2021 ጁላይ 24, ቅዳሜ

የፆም ጣዕም

 

ደራሲው በፆም ክብደቱን ለመቀነስና ጤናማ ለመሆን የቻለ በቀን አንድ ጊዜ ተመጋቢ ነው፡፡ የፆምን ሕይወት
በተግባር እየኖረ፣ ሌሎችን እያማከረና ከዓለም ዙሪያ የተጻፉ ምርምሮችን እያነበበ ያዘጋጀውን ይህን መጽሐፍ
ይዞላችሁ ቀርቧል፡፡
 ‹‹በወለድኩ ቁጥር ክብደቴ ይጨምራል እንጂ አይቀንስም፡፡ ራሴን ጠልቼ ነበር፡፡ ገመድ ብዘልም
አልቀነስኩም፡፡ ስሮጥ መንገዱ አይመቸኝም፡፡ መንገድ ላይ በምሮጥበት ጊዜ አላስፈላጊ ነገር የሚናገሩኝም
ሰዎች ያናድዱኛል፡፡ በፆምና በቀላል እንቅስቃሴ የምፈልገው ክብደት ላይ ለመድረስ ችያለሁ፡፡›› ደራሲው
በከፈተው የመማማሪያ መድረክ የተለወጠች ግለሰብ
 አንድ ሰው በዕድሜ ዘመኑ 540 ኩንታል ምግብ ይመገባል፡፡
 አንድ ጤነኛ ሰው ዉኃ ካገኘ ያለምግብ ሁለት ወራት ለሚጠጋ ጊዜ መቆየት ይችላል፡፡
 በዓለም ዙሪያ 2.8 ሚሊዮን ህዝብ በምግብ በሚመጣ ውፍረት ምክንያት ይሞታል፡፡ በኢትዮጵያ የውፍረት
መጠን ከሃያ በመቶ በላይ ነው፡፡ ከልክ በላይ ውፍረት ደግሞ ከስድስት በመቶ በላይ ነው፡፡ እርስዎ በእጅዎ
ባለው የማያስከፍል ያለመብላት ውሳኔ ጤናማ መሆንና ሕይወትዎን መታደግ ይችላሉ፡፡
 በቀን ሦስቴ መመገብ ከጥቂት መቶ ዓመታት ወዲህ የመጣ ነው፡፡ ባህላዊ እንጂ ሥነሕይወታዊ ምክንያትም
የለውም፡፡
 ቀኑን ሙሉ መብላት ትክክለኛ የአኗኗር ዘይቤ አይደለም! ከቁርስ፣ ምሳ፣ እራት አባዜ እንውጣ! ከምንበላው
እኩል ስለምንበላበት ጊዜ እንወስን፡፡ ከምግብ በኋላ ረጅም ጊዜ ስንቆይ ሰውነታችን ስብን ለማቅለጥ፣
ለመታደስና በሽታን ለመከላከል ዕድል ያገኛል፡፡
 የጤናችንን ሁኔታ በቀላሉ ለማወቅ፣ መመገብ ስላለብን ምግብ ይዘት ለመገንዘብ፣ የፆምን አሰራር
ለመረዳትና ስለምግብ ጥያቄያችን መልስ ለማግኘት የሚረዳን መጽሐፍ!
 ገንዘብዎን ይቆጥቡ፣ ጤናዎን ይጠብቁ፣ ዕድሜዎን ያርዝሙ፣ ጤናማ የአመጋገብ ስርዓት ይከተሉ!


3 አስተያየቶች:

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...