበደና ሌሎቹም ተሳታፊዎች እኔ ከመግባቴ በፊት የተናገሩት እንዳለ ሆኖ እንዳለጌታ ስለ ቡክ ባንኩ፣ ስለ ንባብ፣ ስለ ትውልዱ ሃሳቡን አጋርቶናል፡፡

‹‹ለዕውቀት ለሥራ ግሎ ለመነሣት

ቆስቋሽ ይፈልጋል የሰው ልጅ እንደ እሳት፣›› የሚል የደራሲ ከበደ ሚካኤልን ግጥም ጠቅሶ ለስራ መትጋት እንዳለብን አውስቷል፡፡ ንግግሩ ሁሉ ትህትና የተሞላበትና አነቃቂ ነው፡፡ በቀናነቱ የማይስማማ የለም፡፡ እስኪ ከዚህ ትህትናውና ከበጎ አድራጎት ስራው ለመማር የማይፈልግ ማነው? ደራሲው ስለ አድራጎታችን ማሰብ እንዳለብን አውስቷል፡፡ አገሩ ሁሉ የማይረባ ነገር ይጽፋል የምንለው እኛ እያነበብንላቸው መሆኑን እንዳንዘነጋ አውስቶ መርጦ ማንበብም አስፈላጊ ነው ብሏል፡፡ ከስራችንም ውስጥ ምን ይቅደም ብለን ማሰብ እንዳለብን ጠቅሶ እንደግለሰብም ሆነ እንደአገር መቅደም ካለባቸው አንዱ ንባብ መሆኑን አስታውሷል፡፡

እንዳለጌታ ዛጎል ቡክ ባንክ በደራሲ ዮርዳኖስ አልማዝ ሠይፉ በኩል በደቡብ አፍሪካ ላሉና የአገራቸውን መጻሕፍት ለማያገኙ ልጆች መጻሕፍት መርዳቱን ነግሮናል፡፡ ውጪ ያሉ ልጆች እንዲያነቡ አገር ውስጥ ባሉ ደራስያን የተጻፉትን እንደ አትሌቱ ያሉ መጻሕፍትን ማቅረብ እንደሚቻልና መተጋገዝ እንደሚኖርብን ገልጧል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ መጽሐፍ በማጣት ጨለማ ውስጥ የሚኖር አይኖርም የሚል እምነት አለው፡፡ ለዛጎል ቡክ ባንክ እገዛ ድርጉልኝ ወይም ስጡኝ ማለት እንደማይፈልግና የፈለገ ይምጣና ይስጠን የሚል ሃሳብ እንዳለው ገልጾ ይህ ሃሳቡ መቀየር እንዳለበት ከጓደኞቹ ጋር በሚያደርገው ምክክርና እሱም በተለመከተው መሰረት እያመነ መምጣቱን ነግሮናል፡፡

በአዲስ አበባ በዛጎል ቡክ ባንክ የሚሰራውን ስራ የዛሬው የዙም ስብሰባው ተሳታፊዎች ያውቃሉ፡፡ ለማወቃቸውን የዩቱብ ቻነላቸው ምክንያት እንደሆናቸው ብዙዎች ተናግረዋል፡፡ አሜሪካ ሆነውም አገራቸው እንዳሉ እንዲሰማቸው አድርጓቿል- እንደ ገለጻቸው፡፡ 

ደራሲ ዓለማየሁ ማሞ 29 መጻሕፍት የደረሱ መሆናቸው ተገልጾ እንዲናገሩ ተጋበዙ፡፡ እርሳቸውም ከባህር ኃይል ጀምሮ የነበራቸውን የንባብ ልምድ አጋሩን፡፡ የመጻፍና የማሳተም ስራቸውን አስቃኙን፡፡ ሌሎች ሰዎች እንዲጽፉ የሚያደርጉትን ድጋፍም እንዲሁ፡፡ ከዛጎልም ጋር የሚያያይዛቸው አንድ ሁነኛ ጉዳይ አለ፡፡ ዛጎል ለአብያተመጻሕፍት ለመተዋወቂያ ከሚሰጠው 200 መጽሐፍ በኋላ ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡት 981 መጻሕፍትን ይጨምራል፡፡ ይህም ቁጥር እንግሊዞች ከአፄ ቴዎድሮስ ከመቅደላ የዘፏቸው መጻሕፍት ቁጥር ነው፡፡ እናም ደራሲ ዓለማየሁ ማሞ የሚረዱኝና የሚረዱኝ (ረ ይጠብቃል) ከሚሏቸው ጥቂትና ሁነኛ ወዳጆቻቸው ጋር በመሆን በአንድ ዓመት ጊዜ አገር ቤት የመታተም ዕድል ካገኙት መጻሕፍታቸው 2062 የሚደርሱትን ለዛጎል አበርክተዋል፡፡ ከሰጡት ወደፊት የሚሰጡት እንደሚበዛ ስለነገሩን እናመሰግናለን!

ፋሲል ስዩም ገሠሠ ከፀሐይ አሳታሚ ጋር በመሆን በአሜሪካ የመጻሕፍት ውይይት ክበቦችን አቋቁሟል፡፡ ልጆችም ሆኑ ትልልቆች በየዕድሜያቸው እያነበቡ እንዲወያዩ ያደርጋል፡፡ በተግባር የሰራቸውንና ያገኛቸውን ልምዶች አጋርቶናል፡፡ እንደ ፋሲል ሁሉ ተሰብሳቢዎቹ በየሙያቸው፣ በገንዘባቸውና በጊዜያቸው አገራቸውን ለማገልገል የሚተጉ ናቸው፡፡

የኦንላይን ፒዲኤፍ ንባብን አስመልክቶም የተናገሩ አሉ፡፡ አንዳንድ መጽሐፍ በኢሜል ስለመላክ ተነጋግረናል፡፡ አንድ ተሳታፊ 117 ሚሊየን ብንሆንም ኢትዮጵያን የሚያሻግሯት ጥቂት እንደሆኑ በመግለጽ የግለሰቦችን ሚና ጠቀሜታ ያዩበትን መንገድ አስረድተውናል፡፡ ከአራቱ መጻሕፍቷ ከእያንዳንዳቸው 100 ቅጂ ቃል የገባችው ደራሲት እመቤት መንግስቱም ተሳታፊ ነበረች፡፡ ደራስያን በአመዛኙ በድርሰት ላይ እንጂ በአካዳሚው ዘርፍ በመማርና በማደግ ላይ በማያተኩሩበት ጊዜ እስከ ፒኤችዲ ድረስ መሄዱን ጠቅሰው ዶክተር እንዳለን ያደነቁ ተሳታፊም ነበሩ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማይጠቅም መጽሐፍ እንዳናመጣና መጽሐፍ ስንመርጥ እንድንጠነቀቅ መክረውናል ያሉም እንዲሁ፡፡ ያላነበብነውን መጽሐፍ አንሰጥም የሚለው የእንዳለጌታና የዛጎል ቡክ ባንክ ሃሰብ ሲታከልበት የመጽሐፍ ምርጫ ጉዳይ ትልቅ ቦታ እንዳለው እንገነዘባለን፡፡ 


 

እኔም በተሰጠኝ ዕድል ንግግር አድርጌያለሁ፡፡ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደን በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል የጥበብ ምሽት ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተዋወኩት፣ ከዚያም ለሌላ ጥናታዊ ጉባኤ ወደ ከተማችን እንደመጣ ተገናኝተን ቤተመጻሕፍቴን (ራስ አበበ አረጋይን) አይቶ እንደተወያየንና እንዳበረታታኝ ገለጽኩ፡፡ በ2013 ዓ.ም. በዛጎል ቡክ ባንክ 200 መጻሕፍት እንደተበረከተልንና የስጦታውን ሁኔታም በሦስተኛው መጽሐፌ ‹‹ብዕረኛው የሞጃ ልጅ›› ጽፌ ማካተቴን፣ ያንንም ጽሑፍ በዋልያ መጻሕፍት መደብር የቅዳሜ ዝግጅት ላይ ተገኝቼ እንዳነብ እንዳደረገኝ ገለጽኩ፡፡ ከዚያ ካቀረብኩት ጽሑፍም ሃሳቦችን በመዋስ ከተናገርኩት አንዱ የሚከተለው ነው፡፡ በቤተመጻሕፍታችን አንዲት መጽሐፍ እንኳን ትውልድን በማስተማር ረገድ ያላትን ጥቅም በቤተመጻሕፍታችን በምትገኝ በአንዲት የ11ኛና 12ኛ ክፍል የሒሳብ አጋዥ መጽሐፍ ለሰባት ዓመታት በየቀኑ በሚባል ሁኔታ መነበብና የብዙዎችን ሕይወት የመቀየር ሚና አስረዳሁ፡፡ ያለብንን የመጽሐፍ እጥረት፣ ካሉን መጻሕፍት 20 በመቶው ማለትም 600 መጻሕፍት ብቻ በሦስት አገር በቀል ድርጅቶች ድጋፍ መገኘታቸውን፣ ሌሎቹ እኔ ከመጻሕፍቴ ሽያጭና ከራሴ ገንዘብ ያሟላኋቸው መሆናቸውን፣ የአገር ውስጥ መጽሐፍ ካልሆነ እንደማይነበብ ጨምሬ ዋና ዋና ሃሳቦችን አቀረብኩ፡፡ እነዚህም የራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍትን የሰባት ዓመታት ጉዞና የግል ቤተመጻሕፍት አሰራርና ይዞታ የመሳሰሉት ናቸው፡፡

ስለመጻሕፍት ፍላጎታችንን ከተናገርኩ በኋላ በአፍመፍቻ ቋንቋ ስለመማር ሃሳብ ያቀረቡ ተሳታፊም ነበሩ፡፡ እርሳቸውም እነ ፕሮፌሰር መሳይ ከበደ በደርግ ጊዜ ይህን ሃሳብ ሲያቀርቡ እንደተሳቀባቸው ገልጸው የዓለም አገሮች ግን አብዛኞቹ በቋንቋቸው እንደሚማሩ ተናግረዋል፡፡ በራሱ ቋንቋ ያልተማረ አያድግም፡፡ እንኳን ማደግ መሰረታዊ ፍላጎቱንም አያሟላም፡፡ መፈልሰፍና ማወቅ የሚቻለው በራሳችን ቋንቋ ስንማር ነው ብለውናል፡፡

ዶክተር እንዳለጌታ ከበደም ስለስራዎቼ በመናገር አስተዋውቆኛል፡፡ በዘር ማጥፋት ላይ የሚያተኩረውን ሌፍተ ቱ ቴል የተባለውን የኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛን መጽሐፍ ሁቱትሲ በሚል ርዕስ መተርጎሜንና ማሳተሜን ገለጸላቸው፡፡ በዚህ ሳልወሰን ወደ ኦሮምኛ አስተርጉሜ ማሳተሜንም በማመስገን አስተዋወቀኝ፡፡ የዚህን ስለ ይቅርታና መቻቻል የሚያስተምር ግለታሪክ መተርጎምና መታተም አስተዋጽኦ፣ የቤተመጻሕፍቴን ስራ፣ በአካዳሚው ዘርፍ ለመማርና ለማደግ ያለኝን ዕድል ገትቼ ስራዎቹን መስራቴን ገልጾ አመሰገነኝ፡፡

በዝግጅቱ ደራሲ ይታገሱ ጌትነት ተሳትፏል፡፡ የቀድመ ማስታወቂያ ሚኒስትር ግርማ ይልማም ስምና ተግባር ሲጠራ ሰምቻለሁ፡፡ ከአገር ውስጥ እኔና ይታገሱ ስንሆን በአጠቃላይ 25 ሰዎች ተሳትፈዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሊሆን የቻለው ዶክተር እንዳለ የአሜሪካ ዕድል በማግኘቱና አሜሪካ ያሉ ወገኖች በእርሱ በኩል አገራቸውንና ወገናቸውን ለመርዳት በመፈለጋቸው ነው፡፡ አሜሪካ የዕድሎች አገር ነው የሚባለውን እውነትነት ያሳየ ስብሰባ ነበር፡፡ የአስተባባሪው ማበረታቻና ምርቃት በየመሃሉ ያጀበው ውይይታችን እየደበዘዘ የሚመስለውን ኢትዮጵያዊነታችንን የሚያነቃቃና ለበለጠ ስራ የሚያነሳሳ ነው፡፡ ካለባቸው የጊዜ እጥረትና የኑሮ ጫና ዛሬ የሦስት ሰዓታት ጊዜያቸውን ስለሰጡን ማመስገን ይገባናል፡፡ ያልጻፍኩትን ብዙ ቁምነገር ያስጨበጡን ብዙዎች ናቸው! ከሁሉም በላይ ለዛጎል ቡክ ባንክ የገንዘብ መዋጮ ማድረጋቸው አገርቤት በየቤተመጻሕፍቱ የሚደርስ ስራ ነውና ድንቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡  

በአቶ አመኃ አስፋው ምርቃት ይዘጋ የተባለውን እርሳቸው ለደራሲ እንዳለ እድሉን ሰጥተው ተዘጋ፡፡

‹‹በትን ያሻራህን ዘር

ይዘኸው እንዳተቀበር›› በሚል የደበበ ሠይፉ ግጥም ደራሲው ሲዘጋ ሌላ ተሳታፊ ‹‹አዲስ አበባ ነግቷል›› ሲሉ ወደ መስኮት ሳይ ወገግ ብሏል፡፡ ሠዓቴን ከጠዋቱ 1፡00 ይላል፡፡ ደብረብርሃንም ነግቷል፡፡ በእውነቱ እውነተኛ የጥበብ፣ የእውቀት፣ የፍቅር፣ የመልካም ነገር ሁሉ ንጋት እንዲመጣልን እመኛለሁ፡፡ ለዚህም የሁላችንም ጥረትና ቀናነት ያስፈልጋል፡፡

 

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...