የሰቆጣ ሰዎች በድርቅ ምክንያት በ2008 ዓ.ም. ተፈናቅለው ደብረብርሃን እንደመጡ አንዷ ተፈናቃይ የነገሩኝን ከቆየ ማስታወሻዬ አገኘሁት፡፡
‹‹ክረምት ሲመጣ ተበዳድረን ነው፡፡ ሐብታም የሆነ ችግርን ሊገፋው ይችላል፡፡ የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ ክፈሉ ይሉናል፡፡ እኛ ግን የሚከፈል የለንም፡፡
እርዳታው ከመንግስት ይወጣል መሰል፡፡ ለእኛ ግን አይደርሰንም፡፡
እርዳታ እንደሚያስፈልግ ያወቅነው በሰኔ ነው፡፡
ከመምጣታችን በፊት ከብቶቻችንን አርደን በላን፡፡ የሚጠጣ ውሃ የለም፡፡
እዚህ መጥቼ ቁጭ ብዬ እስከ 7፡00 ድረስ አለቀስኩ፡፡ ወንድሜ ‹ምን አባሽ ያነፋርቅሻል! ሄደሽ እንሰዉ አትለምኚም እንዴ!› አለኝ፡፡ አገሬ ልሂድ ብለው ‹እንዴት አድርገሽ? 300 ብር ከየት ታመጫለሽ?› አለኝ፡፡
አገሩ አዝመራው ጥሩ ነው ስንባል ጊዜ ወደዚህ ወደ ደብረብርሃን መጣን፡፡
ብርድ ሞትን እዚህ፡፡››
አሁንም አሉ፡፡ መፍትሔ ቢፈለግላቸው ጥሩ ይመስለኛል፡፡
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ