2016 ማርች 19, ቅዳሜ

መጻሕፍት



ጤና ይስጥልኝ፣
በደብረብርሃን ከተማ የጀመርነው መጻሕፍትን ባሉበት የማድረስ ተግባራችን በይፋ ተጀምሯል፡፡ የሚፈልጉትን መጻሕፍት ይዘዙን፡፡ የምንሰጣቸው አገልግሎቶች፡-
1. የራስዎ አነስተኛ የመጻሕፍት ስብስብ እንዲኖርዎት እናግዛለን (የመጻሕፍት መደርደሪያ ሞዴሎችን እናቀርባለን)
2. ምን እንደሚያነቡ እናማክራለን
3. የንባብ ችግር ካለብዎት እናግዛለን
4. በኢንተርኔት፣ በስልክ፣ በሶፍት ኮፒ ሱስ ከተጠመዱ ወደ መጽሐፍ እንዲመጡ እናደርጋለን፡፡ (እንደ እኔ)
4. የፍጥነት ንባብ (speed reading with a better comprehension) እናለማምዳለን
5. ያገለገሉ መጻሕፍትን እንገዛለን፡፡ ገዝተውት ሳያነቡት የተቀመጠ መጽሐፍ ካለ ለምን ሸጠውልን ሌሎች አያነቡትም? መጻሕፍትን ከእስር ነጻ እናውጣቸው!
6. እናከራያለን (የሚከራዩት ገንዘብ አስይዘው ሲሆን፤ ክፍያው በቀን ሁለት ብር ነው፡፡)
7. ከእኛ የገዙትን መጽሐፍ አንብበው ከአንድ ሳምንት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ንጽሕናውን እንደጠበቀ ከመለሱልን ከዋጋው በ60 ፐርሰንት እንገዛለን፡፡
8. ከእኛ የገዙትን መጽሐፍ ማንበብዎን በስልክና በኢንተርኔት እንከታተላለን
9. መጽሐፍ ለሚያሳትሙ ደራሲያን የምክር አገልግሎት እንሰጣለን
10. የመጻሕፍት ውይይት እናካሂዳለን
11. የመጻሕፍት ዕቁብ እናስጀምራለን፤ መጻሕፍቱን እናቀርባለን፤ በቡድኑ ምን ይነበብ በሚለው ላይ እናማክራለን
12. በሌሎች ከተሞችም የመጻሕፍት ሽያጭና እኛ ከምንሰራው ጋር የሚመሳሰል ስራ ለመጀመር ለሚያስቡ የምክር አገልግሎት እንሰጣለን፡፡
ሌላ ምን አገልግሎት ብንጨምር ጥሩ ነው ትላላችሁ? ለተጨማሪ መረጃ በ 0913 6588 39 ወይንም 0970 38 10 70 ይደውሉ፡፡ ጊዜያዊ ማዕከላችን ጓሳ ቡና ሲሆን መገኛውም ደብረብርሃን፣ ጠባሴ፣ ከእርሻ ሰብል ፊት ለፊት ነው፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...