2023 ማርች 17, ዓርብ

ቁልፍ የሕይወት ክህሎቶች

ቁልፍ የሕይወት ክህሎቶች

በአሸናፊ ታደሰ

ዳሰሳ በመዘምር ግርማ

መጋቢት 2015 ዓ.ም

 

ስለ መጽሐፉ ያለኝን ግምገማ ከማቅረቤ በፊት መጽሐፉን ስላገኘሁበት አጋጣሚ ላንሣ፡፡ የሁለተኛ ደረጃ መምህሬ መምህር ጌቱ ተፈራ ትናንት ሰው ላስተዋውቅህ ብለው መምህር አሸናፊ ታደሰን ይዘዋቸው መጡ፡፡ መምህር አሸናፊን እንደማውቃቸው አላወቁም፡፡ ይሁን እንጂ የኃይለማርያም ማሞ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሥነልቦና አማካሪና መምህር ሆነው እንደማውቃቸው ነገርኳቸውና ተደሰቱ፡፡ አሁን የደብረብርሃን መምህራን ኮሌጅ መምህር ናቸው፡፡ ስለ መጽሐፍ የመጻፍ፣ የማሳተምና የማሰራጨት ጉዳይ ብዙ አወጋን፡፡ መጽሐፉን አንድ ቀን ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አነባለሁ ባልኩት መሰረት እነሆ አነበብኩት፡፡ የተሰማኝንም ለመጻፍ ቻልኩ፡፡  ‹ቁልፍ የሕይወት ክህሎቶች› የተባለው ይህ መጽሐፍ መምህራችን እኛን በትምህርት እንድንተጋና ክህሎቶቻችን እንዲዳብሩ ይመክሩን የነበረው ነፀብራቅ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡ ይህን አስተዋጽኦም ከትምህርት ቤታችን በዘለለ ለአሁኑም ትውልድ ማቅረባቸው ያስመሰግናቸዋል፡፡ እነሆ ወደ መጽሐፉ፡፡ ለመሆኑ መጽሐፉ ምን ይዟል? በምንስ ዓይነት አቀራረብ?

‹‹ደስተኛ ሕይወትን ለመኖር የሚያገለግሉ የተፈጥሮና የትምህርት ውጤት የሆኑ ዕውቀትና ክህሎቶች ወይም ብቃቶች›› በሚል ደራሲው የገለጿቸው የሕይወት ክህሎቶች በአእምሯዊ፣ በስሜታዊና በማህበራዊ ዋና ዋና ምድቦች ተከፍለዋል፡፡ ክህሎቶቹን በንባብ ልናገኛቸው ብንችልም ለበለጠ ውጤታማነት ደራሲው የተግባር ሥልጠና ወደመስጠት ሊያሸጋግሩት የሚገባ ይመስለኛል፡፡ እርሳቸውም ጠቆም ያደረጉት ክህሎቶችን፣ ይዘቶችንና ስልቶችን በሚገባ አጣምሮ ያካተተ የተግባር ስልጠና ያስፈልጋል፡፡

የሕይወት ክህሎቶቹን ከአሁን በፊት ከሥልጠና ሠነድ ባገኘኋቸው ጊዜ በጣም ተሰምቶኝ የአብዛኛው ኢትዮጵያዊ በተለይም ገጠር ያደግን ህብረተሰብ ክፍሎች ችግር አድርጌ አይቼዋለሁ፡፡ እኔም በግሌ ክህሎቶቹን ከማጣቴ አንጻር ብዙ ችግር ገጥሞኛል፡፡ እስኪ እርስዎም ገጥሞዎት ከሆነ የራስዎን ሁኔታ እያሰላሰሉ ይከተሉኝ፡፡ በመጽሐፉ ‹የንጥል ኩነት ትንተና› የሚሉ ምሳሌዎች ለእያንዳንዱ ክህሎት የቀረቡ ሲሆን፤ እነሱም ሃሳቡን ከአገራዊ ተጨባጭ ምሳሌ ጋር ለመረዳት ይጠቅማሉ፡፡

ራስን ማወቅ በሚለው ክፍል አእምሯዊና አካላዊ ጥንካሬን፣ ጠባይን፣ ፍላጎትን፣ ምኞትን፣ የምንወድና የምንጠላውን ማወቅ ያለውን ጠቀሜታና አለማወቅ ያለውን ጉዳት እንረዳለን፡፡ ያላወቀ ሰው የሚገጥመውን ጉዳት ለመረዳት በሰዎች ግፊት ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ገብቶ ስላልተሳካለት ግንበኛ የሆነውን ዘርጋው አውሌን ታሪክ ማንበብ በቂ ነው፡፡ ራስን ከማወቅ ጋር የሚያያዘው የራስ ግምት ደግሞ ስለራሳችን ያዳበርነው ግምት ከየት እንደመጣና እንዴት እንደሚሻሻል ያስተምራል፡፡ ከትምህርት፣ ከእርስበርስ ግንኙነትና ከአካላዊ ብቃትዎ አንጻር ለራስዎ የሰጡት ግምት ከፍተኛ ይሁን ዝቅተኛ ለመገምገምና ለማሻሻል ይህን ክፍል ይመልከቱት፡፡

ተቆርቋሪነት ስሜት ክህሎት ሕይወት በሌሎች ሰዎች ዘንድ ምን እንደምትመስል ገምተን መረዳትን ይመለከታል፡፡  በብዙ መልኩ የሚንጸባረቀው ይህ ክህሎት ከጎለበተ ለማህበራዊ ሕይወት፣ ለአገር ብሎም ለሁለንተናዊ የእርስበርስ ግንኙነት እርሾና ለእኔ ብቻ የሚልን አስተሳሰብ የሚያስቀር ነው፡፡ በአገራችን በአሁኑ ጊዜ እኔና ለእኔ የሚል አስተሳሰብ በመግነኑ ይመስለኛል ምስቅልቅል ውስጥ የገባነው፡፡ የዚህ ክህሎት አለመኖር ይህን ያህል ከጎዳን መኖሩ ምን ያህል ይጠቅመናል?        

አስተዋይነትና አመዛዛኝነት ያለው አስተሳሰብ ደግሞ ‹‹መረጃና ልምድን በተጨባጭና ከስሜት ነጻ በሆነ መንገድ የመተንተን ችሎታ›› ተብሎ ተገልጿል፡፡ በአእምሮ ሳያወጡና ሳያወርዱ፣ ሰውን ያስቀይማል አስቀይምም ሳይሉ እንደደቦጭ ሁሉ ከሰዎች ጋር ንግግርና ምልልስ ውስጥ መግባት ግጭት ላይ እንደሚጥልና ያልተፈለገ ነገርን እንደሚያስከትል ከመጽሐፉ ስናነብ ራሳችንንና ሌሎችን ወዳጆቻችንን በአእምሯችን ብንስል መልካም ነው፡፡ ይህ ክህሎት የፍቅር ጓደኛን ከመምረጥና ከሌሎች ወሳኝ የሕይወት ምዕራፎችም ጋር ይያያዛል፡፡ ከአስተዳደግና ከትምህርት ጭምር ያጣናቸው የዚህ ክህሎት ንዑሳን ክፍሎች ስለሚኖሩ ከራሳችን ጋር መነጋገሩ መልካም ነው፡፡

የፈጠራ ችሎታ የሚንፀባረቅበት አስተሳሰብ ሁኔታዎችንና ሃሳቦችን ለየት ባሉ ስልቶች ለመተርጎምና አዳዲስ ሃሳቦችንና ንድፎችን ለማፍለቅ የሚጠቅም ሲሆን በዘመናችን ተፈላጊውን የሃሳብ ተለማጭነትና በነባር አሰራሮች ላይ ለውጥ ማምጣትን ያመጣል፡፡ በአገራችን ካሉ የፈጠራ ሰዎች እስከ ዓለም አቀፎቹ የተጠቀሙቸውን ስልቶች እኛም በዕለትከዕለት ሕይወታችን መጠቀም እንደምንችል መገንዘብና መሞከር ያስፈልጋል፡፡

የችግር አፈታት ክህሎት ልዩልዩና ውስብስብ ችግሮችን ለመፍታትና በአግባቡ ለማስተናገድ የሚያስፈልገው በጥልቀት ማሰብና ማሰላሰል ነው፡፡ ከግል ችግሮቻችን ዓለምን በቅርቡ እስካናወጠው የኮሮና ወረረሽኝ ድረስ ምን ያህል ሳይንሳዊ መንገዶችን ተከትለን መፍትሔ ፈለግን ሲል የሚሞግተን መጽሐፍ መፍትሔውን ያስቀምጣል፡፡     

የውሳኔ አሳጣጥ ክህሎት ሌላው ወሳኝ የሆነ ክህሎት ነው፡፡ እርስዎ እስኪ በሕይወትዎ የወሰኑትን አንድ ጉልህ ነገር ያስቡ፡፡ ምን ጠንካራና ደካማ ጎን አለው? ለወደፊቱስ ውሳኔ ከመወሰንዎት በፊት አስፈላጊውን ሳይንሳዊ ሂደት መከተል ያለብዎት አይመስልዎትም?  ከውስጣዊ ማንነታችን ጋር የሚጣጣሙ ውሳኔዎችን ለመወሰንና ሕይወታችን እንዳይበላሽ ለማድረግ የውሳኔ አሰጣጥ ክህሎን ማወቅና መተግበር አለብን፡፡

ስሜትን በአግባቡ የማስተናገድ ወይም የመቆጣጠር ክህሎት ሳይንሳዊ መሰረትና ማብራሪያ ያለው ሲሆን፤ ስሜታችንን በአግባቡ መግለጽን ካልተማርን ጤናማ ስሜትንና ሥነምግባርን ማዳበር ላንችል እንችላለን፡፡ ስሜትን መቆጣጠርም ሆነ ውጥረትን መቋቋም ሕይወትን የሚያሰምርና ከበሽታና ከችግሮች የሚያድን ነው፡፡ ስሜታችንን ለይተን መቆጣጠር ስንችል፣ ውጥረትን የመቋቋም ክህሎትን ስናዳብርና የውጥረትን ምልክቶች ለይተን ስናውቅ ስሜትን በአግባቡ ማስተናገድም ሆነ መቆጣጠር እንችላለን፡፡ ዝርዝሩ ብዙ ሲሆን፤ መጽሐፉም መነሻ ይሆነናል፡፡

መግባባት ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ብንገነዘብም ከግል እስከ አገር መግባባት ሲያቅተን ይስተዋላል፡፡ የመግባባት ክህሎት እንዴት ያለ መሆኑን ከመጽሐፉ ስንረዳ እንደ ጎንጥ ችግሮቻችንን በጠብና በማስፈራራት ከመፍታት ይልቅ የተሻለ አማራጭ እንወስዳለን፡፡ በልዩ ልዩ መንገዶች ተግባቦትን ለማሳካት  ስናስብ መልዕክቱ፣ የመልዕክቱ ማስተላለፊያ መንገድ፣ የተግባቦቱ ማዕቀፍ፣ መልዕክት አደናቃፊዎችና የተቀባይ ግብረመልስ በሚለው መንገድ የምንጠቀም ሲሆን ይህም ሂደት በልዩ ልዩ ሁኔታዎች ሊሳካ ወይም ሊስተጓጎል ይችላል፡፡

የእርስበርስ ግንኙነት ክህሎት በተለያዩ አውዶችና ዓላማዎች ከሰዎች ጋር የሚኖሩንን ግንኙነቶች የተመለከተ ሲሆን የዚህም ስኬትና ውድቀት ግንኙነታችን የተሳካ እንዲሆን ወይም እንዲቋረጥ እስከማድረግ የራሱ የሆነ ሚና አለው፡፡  ልዩ ልዩ ጥቅሞች ያሉት የእርስበርስ ግንኙነት ደረጃዎችም አሉት፡፡ ትውውቅ፣ ማጎልበት፣ መቀጠል፣ መበላሸትና ማቋረጥ ሲሆኑ፤ በተለያዩ የግንኙነት ዓይነቶች ውስጥ የሚሰሩና ከግል ሥነምግባር ጋርም ትስስር ያላቸው ናቸው፡፡  

የአቻ ግፊትን የመቋቋምና የራስን አቋምና ስሜት ፊት ለፊት የመናገር ብቃት በሚል ከቀረበው ምዕራፍ የአቻ ግፊትን በቀላሉ ሊገጥመን በሚችል ሁኔታ ይጀምራል፡፡ ተማሪ ሆነህ ጓደኞችህ ደብሮናልና ሻይ ጠጥተን እንምጣ ያሉትን ሃሳብ ተቀብለህ ሄደህ ግብዣው ወደ ምግብና አልኮል እንዲድግ የተደረገበትን ሁኔታ ተጠቅሷል፡፡ ይህ መጥፎ ግፊት በሚለው ሊመደብ ይችላል፡፡ የዚህን ዓይነቱን ግፊት እንዴት ልንመረምርና ምላሽ ልንሰጠው እንችላለን? ይህ ቀጥተኛ ሲሆን በተዘዋዋሪ የሚመጣብን በማየታችን ብቻ ለማድረግ የሚገፋፋ ቀጥተኛ ያልሆነም ግፊት አለ፡፡ በይሉኝታም ይሁን ውጤቱን ባለማመዛዘን ከመግባት የራስን አቋምና ስሜት በግልጽ ስለመናገርና ስለአፈጻጸም ሂደቱ በመጽሐፉ የተጠቀሱትን ነጥቦች መጠቀም አስፈላጊ ነው፡፡

የመደራደር ክህሎት የመነጋገርና የመተማመን ብቃትን የሚጠይቅ ሲሆን ስኬቱ ክህሎቱን በማወቅ፣ በመለማመድና በመተግበር ይጎለብታል፡፡ የክህሎቱ አለመኖር የሚያመጣውን ቀውስ አስቡት፡፡ ሁለታችንም ተደስተንና ረክተን ጉዳያችንን ለመፈጸም  የሚጠቅመው ክህሎቱ የራሱ ደረጃዎች ያሉትና ያለመሰልቸት መተግበር ያለበት ነው፡፡

የማዳመጥና የጥናት ክህሎቶችን ስታስቡ በእናንተ የትምህርት ሕይወት እንዴት ይገለጻሉ? መጽሐፉ የውጤታማ አድማጭነት መመሪያዎችን ሲያቀርብ ትምህርት በሚሰጥበት ጊዜ ያለ የማዳመጥ ሂደትን በልዩ ሁኔታ ያቀርብልናል፡፡ ከማስታወሻ አያያዝም ጋር አስተሳስሮ ያቀርባል፡፡ መደበኛ የጥናት ፕሮግራም መኖር፣ በንባብ ወቅት መከተል ያለብን ተግባራት፣ የንባብ ስልቶችና ዓይነቶችን ያቀርባል፡፡  

የጊዜ አጠቃቀም ክህሎት ለውጤታማነትም ሆነ ለሕይወት ትልቅ ግብዓት መሆኑ አሌ አይባልም፡፡ የጊዜ ብክነትን የሚያመጡ በርካታ ምክንያቶች የተጠቀሱ ሲሆን በእኔ በኩል በጣም የሚያጋጥመኝና በመጽሐፉ የተጠቀሰውን አላስፈላጊ ከሰላምታ የሚከተሉ ጨዋታዎች መኖርን እንደምሳሌ መጠቀም ይቻላል፡፡ የቀረበውን የጊዜ አጠቃቀም መመዘኛ ሰንጠረዥ ተጠቅመን አጠቃቀማችንን ነጥብ እንድንሰጥ የሚጋብዘው ይህ ክፍል  ስለ ውጤታማ የጊዜ አጠቃቀም ጠባያት ያስተምረናል፡፡

ገንዘብን በአግባቡ የመቆጠብ ችሎታ ወይም ልምድ በትምህርት ቤት ያልተማርነው ወይም የትም ያልሰለጠነው ሳይሆን አይቀርም፡፡ ገንዘብን ለአስፈላጊው ጉዳይና በተገቢ መንገድ ማዋል፣ መቆጠብ፣ ብድርን በትክክል መጠቀምና ከዕቅድ ጋር ማስኬድ የተገባ ነው፡፡ ለዚህም ዝርዝር ነጥቦች ተቀምጠዋል፡፡

ራስን ከአደጋ የመጠበቅ ብቃት በጣም አስፈላጊ ሆኖ የቀረበ ሲሆን በአሜሪካ በተለያዩ የዕድሜ ደረጃዎች ያሉ ሰዎች ለአደጋ የሚጋለጡባቸውን ምክንያቶች በማቅረብ ይጀምራል፡፡ የመኪና አደጋን አስመልቶ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ 30 እጥፍ አደጋ እንዳለ ሲገልጽ ለልዩ ልዩ አደጋዎች ማድረግ ያለብንን ጥንቃቄ ያስገነዝባል፡፡ ለመሆኑ እርስዎ ለየትኛው አደጋ መከላከል ክህሎቱ አለዎት? መጽሐፉ መነሻ ክህሎቶችን አስቀምጧል፡፡

የግልና አካባቢ ንጽህናን የመጠበቅ ዕውቀትና ክህሎት እንዲሁም የደን ደህንነትን የመጠበቅ፣ የመተካትና የመጠቀም ዕውቀትና ክህሎት ቀጣዮቹ ናቸው፡፡ በመጽሐፉ ውስጥ ለጥቅም የዋሉትን ቃላት በሙዳዬ ቃላት በይነዋል፡፡ የማጣቀሻ ጽሑፍ ዝርዝርም ተካቷል፡፡ ትክክለኛው መጽሐፍ በትክክለኛው ጊዜ!

2023 ማርች 13, ሰኞ

ልቼ፣ የአፄ ምኒልክ መናገሻ ከተማ ወድማለች

 

ልቼ፣ የአፄ ምኒልክ መናገሻ ከተማ ወድማለች

የጉዞ ማስታወሻ

በመዘምር ግርማ

መጋቢት 3፣ 2015 ዓ.ም.

 

የአድዋን ድልና የጥቁሮች የታሪክ ወር የሆነውን የካቲትን በማሰብ በ2007 ዓ.ም. እንጎበኛቸዋለን ካልናቸው ሦስት ታሪካዊ ከተሞች ማለትም አንኮበር፣ አንጎለላና ልቼ አንዷ የሆነችው ልቼ በወቅቱ ሳትጎበኝ ቀረች፡፡ ሌሎቹን ጎብኝተን በጉዞ ማስታወሻ ያስተዋወቅነውና ሌሎች ጎብኝዎችን ለመሳብ የቻልንበት ወግ ሳይደርሳት ቀረ፡፡ ቀኑ ደርሶ የራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት የጉዞ ማህበር አባላት ለዚህች ቀን ተቀጣጠርን፡፡ ዘንድሮ ከዘጠነኛው የአንጎለላ የእግር ደርሶ መልስ ጉዞና የአንኮበር ጉዞ በኋላ ልናያት ቆርጠናል፡፡ 

እሁድ ጠዋት በአጋጣሚ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን 16ኛው የግማሽ ማራቶን ውድድር ከጫጫ እስከ ደብረብርሃን ይካሄድ ኖሮ መንገድ ለትራንስፖርት ተዘጋ፡፡ ይህን ያላወቁና ቀድመው ያለተነሡ አባላት በከተማው መካከል የተቀጣጠረው ቡድናችን ስላመለጣቸው ቀሩ፡፡ እነሱን ሌላ ቀን ትጎበኛላችሁ ብለን 15 አባላት በእግራችን ወደ ልቼ አቀናን፡፡ ስንጓዝ እንደወትሮው የታሪክ ርዕሶችን እያነሣን ለመወያየት ያመቸን ዘንድ በአራት ቡድኖች ተከፍለናል፡፡ በውይይትም ጥሩ መንገድ አሳለፍን፡፡

አንድ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በግምት አራት ኪሎሜትር የሚሆነውን መንገድ አገባደን ልቼ ደረስን፡፡ ለታዕካ ነገሥት ልቼ ኢየሱስን ቤተክርስቲያን ካህናት ስለ ጉብኝት ፍላጎታችን አስረድተን እገዛቸውን ጠየቅን፡፡ አንድ ቄስም ባማረ ሁኔታ ያስጎበኙን ጀመር፡፡

ቤተመንግሥቱ በነበረበት ቦታ ላይ የተገነባው ዘመናዊ የቤተክርስቲያን ሕንፃ ተጠናቋል፡፡ በስተደቡብ አቅጣጫ በግቢ ውስጥ አፄ ምኒልክና አፄ ዮሐንስ ስምምነት የፈጸሙበት ቦታ ላይ የነበሩት ድንጋዮች ቤተክርስቲያኑ ሲታነጽ በስህተት መነሳታቸውን ነገሩን፡፡ በስተሰሜን የቤተመንግሥት ፍርስራሽ ይገኛል፡፡ በስተምስራቅ ደግሞ የበፊቱ ሰገነት በነበረበት ዲብ እንዳለ ሆኖ የቤተክርስቲያኑ መቃኞ ተሰርቶበታል፡፡

አስጎብኛችን እንዳሉን የአንኮበሩ ቤተመንግሥት የአፄ ምኒልክ አያቶች ሲሆን ይህኛው ግን የእርሳቸው ነው፡፡ እኛም ከታሪክ ንባባችን ይህ ቦታ ቤተመንግሥታቸው የነበረበት መሆኑን አንብበናል፡፡ ጳውሎስ ኞኞ አጤ ምኒልክ በሚለው መጽሐፋቸው ገጽ 49-50 የጻፉትን እንመልከት ‹‹በዋና ከተማቸው በልቼም ሦስት ቀን የቆየ ግብር አብልተው ሕዝቡን አስደሰቱት፡፡ ስለዚያ ግብር ሁኔታ ማሳዣ ሲጽፉ ‹… የተሠራው አዳራሽ ትልቅ ነበር፡፡ በአዳራሹም ለምግብ ማቅረቢያ 150 ረጃጅም ገበታ ተዘርግቶ ነበር፡፡ ወታደር፣ ሲቢል፣ መኳንንት፣ ቄስ፣ የልቼና ያካባቢዋ ታላላቅ ሰዎች ሁሉ ተጠርተው ነበር፡፡ ከጎጃም፣ ከጎንደር፣ ከትግራይና ከመላው ኢትዮጵያ ታላላቅ ሰዎች መጥተው ነበር፡፡› … በግብሩ ጊዜ በአዳራሹ ውስጥ ንጉሥ ምኒሊክና መሐመድ አሊ በአንድነት ተቀምጠው ታዩ፡፡››

ከዚህ ላይ በአእምሯችን ሊመጣ የሚችለው ጥያቄ ያ የቤተመንግሥት ግቢና አዳራሽ አሁን የት ገባ የሚል ነው፡፡ ያ ግብር ያበሉበት፣ የኖሩበት፣ ክፉና ደጉን ያዩበትና ያስተዳደሩበት ቤተመንግሥት ምልክቱም የለም፡፡ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጊዜ ቦታው ጥቅም ይሰጥ እንደነበር አስጎብኛችን ነግረውናል፡፡ የተከበረውን ቦታ ያጠፋው ስፍራውን በመሬት ላራሹ ለገበሬዎች ያከፋፈለው ደርግ መሆኑን አውስተው በ1989 ዓ.ም. የመሬት ድልድል በኢህአዴግ መንግስት ገበሬዎቹ እንዲነሡና ለቤተክርስቲያን ቦታውን እንዲሰጡ ተደርጎ በአሁኑ ጊዜ 12 ሄክታር ቦታ በቤተከርስቲያኑ ይዞታነት እንዳለ አስረድተውናል፡፡ ይህም ቦታ ሦስት ዙር የጥንቱን የቤተመንግሥት የካብ አጥር የያዘ ሲሆን ያንንም አጥር አይተናል፡፡ በግሌ የገረመኝ ነገር ገና ሥልጣን እንደተቆጣጠረ የአፄ ዘርዓያዕቆብን የመካከለኛው ዘመን እውቅ የደብረብርሃን ቤተመንግሥት ፍርስራሽ በትራክተር ጠራርጎ ያጠፋው የኢህአዴግ መንግሥት ይህን ስፍራ ለቤተክርስቲያንም አልሰጥም ብሎ በመኖሪያ መንደርነት እንዴት እንዳላጸናው ወይም በሌላ መንገድ አሻራውን እንዳላጠፋው ነው፡፡ ከቤተክርስቲያኑ ቅጽርግቢ ውጪ ወጥተን የአፄ ምኒልክ ጊዜ ጥቅም ትሰጥ የነበረችውን ያን ጊዜ በልዩ ሁኔታ የተገነባች ምንጭ አይተናል፡፡ ውኃም እየቀዱ የነበሩ የአካባቢው አርሶአደሮች ቀድተው ሰጡንና ጠጣን፡፡

ከምንጯ አለፍ ብሎ የበዛብህ መቃብር አለ፡፡ እሱንም ባሻገር አይተናል፡፡

‹‹አንተም ጨካኝ ነበርክ ጨካኝ አዘዘብህ፣

እንደ ገና ዳቦ እሳት ነደደብህ››

የተባለው በዛብህ በስልጣን ሽኩቻ ምክንያት ተደጋጋሚ የአመጽ ሙከራ በማድረጉና በምህረትም ባለመመለሱ በኋላ ሞት ተፈርዶበት የነበረ ሰው ነው፡፡

አስጎብኛችን ‹‹ለስፍራው ለወደፊቱ ምን ይደረግ›› ብለን ላቀረብንላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ ቦታው መልማት እንዳለበት ገልጸው የእምዬ ምኒልክን ውለታ መመለስ እንዳብን አሳስበዋል፡፡ ስለአጼ ምኒልክ ደግነት ነገሩን፡፡ ፈጣሪ ባስመለከታቸው ሁሉ በዘመኑ የማይታመን ድንቅና መልካም ሥራ መሥራታቸውን ነገሩን፡፡

በመቀጠል በስፍራው ሎጅና ሙዚየም ለመስራት በደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ባለፈው ዓመት የተጣለ የመሰረት ድንጋይ አየን፡፡ ስራው እንደሚጀመር ተስፋ አደረግን፡፡ በስፍራው ያለውን ታሪክ በቃል ከመገንዘባችን በዘለለ ለምልክት የሚሆን ቅርስ ባለመኖሩ ቅር እያለንንና የቤት ስራ እንዳለብን በመገንዘብ ወደ ደብረብርሃን በእግራችን ጉዞ ጀመርን፡፡ ውይይታችንንም አባላትን በመቀያየር ቀጠልን፡፡ ደብረብርሃንም ከቀኑ 6፡00 ላይ በሰላም ደረስን፡፡ 




 

 

2023 ማርች 9, ሐሙስ

My Jobseeking Story under a Repressive Regime in Ethiopia From 16 Years Ago

About this article

This story from 2013 by itself has its own story which is a story of self-censorship. I am now writing in 2023. Self-censorship could have various forms. Mine is of a different breed. This is reflected in a task I have been doing this week. I have been checking all my hard and soft copy documents from my entire life. I grabbed an old notebook from a 2015 British council and Ministry of Education training. The training concentrated on all the skills of English. I found the draft essays I wrote for the writing part. One of them was of my job-seeking one. The story of that essay I wrote is very appealing. In one of the evenings I wrote it following the steps, revised and proofread it to finally fall in love with it. Afterwards, I printed it the next morning and headed to the training venue. I handed it to my writing trainer who was preparing herself for the day’s session before anyone came in early morning in one of the training halls of Ras Amba Hotel in Addis. I had the courage to give her because she was non-Ethiopian. Could she be a government sympathizer?       

Ten years after that, I still remember the feeling that Brit exhibited in her face. She clinched her fists and munched her lower lip. She told me that mine was an excellent one. However, I think afterwards I discarded the paper that I loved. Even if I valued it because it was my own story of being subjected to injustice, I destroyed it for fear of being discovered by the government. And I removed its soft copy from my computer too. This was for fear of being attacked if the government by any means searches my house or computer. I was censoring myself. After I wrote this new note, something struck my mind and I went to my yahoo account and searched using its title. I got it! I couldn’t believe my eyes. I have been looking for it everywhere regretting my decision. I even thought it was time to publish it on my blog when the TPLF government fell five years ago. Now I got it from the sent items list. I couldn’t believe that even I had a friend to send the article to. Could anyone be trusted with this piece which criticized the employment and political system of the government that is no more on power now?

Reading it reminded me of my student days which were not simple ones for financial difficulties. How I was not an easy going guy then! How I had a solitary lifestyle and a rigid mindset! I had a fear deep in my heart what my future would look like. Sixteen years after graduation, there seems to be no significant change if not for a few of my contributions in my field. These include three books published, a private library opened and a few other issues.  I invite you to read it below.

Mezemir Girma,

Debre Birhan

 

 

Once Pushed Out, Victor At Last! 

Mezemir Girma   

2013

Addis Ababa

My university days were not as frightening as my job seeking ones because my time at university, though challenging, was productive and rather enjoyable. I graduated with a bachelor’s Degree in English Language and Literature (non-teaching) from Addis Ababa University in August 2007. When I finished I didn’t think that I would face a considerable challenge tougher than getting a degree – securing my bread. Nevertheless, I had to face the challenge of seeking a job which has become even more challenging for most of the graduates now after five years. What was my dream job first of all? I was aspiring to be employed as a journalist, a public relations officer, or an expert in one of the public offices as I studied courses which prepared me for these positions. But all what happened then was that graduates were recruited as early as they were still in their university dormitories, based on a non-academic criterion, which I wouldn’t qualify for. Those classmates of mine who had the least grades were assigned at nice positions. I was not considered even if I had one of the best grade point averages (GPAs).

By the way, I was one of the graduates with the best GPAs whose names had been sent to the Ministry of Education which requested a list be sent to it for Assistant Graduate positions in the 13 newly opened universities in the regions. I and my friends even filled in forms and ranked universities where we wanted to work. But the ministry officials did not post the names of mine and most of my friends in the state Amharic daily newspaper, Addis Zemen (literally meaning New Era). It was all the names of the graduates from the regional universities that they were posting as it was with GPAs that they selected. Normally Addis Ababa University (AAU) graduates had no better grades than their regional universities’ counterparts because of the strict grading trend at AAU.   

No option did I have. The vacant posts left for me were in the private organizations in Addis Ababa. Non-Governmental Organizations, which had the most coveted jobs in town, were unthinkable, since they were in most cases said to be employing people based on recommendations and a rich work experience. So, where did I go to apply? It was to private schools, private media and tourist organizations which were all not well paying ones. Do you want to know if I succeeded? If so, okay, please keep reading.  

An employee was not to be proud of having a job in the private schools, after all. You know why? Their jobs were not as secure as the public ones since they would fire you based on any pretext including the compliant of a student or a student’s parent since they were their sources of income they didn’t want to lose. They would not pay you salary during the two summer months in which there is no school as if you were not eating and living during that season. In the beginning, if you pass their interviews and get employed amid all the partiality you experience, be it ethnic, religious, or linguistic, you will definitely start your suffering. Is there any happy private school teacher in Addis Ababa? The answer is, NO, in most cases! The employers’ boastful act, the huge work load and the meager salary, the 6, 7 or 8 square meter narrow old rented room he/she is living in paying at least one third of his/her monthly income make life miserable. There is a usual saying among the Addis Ababans- “We the lower class people are not living true life here, but witnessing the rich live it to the brim”. If the rich, in most cases, were better than me academically or if they learnt throughout their ages, my senses wouldn’t boil. I think most of them have not even read at least the classic Ethiopian novel “Fikir Eske Meqabir”, or a book of the Holy Qoran or Bible. They cannot tell you what this week’s newspapers in Addis Ababa wrote about. They would even say that reading is boring after all. However, the money is unfairly made go to them.

What did my job seeking days look like? My daily routine was as follows: In the morning hours I used to go to Arat Kilo square which is some half an hour walk from the room I rented and read vacancies posted on the commercial noticeboards there. With a public phone, I phone to the employers who are advertising a vacancy and check where their offices are found if they have not indicated in their notices. If it is a job that suits me, I go to their offices asking people I meet on the roads where the particular place is. Then I submit a copy of my application letter, curriculum vitae and credentials to the organizations. Then I seek other notices in newspapers. I had to pay 25 cents to read a single newspaper and check if there is a vacancy I need posted. I always ate lunch outside and went home back in the evening tired and hopeless.            

It was via the phones of my relatives and friends that employers reached me. Most schools had both written exams and interviews. If you pass the written exams, you will be among those who go for interviews. You then agree or disagree on the salary, workload, working environment or other imposition if you only pass. You don’t know sir! All this up and down you underwent may be for the employers’ mere convenience. It is said that they use the written exam sheets and the copies of credentials of you and of the many applicants as a proof of accountability when government supervisors visit them. So they employ the already known nominee who is their close relation or whatever. In some case, there are good and impartial employers, though. I don’t need to conduct a formal survey to say that most are not good ones as I experienced many unethical school owners and administrators. It is to 47 organizations that I applied in the three months immediately after my graduation, most of them being schools. People consoled me saying that it is a common practice in Europe to apply to not less than 100 companies to get a job. This helped me a lot. 

One afternoon in November 2007, two young men and a young woman interviewed me in their school found in southern Addis Ababa, my home being in the northern tip. They were satisfied and hired me. I was elated too. I worked in this English medium elementary school as a grade one and two science and social science teacher. This is the place where I enjoyed working for three and a half months not mentioning another where I worked as an English teacher for two weeks. I used to commute the long distance in the Lion Buses of Addis Ababa. It was in this bus that I heard one day a singer ‘newsreader’ beggar say “Lion Bus- the poor’s shoes”. Not long after I was told that I passed the three month probation period, I got an opportunity to go for a better job outside Addis Ababa as a lecturer in one of the state universities. Look! It is for six months that I was waiting for this seemingly nice job.  

There in the universities you would have the chance to study your master’s degree and to grow financially. Recently a year after I was graduated in a Master’s Degree my former non-Ethiopian university friend who is a diplomat of one African State told me that he rather wanted to be a university lecturer than a diplomat. Is it such a coveted work that I am doing? I was once pushed out and now I am in such a work which satisfies me and in which I serve my country happily.       

 

 

2023 ማርች 4, ቅዳሜ

ስውር ምንጭ - የሐውለት አህመድ ‹‹አሽር ቤት›› መጽሐፍ ዳሰሳ ከትዝታዎች ጋር

ስውር ምንጭ

የሐውለት አህመድ ‹‹አሽር ቤት›› መጽሐፍ ዳሰሳ ከትዝታዎች ጋር

በመዘምር ግርማ

የካቲት 25፣ 2015 ዓ.ም.

ደብረ ብርሃን

 


ከልጅነት ሕይወቷ በተለይ ሰባቱን ዓመታት አስመልክቶ የተጻፈው ይህ ‹‹አሽር ቤት›› የተባለው መጽሐፍ 174 ገፆች ሲኖሩት ዋጋው 290 ብር ነው፡፡ ከሥነጽሑፍ ዘውጎች ለማስቀመጥ ከታሰበ ‹ሜሟ› ማለትም ማስታወሻ ሊባል ይችላል፡፡ አቀራረቡ እንደ አጭር ልቦለድ ስብስብ ያለ ነው የሚያስበለው አጫጭርና የራሳቸው ርዕሶች ያሏቸው ታሪኮች ስላሉት ነው፡፡ ከክፍል ክፍል ሲሸጋገሩ ለማንበብ የሚያጓጓና ልብ-ሰቃይ የሆነው ታሪኩ፤ እንደ ወጥ ረጅም ልቦለድ የተያያዘ ነው፡፡ ለማንበብ ከሁለት እስከ ሦስት ሰዓታት የፈጀብኝን ይህን ታሪክ ትናንት ማታ ከእንቅልፌ በፊትና ዛሬ ጠዋት ከእንቅልፌ በኋላ አነበብኩት፡፡ የቃላቱ ብዛት በማባዛት ለሃያ ሺህ ቃላት የሚጠጋ እንደሆነ የገመትኩ ሲሆን የአንድን ኖቬላ ያህል ርዝመት አለው ለማለት ይቻላል፡፡ ስለሆነም እንደ አንድ ወደረኛ አጭር ልቦለድ ከአንድ ቁጭታ ሊነበብ የሚችል ሲሆን ለፈጣን አንባቢ ጊዜ አይወስድም፡፡ ግን በየመሃሉ ቆም እያሉ ማሰብና ማሰላሰል ስለሚኖር ጊዜ ቢወስድብዎትም አይገርምም፡፡  እንደኔ ያለው ደግሞ በመጽሐፉ ላሉት ታሪኮች በአጋጣሚ የተገኘ ቅርበት ያለው ሰው ምስክርነቱና የሚሰጠው ምላሽ በእጅጉ ይጠበቃል፡፡

አብዛኞቹን ታሪኮች ባለታሪኳ በፌስቡክ ገጿ በለቀቀችበት ወቅት ተከታትዬ አንብቤያለሁ፡፡ ያላነበብኳቸውም ነበሩ፡፡ ዛሬ ሁሉንም በአንድ ጥራዝ ማግኘቴ ስለጠቀመኝ እንኳንም ታተሙ ብያለሁ፡፡ ሁሉንም እንዳዲስ ለማንበብም ፍላጎቴ ነበር፡፡ የቋንቋ አጠቃቀሟን አስመልክቶ ለአረብኛ ቃላት የግርጌ ማስታወሻ ማስቀመጧ ማለፊያ ነው፡፡ አንዳንድ የእንግሊዝኛ ቃላት ቋንቋውን የማይችሉ ወገኖችን ግር ሊያስብሉ ቢችሉም መሰረታዊ የመረዳት ችግርን አያመጡም ባይ ነኝ፡፡ እንግሊዝኛ የአማርኛ ንግግርና ጽሑፋችን እንዲሁም የሕይወታችንም ጌጥ ስለሆነ፡፡ አረብኛ የሙስሊሙ ህብረተሰብ፣ ግእዝ የክርስቲያኑ እንደሆነው ሁሉ እንግዚዝኛም የትምህርት ቤት ደጅ የረገጥን ሰዎች ንግግር ማድመቂያ ነው፡፡ ‹‹የደራሲዋ የአጻጻፍ ዘዬ ራሷ ደራሲዋ ነች›› እንደሚሉት የሥነፅሑፍ አሳብያን የአማርኛ፣ የአረብኛ፣ የእንግሊዝኛና የአርጎብኛ ውህድ በመጽሐፏ እናገኛለን፡፡ የሐውለትን አቀራረብ በቋንቋ ብቻ ሳይሆን በአጻጻፍ መላዋም ማየት ይቻላል፡፡ ከብዙ በጥቂቱ ምልልስ፣ ትረካ፣ ገለጻ፣ ግነትና ልዩ ልዩ ዘይቤዎች በጽሑፏ ይገኛሉ፡፡ እነዚህን ጌጦች ከልቦለድ አላባውያን ጋር አሰናስላ በፈጠራዊ ኢ-ልቦለድ ምድብ ሊገባም የሚችል ማስታወሻ አስነብባናለች፡፡ ይህን ድምዳሜ ሳቀርብ ከአጻጻፍ ዘዴ አንጻር እንጂ የተባለው ታሪክ አልተፈጸመም ማለቴ እንዳልሆነ ልብ ይሏል፡፡ በቀላልና ግልጽ አቀራረብ የቀረበው መጽሐፉ አረብኛንና የቁርአንን ትምህርት ሁኔታና ተፈጥሮ ያስተዋውቃል፡፡ ፊደላቱንና የአነባበብ ዘየውንም ያሳያል፡፡ ይህን ለመሞካከር ላሰበ መጽሐፉ መነሻ ይሆነዋል፡፡ 

ጽሑፌን የሚያሳምሩልኝ የትዝታ ጌጦች ስላሉኝ በተኖረ ልምድ ላይ ተመስርቼ የሚከተሉትን ገፆች አብረን እንቆያለን፡፡ እኔ በቄስ ትምህርት ቤት ባልማርም እዚያ የተማሩ ልጆች ከሚነግሩኝና ስለቄስ ትምህርት ቤት ካነበብኩት ጋር የአሽር ቤትም ነገር ተመሳስሎብኛል፡፡ በአንዲት ቤት ሁሉም ተማሪ መማሩ ያመሳስለዋል፡፡ የሦስቱ የደብረብርሃን አሽር ቤት ተማሪዎችን ብሽሽቅ ጉዳይ ሳነብ ሳሲት ደብተራ ዘለቀ ጋ የሚማሩት ተማሪዎች ከመንግስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች የሚደርስባቸው የግጥም ውረፋ ትዝ አለኝ፡፡ በቄስ ትምህርት መጽሐፍ ቅዱስን አንብቦ መጨረስ መኖሩን እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ በአሽር ቤት ግን ቁርአንን ማንበብ ግድ ነው፡፡ ሐውለትም ከሁለት ጊዜ በላይ አንብባለች፡፡ የኔ ጥያቄ ትርጉሙን ትረዳዋለች ወይ የሚለው ነው፡፡ ለውህ የተባለውን መጻፊያ የጣውላ ቁራጭ የመሬም የልጅ ልጅ መሊካ ስታጸዳ አይቼዋለሁ፡፡ ወደ አሽር ቤቴ ልሂድ ስትልም ስለምሰማ ቃሉ አሁን አዲስ አልሆነብኝም፡፡ የመጻፊያውን ነገር ስናነሣ አሽር ቤትን ከቄስ ትምህርት ቤት የሚለየው  ነገር ነው፡፡ ቄስ ትምህርት ቤት ከብዙ ቆይታ በኋላ ወደ ጽሐፈትና ሥዕል የሚያመሩ ልጆች እንጂ አብዛኛው መጻፍ እንደማይማርና እንደማይችል ነው የሰማሁት፡፡ የቁም ጽሕፈት የሚለምዱት በሂደትና ምናልባት በስተመጨረሻ ነው፡፡ እንደ አሽር ቤቱ ሁሉ መድ ወይም ቀለም ከእጽዋት የሚያዘጋጁትም ሆነ ብራና የሚፍቁት በኋላ ነው፡፡ ሽምደዳውም ተመሳሳይነት አለው፡፡ የትምህርት ስርዓቱም መምህሩ ሁሉንም ሳይሆን የመጨረሻዎቹ ከፍተኛ ደረጃዎች ላይ ያሉትን ያስተምራሉ እንጂ ሌላው እርስ በእርሱ እንደሚማማርና እርሳቸው ፈትኖ ከደረጃ ወደ ደረጃ ለማሳለፍና የመማማሩን ስርዓት ለመከታተል ነው የሚያስፈልጉት፡፡ የማስተማር ስርዓቱ የሁለቱም ኃይማኖቶች ምርምሮች እንደተሰራበት ሰምቻለሁ፡፡ የሙስሊሙን የኃይለማርያም ማሞ ትምህርት ቤት የፊዚክስ መምህራችን አህመድ ለማስተርሳቸው መስራታቸውን የኔም የሐውለትም መምህራችን የነበረውና የአሁኑ የሥራ ባልደረባዬ ዶክተር ሰይድ ነግሮኛል፡፡ እንደ ዶክተር ኃይለገብርኤል ዳኜ ዓይነቶቹ ደግሞ በሁለቱም ላይ የሰሩ አሉ፡፡ ከኃይማኖቱ ዉጪ ያሉት የሚሰሩት የራሱ የሆነ ውጫዊ ምልከታ ስለሚኖረው ጠቀሜታው የጎላ ይመስለኛል፡፡

ሙስሊሞች በአረብኛ ትምህርት አእምሯቸውን እንደሚያሰሉ ሐውለት የገለጸቸው እውነት ነው ባይ ነኝ፡፡ የቤተክህነት ትምህርትም እንደዚሁ ስለሚባል፡፡ ልዩነቱ የቤተክህነት ትምህርት የተማሩ ሰዎች ግእዝ ከአማርኛ ጋር ስለሚቀራረብ የበለጠ ዕድል ያላቸው ይመስላል፡፡ በዚያ ያለፉት ታዋቂ የአማርኛ ደራስያን መሆናቸው አይካድም፡፡ ይህን ዕድል ምናልባት በሙስሊሞች ዘንድ እንዳናገኘው የሆንን ይመስለኛል፡፡፡ ለዚህም ምክንያት ሊሆን የሚችለው ልጆቹ አረብኛን አቀላጥፈው ችለው በቋንቋው የመጻፍና የማሳተም ዕድል ስለሌላቸው ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ወደ አረብና ሙስሊም አገራት የመሄድ ዕድል ያላገኙትን አስመልክቶ ነው፡፡ በእርግጥ እኛ ስላላነበብንና ዕድሉ ስለሌለን እንጂ በዘርፉ ተጽፏል፡፡ ወደፊትም ማንበብና ማወቅ ያለብን ብዙ የአረብኛ ሥነጽሑፍና የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ታሪክ አለ፡፡ በቢቢሲ ስለ አፍሪካ የእስልምና ተማሪዎች የትምህርት ሁኔታ ያነበብኩት ተማሪዎቹ ምግብ ከህብረተሰቡ የሚለምኑበት ሁኔታ በደብረብርሃን የለም፤ ለበዓላት ስጦታ ለመጠየቅ ወደሚያውቋቸው ሙስሊሞች ቤት ከመሄዳቸው ውጪ፡፡ በሌሎች ገጠራማና ተማሪዎች ከወላጆቻቸው ርቀው በሚኖሩባቸው ቦታዎች ግን ሳይኖር አይቀርም፡፡

እኔ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርቴን የተማርኩት በደብረብርሃን ነው፡፡ እስከ 8ኛ ከተማርኩበትና ተወልጄ ካደኩበት ሳሲት 92 ኪሎሜትር ርቄ በኪራይ ስማር የ11ኛና የ12ኛ ክፍል ትምህርቴን በእነ ሐውለት ግቢ ተከራይቼ ነበር፡፡ አከራዬ የአቶ ወርቄ ቤተሰብ እነ እንግዱ ቢሆኑም መውጫዬ በነ ሐውለት በኩል ስለሆነ ከነሱ ጋር ነው ይበልጥ ቅርርብ የነበረኝ፡፡ በመጽሐፉ የተጠቀሰችው የሐውለት አክስት ወይዘሮ መሬም በጣም ደግና እንደ ልጅ የምታየኝ ነበረች፡፡ ስለ ኃይማኖት መቻቻል ለመግለጽ ካስፈለገ ሐውለት በመጽሐፏ ከጠቀሰችው በላይ አክስቷ መሬም ክርስቲያን ማግባቷ ይገልጸው ይሆናል፡፡ ከክርስቲያን ባሏም ሁለት ልጆችን ወልዳለች፡፡ ታናሽ እህቷ ሠሚራም ከኔ ጋር ተመሳሳይ የክፍል ደረጃ ላነበረች፡፡ ሐውለት ግን አራት ዓመት ትቀድመናለች፡፡ የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ ሆኜ እሷ ወደ ዩኒቨርሲቲ ስለገባች በአካል አላውቃትም ነበር፡፡ ከእርሷ በፊት ግን ዝናዋን ከመምህራን ሰምቻለሁ፡፡ ከዚያም በዘለለ ቤተመጻሕፍት ካገኘሁት የአዲስዘመን ጋዜጣም ቃለምልልሷን አንብብቤያለሁ፡፡ የናቹራልም የሶሸልም ተማሪ እንዳልሆነች ልግለጽላችሁና የምን እንደሆነች ገምቱ፡፡

የደብረብርሃንን ብርድ በትክክል ስለገለጸችው የምለውም የለኝ፡፡ በስስ ቲሸርትና በዚያች የደንብልብስ የተቋቋምንበት የአራት ዓመት ጊዜ አስገራሚ ነው፡፡ ገል መታቀፍ ያለችው ዘዴ ለኛ ቤተሰብ ላልነበረን ልጆች የቅንጦት ነበር፡፡ ሐውለት በዚህ መንገድ በትጋት አጥንታ የደረሰችበትን ደረጃ ወደፊት ስለዓለማዊ ትምህርቷ ትስጽፍ ታጋራናለች ብዬ አስባለሁ፡፡ እኔ ከአክስቷና ቤተሰቧ ንዲሁም ከትምህርት ቤት መምህራን ስለሐውለት የሰማሁት አነሣስቶኛል፡፡ በኋላ በቴሌቪዥን ዜና አንባቢ ሆና ስትመጣ ለሁሉም የደብረብርሃን ልጅ፣ ሙስሊም፣ ሴት ሁሉ አነሣሽ ሆናለች ለማለት እችላለሁ፡፡

ከአርጎባ ዘመዶቿ የቅርቡን ትውልድ የተወሰኑትን አውቃቸዋለሁ፡፡ እናትና ልጆቹ ወለላና ሲቲም እኛው ግቢ ተከራይተው ይኖሩ ነበር፡፡ ስለ አያቶቿ እሰማለሁ እንጂ አልደረስኩባቸውም፡፡ ስለ ሴት አያቷ ደግነት ሳነብ የመሬምን ደግነት ስለማውቅ እንባዬ ችፍ ብሏል፡፡ በነገራችን ላይ ሐውለት በልጅነቷ እንዲኖራቸው ትመኘው የነበረው ቴሌቪዥን በቤታቸው የተገዛው በኔ ዕድሜ ነው፡፡ ብዙ ዜናና መዝናኛ ያየሁበትም ነው፡፡ ምናልባት እሷንም ጭምር፡፡

የኃይማኖት መቻቻልን አስመልክቶ ባለፈው ከደብረብርሃን ሙስሊሞች አንዱ ከሆነው ከግሪን ዞኑ ከድር ጋር ተገናኝቼ በለጠፍኩት ጽሑፍ እንዳልኩት ነው፡፡ ልዩነታችን ምንም አይታየንም ለማለት ይቻላል፡፡

መቼም ስለ ሙስሊሞች ትምህርት ቤት ሲነሳ ቀድሞ ስለ ሙስሊሞች ማሰብና የኔ እሳቤ ምን ይመስል እንደነበር መግለጽ ያስፈልጋል፡፡ ከቆላ የሚመጡት የሐውለት ዘመዶች ክርስቲያን አይተን አናውቅም እንዳሉኝ ሁሉ እኔም ሳሲት ብዙም ሙስሊም አይቼ አላውቅም ነበር፡፡ አልፎ አልፎ ግን ለማየት ችያለሁ፡፡ ቢሆንም እንግዳ ይሆኑብኛል፡፡ ኃይለማርያም ማሞ ስማር ብዙ ሙስሊሞች የክፍል ጓደኞች ሊኖሩኝ ቻሉ፤ በከተማውም ብዙ ሙስሊም አወቅሁ፡፡ ሲሰግዱ ማየት፣ ሲፆሙ ስለፆማቸው መረዳት፣ ስለ አለባበሳቸው መጠየቅ ወዘተ ችያለሁ፡፡ አርጎባ፣ ወርጂና አማራ ሙስሊሞችን ተዋወቅሁ፡፡ ሐውለት በመጽሐፏ እንዳለችውም ሆነ ከአሁን በፊት ከጉግል እንዳነበብኩት የደብረብርሃን ሙስሊም ብዛቱ አምስት በመቶ ነበር፡፡ አሁን ግን ለውጦች ያሉ ይመስለኛል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ የሙስሊምና ክርስቲያን ቁጥር በትክክል እንደማይታወቀው ሁሉ የደብረብርሃንም የሚታወቅ አይመስለኝም፡፡ ለመላ ምት የተጋለጠ ነው፡፡ በዚህች የሙስሊሞች ቁጥር ዝቅተኛ በሆነባት ከተማ ሙስሊሞች የራሳቸው የሆነ ታሪክ አላቸው፡፡ በቀደምት መንግስታት ጊዜ ገብተው የነበሩት አረቦች በተለያዩ ጊዜያት ወደየአገሮቻቸው ቢመለሱም በትዳርና በወዳጅነት ከህዝቡ ጋር ተሳስረዋል፡፡ የሐውለትን አረብ እናት ወይም አከስት እርግጠኛ ባልሆንም ለእረፍት መጥታ አይቻታለሁ፡፡ የደብረብርሃን ሙስሊሞች ከቁጥራቸው ማነስ ውጪ በፍቅር መኖራቸውን አይቻለሁ፡፡ መጽሐፏም ምስክር ነች፡፡ ሙስሊሞች እንደ ደሴት በቁጥር ትንሽ ናቸው፡፡ አሽር ቤትን ሳስባትና አስተዋጽኦዋን ስረዳ ደግሞ ብዙዎች ትኖራለች ብለው የማይምቷት ስለሆነች ‹‹የደሴት ውስጥ ደሴት›› ልላት ቻልኩ፡፡ በተሻለ ሁኔታ የምድረበዳ ምንጭ ልትባልም ትችላለች፡፡ ይህን ሁሉ ቅሬታ አምጪና አወዛጋቢ ነገር የዚህ ጽሑፍ ርዕስ አድርጌው ነበር፡፡ በኋላ ቀየር አድርጌ ‹‹ፎር ዘ ፎለን›› ከሚለው›› ከሎረንስ ቢንየን ግጥም አንዲት መስመር ሃሳብ ወስጄ ርዕስ ሰጠሁት - ‹‹ከዕይታ እንደተወሰወረ የጉድጓድ ምንጭ›› እንዲል፡፡ ለሌሎቻችን በኃይማኖት ምክንያት የተሰወረች ነች -  አሽር ቤት፡፡

መጀመሪያ በአንድ ብር በኋም በአንድ ብር ከሃምሳ ያስተምሩ የነበሩት የደብረብርሃን አሽር ቤቶች ትልቅ ሚና እንደነበራቸው ገብቶኛል፡፡ በብዙ መቻቻልና አብሮነት የኖሩትን ጓደኞቻችንን አፍርተውልናል፡፡ የአረብኛ አጻጻፍ ከቀኝ ወደ ግራ ከመሆኑ ውጪ ምንም አላውቅም ነበር፡፡ ክርስቲያኖች የሙስሊሙን የሚማሩባቸው አጋጣሚዎች እንዳሉ ከሰው ሰምቻለሁ፡፡ ሙስሊሞችም የክርስቲያን ይማራሉ፡፡ ወዳጄ ወሎዬው ዑመር እንዳለው ዳዊት ደግሟል፡፡ ይሁን እንጂ ዳዊት ውስጥ ያሉት የታቦታት ስዕሎች ዳዊቱ ሲነበብ ስለማይታዩና በአብረቅራቂ ጨርቅ መሸፈን ሳላለባቸው ጨርቁን መግዣ ብር ስጪኝ ያላቸው እናቱ ‹‹ከእንግዲህ አትዳቁን፤ ማንበብ ከቻልክ ይበቃሃል›› ብለው እንዳስቆሙት ነግሮኛል፡፡ የአማርኛ ንባብ ለመቻል የቄስ ትምህርት ቤት ለሙስሊሞች ተመራጭ ነበር፡፡ አብሮነትንም ያስተምረናል፡፡ ሐውለት ስለቁርአን ትምህርት ስታወሳ በአእምሮዬ የነበረው ጥያቄ ዘመናዊ ትምህርቷን መቼ እየተማረች ነው የሚል የነበረ ሲሆን ከፈረቃ ውጪና ቅዳሜና እሁድ እንደምትማር ከመጽሐፉ ግማሽ በኋላ ሳነብ ምላሽ አገኘሁ፡፡ በሷ ዕድሜ ትምህርት በፈረቃ መሆኑን ማወቄ አስገርሞኛል፡፡ ምክያቱም እኔ ሳሲት ከአምስተኛ ክፍል በኋላ ነበር ፈረቃ የጀመርኩት፡፡ የአሽር ቤት ትምህርት ለእረፍት ወደ ሌሎች ቦታዎች ሲኬድ እንኳን የማይቋረጥ መሆኑ ገርሞኛል፡፡ ቁጥጥሩ ጥብቅ መሆኑ ለትምህርቱ ጥራት የራሱ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ የቅጣትና ሥነሥርዓት ሁኔታን ጠቀሜታ ደራሲዋ ገልጻዋለች፡፡ ይህም ለዘመናዊ ትምህርት ያለውን አስተዋጽኦ አንስታለች፡፡ የግእዙም አለው እንደሚባለው ነው፡፡ ትምህርት አሰጣጡ ፉክክርም መረዳዳትንም ያቀናጀ በመሆኑ ጥሩ ነው ባይ ነኝ፡፡   

ከዩኒቨርሲቲ ተመርቄ እንደመጣሁ የተቀጠርኩት ደብረብርሃን ነው፡፡ የተከራየሁበት ቤት መታጠቢያ ቤት ሰለሌለው መታጠቢያ የት እንደሚገኝ ስጠይቅ መስጊድ እንዳለ ነገሩኝ፡፡ ሄጄ ሳጣራም መስጊዱ ለገቢ ማመንጫ ታስቦ አገልግሎቱን እንደሚሰጥ ተረዳሁ፡፡ የተወሰነ ጊዜም ታጠብኩ፡፡ የመስጊድን ግቢ ሁኔታ ተረዳሁ፡፡ የመስጊዱ በረንዳም በጫማ የማይረገጥ መሆኑ ገባኝ፡፡ እነ መሬም ጋ ስላደግሁ የሙስሊም ፍራቻ ለቆኛል ለማለት እችላለሁ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአመጋገብ ሥርዓት የሙስሊምና ክርስቲያን በሚል በኢህአዴግ መንግሥት የተከፈለውን አመጋገብ ጥሰን እኔና ሊሻን ከናስር ጋር እንመገብ ነበር፡፡ ሻወሩም አላስደነገጠኝም፡፡ ኃይማኖትንና ኃይማኖተኞችን መጠራጠርና መጠየቅ ስጀመር ሃያ ዓመት እየተጠጋኝ ሲሆን በተለይ ለሙስሊሞች ግን ጥያቄዬና ሙግቴ ጠንከር ያለ የሆነው የአያን ሂርሲ አሊን ሁለት ማስታወሻዎች ወይም ‹ሚሟ› ስላነበብኩ፣ ንግግሮቿን ስለተከታተልኩ ብቻ ሳይሆን ብዙዎቹ ምዕራባውያን የኃይማኖት ነቃፊዎች ትኩረታቸው እስልምናን ማጥቃት ላይ ስለሆነ የዚያ ተጽዕኖ አለብኝ፡፡ የነሱ ምክንያት ክርሰትና በበቂ ሁኔታ ተተችቷል የሚልና ከአክራሪ እስልምና ፋር የተቆራኘ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ ሙስሊምን እንደ ቤተሰቤ እንደማይ የምረዳው ሙስሊም ጓደኞቼን ያለምንም ልዩነት ስቀርብ ነው፡፡ የሐውለትንም መጽሐፍ በፍቅር ሳነብ ያ እሳት የበለጠ ተቀጣጠለ፡፡ በሰፊው የሚወራላቸው ግን ያልሰራንባቸው እሴቶች አሉን፡፡ ለምሳሌ አብሮ የሚበላ ሕዝብ የሚለውን ላንሳ፡፡ አብሮ ሲበላ ብዙም ስላላየሁ የሃሳቡ ደጋፊ አይደለሁም፡፡ በትምህርት ቤት የተማርነው ወይም የሕዝቡን ትስስር ለማጉላት የመጣ ይመስለኛል፡፡ እውነት ከሆነ የበለጠ ቢሰራበት እናተርፍበታለን፡፡ የሙስሊም፣ ክርስቲያንና ሌሎች ኃይማኖቶች መቻቻልም ከወሬ ባለፈ ሊሰራበት እንደሚገባ የገባኝ የሐውለትን መጽሐፍ ካነበብኩ በኋለ ነው፡፡ አብሮነትን የሚሸረሽር ብዙ ድርጊት ስላለ ብዙ ስራዎች ይጠብቁናል፡፡ ስለ እውነት ለመናገር እኔ አብሮ የመብላቱን ነገር አለ ብዬ እንደማልቀበለው ሁሉ የኃይማኖት መቻቻል አለ የሚለውንም እምብዛም አልቀበለውም ነበር፡፡ አለማወቄን ግን ሐውለት አሳወቀችኝ፡፡

ከታሪካችን አብሮነትን የሚያጎሉትን ብንመርጥ ለዛሬም ሆነ ለወደፊት ሕይወታችን ጠቃሚ ይመስለኛል፡፡ ብዙ አማኝ ባለባት አገር አንዳንድ አፍራሽ ነገሮች ከብዙ ጎኖች ይሰማሉ፡፡ ለምሳሌ በወዳጄ በአሊሹ ሙሜ የተተረጎመውን የማልከም ኤክስን ታሪክ ሳነብ ያገኘሁት ጉዳይ አለ፡፡ ይኸውም ማልከም ከአሜሪካ ሐጂ ሄዶ ሁለት የእንግሊዝ ቅላጼ ባለው እንግሊዝኛ የሚናገሩ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ማግኘቱን የሚገልጽበት ነው፡፡ ኢትዮጵያ በክርስቲያን ነገሥታት ተጨቁነውና ቁጥራቸው ዝቅ ተደርጎ የሚኖሩ ሙስሊሞች የሚኖሩባት አገር ተደርጋ መገለጿ ትክክል ነወይ? ምን ይህ ችግር እኮ ከኃይማኖት ውጪም አለ፡፡ በብሔር አስተሳሰብ ውስጥ ያለ ጓደኛዬ በ2002 ዓ.ም. ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ መቻል እንጂ መቻቻል የለም›› ያለኝን ዓይነት አስተሳሰብ ሊሞገትና መልሶ ሊታይ አይገባውም ትላላችሁ? ብሔርና ኃይማኖት አብረናቸው ኖርንም ተውናቸው የሕይወታችንና የታሪካችን አካል መሆናቸው ስለማይቀር በመልካም ጎናቸው ቢጻፍባቸውና ብንነጋገርባቸው ይጠቅም ይመስለኛል፡፡

ሐውለት ከክርስቲያን ጓደኞቿ ጋር የቀረበ ግንኙነት አላት፡፡ ፎርፌ የምትፎርፍበት፣ ለውህ የምታስመልስበት፣ የፍቅር ደብዳቤ የምታመላልስበት፣ ፀጉሯን የምትሰራበት፣ ለክርቲያኖች የመዝሙር ዜማ የምትይዝበት፣ ሥላሴና ጊዮርጊስ አብያተክርስቲያኖች የምትገባበት፣ ቡሄ የምትጨፍርበት ገጠመኝ ሁሉ ከቤተዘመድና ቤተሰብ ወግ ጋር ሳቢ ነው፡፡ መጽሐፏ ደብረብርሃንን ከሙስሊም ዕይታ ለማየትም ጠቃሚ ነው፡፡

በልጆች ዓለም ያሉ እንደ አፈር መብላት፤ በነፍሳት፣ በአይጦችና በሳማ ሰውን ማስፈራራት፣ በኤሊ መጫወት፣ ድንኳን መስበር፣ አለቅነት፣ ዘመድ ጥየቃ ወዘተ የመጽሐፉ ጌጦች ናቸው፡፡ የሐውለት የእርግብ እርባታ ታሪክ ራሱን የቻለ መጽሐፍ የሚወጣው ሙያና ታሪክ ይመስለኛል፡፡ ተመሰጡበት፡፡

በ1980ዎቹ የነበረችውን ደብረብርሃን ከተማን በሚገርም ሁኔታ ገልጻታለች፡፡ መንገዶቹ፣ ቤቶቹ፣ ጋሪዎቹ፣ ሰዎቹ፣ የእምነት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶቹ፣ ብቻ ምንም አልቀራትም፡፡ ስለ ጋሪዎቹ ስትጽፍ የደብረብርሃን ፈረሶች የሚል ጻፍኩትና በድረገጽ የታተመ አንድ የልጆች መጽሐፌን ትዝ አስባለችኝ፡፡ አሽር ቤቱ አጠገብ ያሉት ዉኃ የሚሰጧቸው እናት የሳሲት ትምህርት ቤት ጎረቤት ደጋግ እናቶችን አስታወሰኝ፡፡ የወታደሮች ኮቸሮ፣ የሚሰግዱት ወፎች፣ የወር እንትን፣ የቁርዓን ገጾች፣ የመስጂድ ሐቅ፣ ሂጃብ አስተሳሰር፣ የሚሚ ኩበቶች ብቻ ሃሳቦቹና ርዕሶቹ የተስፋየ ገብረአብን አጓጊ ርዕሶች አስታወሱኝ፡፡ እናንተም የመሐመድ ሰልማን ወይም የአቤል የአዲስ አበባ ጉዶች አጻጻፍ ዘዬ ትዝ ሊላችሁ ይችላል፡፡ ሌላው ጉዳይ ርዕሱን አይቶ ለመገመት አለመቻሉ መጽሐፉን ማንበብና የጉዳዩን ምንነት እስኪያውቁ ድረስ ልብ መሰቀሉ አይቀርም፡፡  

የሙስሊሞችን የዓለም እይታ ለመረዳት ብዙ ማንበብና መጠየቅ እንዳለብን አሁን እየገባኝ ነው፡፡ ልጆቻችውን በኃይማኖታቸው ለማትጋት አሽር ቤት የሚልኩትን ወላጆች ማድነቅም አለብን ተረድቻለሁ፡፡ ለካ የጉዳየን ጫፍ ነው ገና የያዝነው፡፡ መጽሐፉን አስመልክቶ የተሰማኝንና የመጣልኝን አወጋሁ እንጂ እናንተ አንብባችሁ ምን አንደምትሉ አላውቅም፡፡ እኔ በበኩሌ ታሪኩ በተፈጸመበት ከተማ የተመረቀውን ይህን መጽሐፍ በዚያችው ከተማ ማንበቤ ልዩ ስሜት አሳድሮብኝ ስላለቀብኝ ግን ተበሳጨሁ!

መልካም ንባብ!

 

2023 ፌብሩዋሪ 2, ሐሙስ

ለብዙዎቻችን የባከኑብን ዕድሎች

"I knew it was bad behavior. I knew it was wrong. My mates knew too. We talked about it often, while stoned, how stupid we were to be wasting an Eton education." 

Spare, Prince Harry, The Duke of Sussex, page 83.

"መጥፎ ባህሪ እንደነበረ አውቅ ነበር። ስህተት እንደነበረ አውቅ ነበር። ደባሎቼም ያውቁ ነበር።  በኤቶን ትምህርት ቤት ለመማር ያገኘነውን ዕድል በማባከናችን ምን ያህል ደንቆሮዎች እንደነበርን አደንዛዥ ዕፅ እያጨስን በምንደነዝዝባቸው በአብዛኞቹ ጊዜያት እናወራ ነበር።"

ስፔር (ቅያሪ)፣ ልዑል ሃሪ፣ የሰሴክሱ ዲዩክ፣ ገጽ 83 


ይህችን ገጽ አንብቦ ብቻ ማለፍ ይከብዳል። ብዙዎች ያላገኙትን የመማር ዕድል ያገኘን ስንቶቻችን እንደ ልዑሉና ጓደኞቹ ሁሉ አባከንነው! እነሱ ያባከኑት ዕፅ እያጨሱ ነው። ከሱሰኝነት ጉዳይ ዉጪ እንነጋገር። የመማር ዕድሉን ተጠቅመን የወጣብንን ያህል ወይም ከዚያ በላይ ማበርከት እንዴት ተሳነን? ለትምህርት ዓላማ የወጣው ገንዘብ፣ ጊዜ፣ ጉልበት ወዘተ ሲታሰብ ትርፉ የዚያን ያህል አይመስልም። በእርግጥ የትምህርት ሥርዓቱ በጥራት የማስተማርና የመከታተል ችግር ይኖርበታል። ከትምህርት ዉጪ ያሉ የኑሮ ጫናዎችም ይኖራሉ። ቤተሰብና አካባቢም ሚናቸው አይካድም። የሆነው ሆኖ ግን የኃይለማርያም ማሞ፣ የምኒልክ፣ የጥቁር አንበሳ፣ የአብዮት ቅርስ ወዘተ የትምህርት ዕድልና ልፋት ፍሬውና ምርቱ በጣም ብዙ መሆን ሲገባው የሆነ አይመስልም። የኔልሰን ማንዴላ የፎርት ሄር ትምህርት ብዙ እንዳፈራው አልሆነልንም። ከዚያም በመለስ አልሆነም። ይህን በወቅቱ እናውቀው ነበር? ካወቅነው ምን እርምጃ ወሰድን? ይህን ጉዳት እንደ አገር አስበነዋል? ወይስ አንድ መምህር የዩኒቨርስቲ የሕክምና መምህራንን የወር ደሞዝና ጥቅማጥቅም አስቦ መቶ ሺ ብር አድርሶ በትጋት አለመማሩ እንደቆጨው ከጥቅም አንፃር ብቻ እናስብ ይሆን? ከአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ በኋላስ? በኮሌጅስ? በዩኒቨርሲቲስ? የተሰጠንን ዕድል ተጠቀምን ወይንስ ዕድሜያችንን ጨረስን? በስራ ቦታስ? በአጠቃላይ ሕይወታችንስ? ዓላማ አለን?

አስባችሁት ታውቃላችሁ?

2023 ጃንዋሪ 27, ዓርብ

Paradox, Flash Fiction


Mezemir G.

 

Gete is three-quarters Habesha and a quarter Greek. And who knows for sure what Habesha blood those three-quarters include? Nobody knows the ethnic composition of the others sitting in the hall either. But it is said that most of the time Tigrians, the ruling ethnicity, and a few other sympathizers of the regime frequent such meetings. Anyways, the secret team at the embassy makes sure they have the ethnic profiles of the embassy’s visitors. For the government embassy is a place to trap the diaspora as the river is to trap antelopes for crocodiles. The embassy tries to get their favor for the normal services they get. Gete is sitting in the meeting hall of the Ethiopian Embassy in Berlin. A middle-aged working woman as she is, her days are occupied with lots of activities. Be it as it may, she unusually decided to take part in this affair of Ethiopia, the county she emigrated from as child when the Communist Junta took over.  

She was not sure what to do, say or think. She is there to find out what is going on with the Grand Ethiopian Renaissance Dam. The progress of the dam’s construction seems to go well as the presenter is saying but she smelt a rat. There is news that is coming from both America-and-Europe-based diaspora news outlets that the placement of the dam is not as it should have been. The Tigray-led government is said to anex the dam into greater Tigray. The highly corrupted Metals and Engineering Corporation (METEC) is said to have misused the money that is meant for the construction. There are numerous purported problems with the way the Ethiopian government of EPRDF is handling the dam and leading the country. The dam’s project is too politicized, yet it has also attracted the attention of Ethiopia’s longtime enemies and international powers.

Amid all these, she doesn’t know what to think. Whether she has to oppose or support is not clear to her. She knows how the system is using the divide and rule policy to control Ethiopia. If she supports the project, she may donate too. She took the microphone. Everyone is expecting what this newcomer is about to say. Would she be in for a surprise?  

She gave feedback. Leaving all the ethnic politics and corruption behind she has hope that Ethiopia shall unite. As the granddaughter of a Greek engineer who was killed by the Italians when they invaded Ethiopia in 1936, she feels she is responsible. The engineer was employed by the Ethiopian government and he lived at Dedesa studying the possibilities of building a dam on the Nile when the Italians took over. He died with his secrets. A piece of his secrets only seems to work through his bloodline. The same people who killed him, the Italians, are in Ethiopia building dams and electric power generating plants including the GERD. “A country of paradoxes!” she scribbled in her notebook a moment before she pledged 1,000 Euros and left out not giving in for the announcement of a cocktail.

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...