በቅርቡ ወደ አንድ የግል ትምህርት ቤት ሄጄ ከመምህራን
ጋር በምነጋገርበት ወቅት አንድን ትምህርት በሁለት ቋንቋ እንደሚያስተምሩ ነገሩኝ፡፡ ይህም ማለት ሂሳብንና ሳይንስን የመሳሰሉትን
ትምህርቶች በአማርኛም በእንግሊዝኛም ያስተምራሉ፡፡ ነገሩ የወላጆችንም የመንግስትንም ፍላጎት ለማሟላት መሆኑ ነው፡፡ በአንድ በኩል
ወላጅ ልጁ በእንግሊዝኛ እንዲማርለት ይሻል፤ በሌላ በኩል ደግሞ መንግስት በአፍ መፍቻ ቋንቋ አስተምሩ ይላል፡፡ በመሃል ቤት ተማሪው
ጫና ያርፍበትና አሥራ ምናምን ትምህርት እንዲማር ይገደዳል፡፡ አሥራ ምናምን የሚገባው ኮምፒውተሩ፣ የእንግሊዝኛ ንግግሩ ሲጨማመር
ነው፡፡ በግል ትምህርት ቤቶች የተሻለ የትምህርት አሰጣጥ መኖሩ ባይካድም ተማሪው ግን ይህ ጫና ሊወገድለት ይገባል - በአንዱ ቋንቋ
ብቻ ሊማር ይገባዋል፡፡ ይህን ጉዳይ የሚከታተሉት የትምህርት ሹማምንት ትምህርት ቤት ድረስ ሄደው ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ሰምቻለሁ፡፡
ተማሪዎቹ በሁለት ቋንቋ አይማሩም የሚል አቋም አላቸው፡፡ አንድ ቅር የሚያስብለው ነገር ግን ግብረገብንና ግዕዝና የመሳሰሉት ትምህርቶችም
ሊሰጡ አይገባም መባሉ ነው፡፡ የትምህርቱ ጠቀሜታ እየታየ ተማሪዎች እንዲማሩት ቢደረግ ክፋቱ አይታየኝም፡፡ እርስዎ ስለዚህ ጉዳይ
የተሻለ የሚያውቁ ከሆነ ሃሳብዎን ያጋሩኝ፡፡
የጉዞ፣ የንባብ፣ የቤተመጻሕፍት ፣ የሕትመትና ስርጭት ወዘተ ጽሑፎችን ያገኙበታል። I share my views and reports of my activities in this blog.
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
From my diary
“Are all of these professors?” “You’re not really busy. You do nothing!” These two statements were made by two American volunteers who...
-
6 June 2019 Basic Writing Skills (Sophomore English) Lecture 1.1. Phrases and Clauses 1.1.1. Phrases A phrase can ...
-
ካሚሪቱ በኬኒያ በሚገኘው የካሚሪቱ የማህበረሰብ ትምህርትና ባህል ማዕከል የናይሮቢ ዩኒቨርስቲ መምህራን የጀመሩት በኬኒያ የመጀመሪያው የአፍሪካ ቋንቋና ከአዳራሽ ዉጪ ቲአትር ሲሆን በቅኝገዢውም ሆነ ከነፃነት በኋላ በመጣው...
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ