ሐሙስ 10 ማርች 2016

አንድን ትምህርት በሁለት ቋንቋ የምታስተምሩ ሆይ!




በቅርቡ ወደ አንድ የግል ትምህርት ቤት ሄጄ ከመምህራን ጋር በምነጋገርበት ወቅት አንድን ትምህርት በሁለት ቋንቋ እንደሚያስተምሩ ነገሩኝ፡፡ ይህም ማለት ሂሳብንና ሳይንስን የመሳሰሉትን ትምህርቶች በአማርኛም በእንግሊዝኛም ያስተምራሉ፡፡ ነገሩ የወላጆችንም የመንግስትንም ፍላጎት ለማሟላት መሆኑ ነው፡፡ በአንድ በኩል ወላጅ ልጁ በእንግሊዝኛ እንዲማርለት ይሻል፤ በሌላ በኩል ደግሞ መንግስት በአፍ መፍቻ ቋንቋ አስተምሩ ይላል፡፡ በመሃል ቤት ተማሪው ጫና ያርፍበትና አሥራ ምናምን ትምህርት እንዲማር ይገደዳል፡፡ አሥራ ምናምን የሚገባው ኮምፒውተሩ፣ የእንግሊዝኛ ንግግሩ ሲጨማመር ነው፡፡ በግል ትምህርት ቤቶች የተሻለ የትምህርት አሰጣጥ መኖሩ ባይካድም ተማሪው ግን ይህ ጫና ሊወገድለት ይገባል - በአንዱ ቋንቋ ብቻ ሊማር ይገባዋል፡፡ ይህን ጉዳይ የሚከታተሉት የትምህርት ሹማምንት ትምህርት ቤት ድረስ ሄደው ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ሰምቻለሁ፡፡ ተማሪዎቹ በሁለት ቋንቋ አይማሩም የሚል አቋም አላቸው፡፡ አንድ ቅር የሚያስብለው ነገር ግን ግብረገብንና ግዕዝና የመሳሰሉት ትምህርቶችም ሊሰጡ አይገባም መባሉ ነው፡፡ የትምህርቱ ጠቀሜታ እየታየ ተማሪዎች እንዲማሩት ቢደረግ ክፋቱ አይታየኝም፡፡ እርስዎ ስለዚህ ጉዳይ የተሻለ የሚያውቁ ከሆነ ሃሳብዎን ያጋሩኝ፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ብሔራዊ አገልግሎት ሲነሣ

 ብሔራዊ አገልግሎት ሲነሣ  ከ2008 ዓ.ም. ያለኝ በኢትዮጵያ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጊዜ የነበረው ብሔራዊ አገልግሎት በሚገባ የተጠና ነው። ከረጅም ዓመታት በፊት በጉዳዩ ላይ መጻሕፍትንና አጫጭር ጽሑፎችን ያነበብኩ ይመስለኛ...