በቅርቡ ወደ አንድ የግል ትምህርት ቤት ሄጄ ከመምህራን
ጋር በምነጋገርበት ወቅት አንድን ትምህርት በሁለት ቋንቋ እንደሚያስተምሩ ነገሩኝ፡፡ ይህም ማለት ሂሳብንና ሳይንስን የመሳሰሉትን
ትምህርቶች በአማርኛም በእንግሊዝኛም ያስተምራሉ፡፡ ነገሩ የወላጆችንም የመንግስትንም ፍላጎት ለማሟላት መሆኑ ነው፡፡ በአንድ በኩል
ወላጅ ልጁ በእንግሊዝኛ እንዲማርለት ይሻል፤ በሌላ በኩል ደግሞ መንግስት በአፍ መፍቻ ቋንቋ አስተምሩ ይላል፡፡ በመሃል ቤት ተማሪው
ጫና ያርፍበትና አሥራ ምናምን ትምህርት እንዲማር ይገደዳል፡፡ አሥራ ምናምን የሚገባው ኮምፒውተሩ፣ የእንግሊዝኛ ንግግሩ ሲጨማመር
ነው፡፡ በግል ትምህርት ቤቶች የተሻለ የትምህርት አሰጣጥ መኖሩ ባይካድም ተማሪው ግን ይህ ጫና ሊወገድለት ይገባል - በአንዱ ቋንቋ
ብቻ ሊማር ይገባዋል፡፡ ይህን ጉዳይ የሚከታተሉት የትምህርት ሹማምንት ትምህርት ቤት ድረስ ሄደው ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ሰምቻለሁ፡፡
ተማሪዎቹ በሁለት ቋንቋ አይማሩም የሚል አቋም አላቸው፡፡ አንድ ቅር የሚያስብለው ነገር ግን ግብረገብንና ግዕዝና የመሳሰሉት ትምህርቶችም
ሊሰጡ አይገባም መባሉ ነው፡፡ የትምህርቱ ጠቀሜታ እየታየ ተማሪዎች እንዲማሩት ቢደረግ ክፋቱ አይታየኝም፡፡ እርስዎ ስለዚህ ጉዳይ
የተሻለ የሚያውቁ ከሆነ ሃሳብዎን ያጋሩኝ፡፡
የጉዞ፣ የንባብ፣ የቤተመጻሕፍት ፣ የሕትመትና ስርጭት ወዘተ ጽሑፎችን ያገኙበታል። I share my views and reports of my activities in this blog.
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ሕይወት ከእገታ ማስጠንቀቂያው በኋላ
ሕይወት ከእገታ ማስጠንቀቂያው በኋላ ግንቦት 10፣ 2018 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን ሚያዝያ 26 ፣ 2018 ዓ . ም . ምሽት የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ደረሰኝ...
-
6 June 2019 Basic Writing Skills (Sophomore English) Lecture 1.1. Phrases and Clauses 1.1.1. Phrases A phrase can ...
-
የሥኬት ሥልጠና ቡድናችን አባላት አርፍደው ስለነበር ከቀኑ 11፡00 ሳይሞላና የፋብሪካው ዋና ዋና ዘመናዊ የሥራ ክፍሎች ሳይዘጉብኝ ብቻዬን ከራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት ወደ ጅሩ መስመር በእግሬ በጥድፊ...
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ