2021 ኤፕሪል 23, ዓርብ

‹‹ዓለም ጭፍጨፋ ሲካሄድ ፀጥ ይላል፤ ጭፍጨፋው ሲያልቅ መታሰቢያ ያደርጋል›› የሆሎኮትስ መታሰቢያ ሙዚየም (ያድ ቫሸም) ጉብኝትና ለኢትዮጵያ ያለው ጠቀሜታ

 

ዓለም ጭፍጨፋ ሲካሄድ ፀጥ ይላል፤ ጭፍጨፋው ሲያልቅ መታሰቢያ ያደርጋል

የሆሎኮትስ መታሰቢያ ሙዚየም (ያድ ቫሸም) ጉብኝትና ለኢትዮጵያ ያለው ጠቀሜታ

መዘምር ግርማ

ሚያዝያ 13፣ 2013 ዓ.ም.

በእስራኤል የሆሎኮስት መታሰቢያ ሙዚየም (ያድ ቫሸም) ያዘጋጀውን ጉብኝት ለኢትዮጵያውያን መምህራን ትልቅ ጠቀሜታ ያለውና ለሃገራችንም እጅግ ወቅታዊ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡ ከኢትዮጵያ ኢምባሲ አምባሳደር ረታ ዓለሙና አቶ ኑርሁሴን ኑሩ ባደረጉልን ግብዣ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የሚዲያ ተቋማት የተውጣጣን ሰዎች ሁለት ሰዓት በፈጀው ጉብኝት ላይ ተሳትፈናል፡፡ 

ከጉብኝቱ በፊት ለተወሰኑ ቀናት ባደረኩት ንባብና ዳሰሳ ስለ አይሁድ ህዝብ ስደት (ዲያስፖራ) እና ለሺዎች ዓመታት በዓለም ዙሪያ ስለዘለቀው የዘርፍጅት፣ የመሳደድና የሃገር አልባነት ታሪክ ለመረዳት ችያለሁ፡፡  የአይሁድ ህዝብ ወደ ሃገራቸው ተመልሰው ሃገራቸውን መስርተው ያለፈውን ለመመርመር፣ የአሁኑን ህይወታቸውን ለማቃናትና ለወደፊቱም በሚገባ ለመዘጋጀት እንደቻሉም ተረድቻለሁ፡፡

በጉብኝቱ ዕለትም ለአንድ ሰዓት ተኩል ስለሙዚየሙ ገለጻ ተደርጎልናል፡፡ የቪዲዮ ጉብኝትም አድርገናል፡፡ በዕለቱ ከሙዚየሙና የምርምር ተቋሙ ሦስት እስራኤላውያን የተሳተፉ ሲሆን በሚገባ ገለጻ ድርገውልናል፡፡ አወያይተውናል፡፡ ውይይቱ ሲጀምር አቶ ኑርሁሴን ኑሩ በሰጡኝ ዕድል ራሴንና ስራዬን እንደሚከተለው አስተዋውቄያለሁ፡፡ በአንዲት ሩዋንዳት የተጻፈ መጽሐፍ ‹ሁቱትሲ› በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ መተርጎሜንና ለንባብ ማብቃቴን ገልጫለሁ፡፡ ይህንኑ መጽሐፍም ወደ አፋን ኦሮሞ አስተርጉሜ ለህዝቡ አዳርሻለሁ፡፡ በትግርኛም ተተርጉሟል፡፡ በሚዲያ ስለ ዘረኝነት አስከፊነት ለተለያዩ ሚዲያዎች ቃለመጠይቆች ሰጥተናል፡፡ የኔ ጥረት ህብረተሰቡ ላይ ግንዛቤ ፈጥሯል፡፡ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ባለስልጣናትና ፖለቲከኞች ዘንድ ግን መድረሴን እርግጠኛ እንዳልሆንኩ ተናግሬያለሁ፡፡

በ1953 የተመሰረተው ይህ ሙዚየም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በአውሮፓ በፀረ-ሴማዊ ዘረኛ አይዲዮሎጂና ፕሮፓጋንዳ ምክንያት ሕይወታቸው ላለፈው አይሁዶች መታሰቢያ ነው፡፡ ጥላቻ የሚያስከትለውን ጉዳትና በማናቸውም ቦታ የምንገኝ የሰው ልጆች በሰብዓዊ ፍጡር ላይ ማድረግ ስለማይገቡን መጥፎ ነገሮች ያስተምራል፡፡ የዓለምአቀፉ ፖለቲካም የዘርማጥፋትን ለመከላከል ፍላጎት ያሳየበት እነዚህ ተመራማሪዎች የሚያውቁት ጊዜና ክስተት እንዳልነበረ ገልጸውልናል፡፡ ዓለም ጥሩ የሆነችው የዘርማጥፋት ከተፈጸመ በኋላ ሰለባዎቹን በማስታወስ ነው ብለውናል፡፡

የያድ ቫሸም የቪዲዮ ጉብኝት በተሳካ ሁኔታ ሲጠናቀቅ ግንዛቤያችንን በሚገባ አሳድጎታል ለማለት እችላለሁ፡፡ ለአስርት ዓመታት በጉዳዩ ላይ የተመራመሩ ምሁራን ያደረጉልን ገለጻ ትምህርት ሰጪ ነበር፡፡ በመጨረሻ የጥያቄ ዕድል ተሰጥቶ ሁለት ጥያቄዎችን ጠይቄያለሁ፡፡ እነሱም

ሀ. ያደረጋችሁልን ገለጻ በጣም አስተማሪ ነው፡፡ የአይሁድ ሕዝብና ጀርመን አሁን ሰላማዊ ግንኙነት ማድረጋቸው ከጥፋት በኋላም እንኳን ሰዎች ተራርቀው እንደማይራራቁ አስተማሪ ነው፡፡ የዘርማጥፋት አደጋን ለማስወገድ ግን አሁን ካለንበት የእሳት ማጥፋት ደረጃ አንጻር በቀጥታ ሚና ያላቸው ፖለቲከኞቹ ላይ የእስራኤል መንግስት ግፊት አድርጎ ብሄራዊ እርቅ ቢደረግ አይሻልም ወይ?

ለ. እናንተ ተመራማሪዎቹ በዚህ በአይሆዶች የዘርማጥፋት ጉዳይ ላይ ዘወትር ስታነቡ፣ ስትወያዩና ስትመራመሩ አእምሯችሁ አይጎዳም ወይ? እኔ በግሌ ስለገጠመኝ ነው፡፡

ስለ መጽሐፌ ስለ ሁቱትሲ ለመግለጽ ያህል የዚህን መጽሐፍ የእንግሊዝኛ ቅጂ ያገኘሁት በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ቤተመጻሕፍት በ2007 ዓ.ም. ነበር፡፡ መጽሐፉን ሳነበው ከሩዋንዳ የቱትሲ ዘርማጥፋት ሂደት አንጻር ኢትዮጵያ እየሄደችበት ያለው ዘር ተኮር ፖለቲካ አሰጋኝ፡፡ ስለሆነም በ2008 ዓ.ም. መጽሐፉን ተርጉሜ አሳተምኩ፡፡ በህብረተሰቡም ዘንድ ስለዘር ጥላቻ አደገኛነት ውይይትን ለማጫር በቃ፡፡ በ2012 ዓ.ም እንደገና መጽሐፉን በማሳተም 2ኛ፣ 3ኛና 4ኛ ዕትም አውጥቼ ለማሳተም በቃሁ፡፡ ወደ ኦሮምኛም ያስተረጎምኩት ህዝቡ በሚችለው ቋንቋ ሃሳቡ እንዲደርሰው በማሰብ ነው፡፡ ከትግርኛው ተርጓሚም ጋር በመገናኘት የሚዲያ ቃለመጠይቆች ሰጥተናል፡፡ መጽሐፉ እየሄደበት ያለው ፍጥነትና በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የዘር ማጥፋት አሳሳቢነት ስላልተመጣጠነ መጽሐፉን በፒዲኤፍ ለህብረተሰቡ በነጻ ለመልቀቅ ወስኜ ለቅቄያለሁ፡፡ ይህም በተለይ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ የሆኑና በክፍለሃገር የሚገኙ ወጣቶች እንዲያገኙት በማሰብ ነው፡፡ ደርሷቸው አንብበው የሚደውሉልኝ አሉ፡፡ ‹‹ዘረኛ ነበርኩ፤ ከአሁን በኋላ ግን አልሆንም!›› የሚል መልዕክት የላከልኝም አንባቢ አለ፡፡

በጉብኝቱ የቱትሲና የአይሁዶች የዘርማጥፋት ስላላቸው ተመሳሳይነት ለማወቅ ችያለሁ፡፡ ይህም የሆነው ገለጻ አድራጊዎቹ ከተናገሩትና ራሴም ከወሰድኩት ግንዛቤ ነው፡፡ ተመሳስሎው የዘር ጥላቻን ከመቀስቀስ አንጻር፣ ፍጅቱ ሴትንም ሆነ ህጻናትን ካለመማሩ አንጻርና ከአደረጃጀቱ ሁኔታ አንጻር ነው፡፡  

ለማጠቃለል ያህል የዘርማጥፋት ስጋት ለዛሬ ለነገ የምንለው አይደለም፡፡ ህብረተሰቡን ማስተማር ይገባናል፡፡ ታዋቂ ሰዎችን፣ ምሁራንን፣ ፖለቲከኞችን፣ ጄኔራሎችን ሳይቀር ተጽዕኖ ፈጣሪዎችን ማስተማር አለብን፡፡ ምክንያቱም ከዘር ማጥፋት የሚያተርፍ ስለሌለና በሆሎኮስትም ሆነ በሩዋንዳ እንደታየው የዘርማጥፋትን ደግፎና አካሂዶ ከተጠያቂነት የሚያመልጥ እንደሌለ ለማስገንዘብ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ጥሩ አስተዳደር ካገኘች ለሁሉም ህዝብ የሚበቃ ሃብት ያላት ሃገር ነች፡፡ በኢትዮጵያ የሚኖሩ የተለያዩ ህብረተሰቦች በሰላም የሚኖሩት የዘር ጥላቻንና ዘርተኮር ፖሊሲን ስናስወግድ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ በውይይትና በመግባባት የነገውን የሃገራችንን እጣ ፈንታ ለማስተካከል እንችላለን፡፡ ለዚህም በያድ ቫሸምና በኢምባሲችን የተጀመረው የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃግብርና ድጋፍ እንዲቀጥል ያስፈልጋል፡፡

 


2021 ኤፕሪል 8, ሐሙስ

Staff Life at University

 After class, I headed to the lounge. On my way, I saw students and familiar faces of staff from the university. I greeted those who saw me. Outside the lounge, I met a lecturer of English. He was washing his hands to have breakfast. He is always playful and one you would love to be with. 

We went in together and ordered. The price of food and drinks at this place is way cheaper than outside the university. This is because the place is subsidized. Th price reminds me of someone’s idea of ‘’the Emperor is still alive at this place’’. He is comparing this place and time with the good olden days. Not only the food, the talk at the lounge is not available anywhere. I got wonderful new ideas from lecturers and professors from various fields of study. These staff come and chat with fellow likeminded staff members. From the colleges of natural science, social science, agriculture, law, engineering, medicine and computing different ideas come together. It is at this place that ideas start. If ideas come together like this and melt together, they can transform individuals and the nation. 

Two of the staff that joined us this morning have served at Debre Birhan University for more than ten years and have many memories. The way the describe and narrate certain events from their and our past is likeable. One comes after the other and we widen the circle where everyone has breakfast or coffee and chats. Those who have class went to class and those who don't went to their offices. There is the Internet too. It either steals time or helps people's teaching learning and research efforts. This vicious circle of life at the university has been like this for more than a decade. This is just life - normal life.  

There are also the research seminars and yearly workshops where people from various places and backgrounds gather. Those are really academic platforms and help intellectuals come together. 

2021 ኤፕሪል 7, ረቡዕ

Michelle Obama’s Ascent to Success

 


Mezemir G.

April 7, 2021

I was the attendant at Ras Abebe Aregay Library on March 21, 2021, a Sunday morning. I grabbed a book that I was planning to read for long. It was “Becoming,” by Michelle Obama. At the middle of my reading I was astounded to learn that Michelle read from the Internet that there are people who wrote that she is male. I went to a tailor neighbor of mine and told him about this. He responded, “I’m rather worried about the fate of my country!” “We are all worried about our country. But you know, people who claim there is 666 were talking about it” I tried to explain. He seemed uninterested and I headed back to the library pursued reading.  

I read the first part which is about the childhood of the former first lady. Michelle wrote about her family life in Chicago. The unique encounters she had with her brother Craig and their parents were impressive and ignited similar ones in me. As African Americans, they underwent many ups and downs. Fortunately, they had a strong family that cared for their needs. I was so impressed with the story that when I came to my office at the university on Monday I searched YouTube to learn about Craig’s current status. In one video, both of them were giving an interview on Good Morning America. It was really impressive to have a sibling at your book launch. Lucky Michelle!  

I reminisced about my own childhood when I read Michelle’s. It even occurred to me if I could read a biography’s childhood part without remembering mine. In my family we were two children like Michelle’s. I was with Emebet, my sister. Only because my parents divorced did my sister and I live together with our father. I was 10 when they divorced. I was the first child of my parents. The two of us were given to our father. The other two were given to my mother because they needed her care as they were little ones.

As children, cooking was one of our challenges. Firewood being scarce in our area, we had to go to the jungle and find and fetch home. When women from the neighborhood saw me carrying much wood, they would scold their children and ask them to be as good as I was. Theirs never worried, but I did. Water we fetched from a place which was a kilometer or two away. The nearby communal tap water station was built afterwards. But most often our neighbours gave us firewood and water when we didn’t have. Fanaye and Tiringo were our neighbours who always gave us. Tiringo died recently and I couldn’t make it to her funeral. Bearing all that in mind, if I have to make a contribution to my people back home it should be on energy and water.

Michelle is a strong person with seemingly strange decisions. Punching is one of these. She punched a bully girl who harassed her repeatedly. I was not such a person. I bore it anyway. What surprised me the most was her decision to quit her first job at a well-paying law firm for another one that paid half the salary. Who among us here would make that sacrifice? It was at the law firm that Michelle met Barack Hussein Obama, her husband to be. He was an apprentice from the elite law school of Harvard. He had the most coveted position of the editor of Harvard Law.

How the couple made it all the way to the presidency is astounding. Obama’s interest in politics and his absence from home for elongated times was touching. The couple faced miscarriage as well. How they fought it! Eight years at the white house as black couple is unthinkable bearing in mind that African Americans are minority in the United States. A new thing I read in the book was that the gun attack someone made on white house. Why did the USG build the palace like that? I think it should have been a shorter building and covered with trees. All the beauty, grandeur and abundance of the white house seem to fly away with the eight years of Obama’s tenure. We learn from the US system of government that there is no presidency for life. This was the exact idea Obama raised to the African leaders at the AU in Addis. But given the effort and intellectual ability of Obama and his family to get back to normal life from that height they had climbed seems distressing. If they were billionaires for example, they could have the luxury for life. This is my thought as an Ethiopian. At least this is how it is here.  

I read one of Obama’s books before. “Becoming” has inspired me to read the others as well. If I muster the energy and stamina, I don’t have to worry about the books since I have copies. 

 

 

2021 ማርች 12, ዓርብ

Let me introduce you to the librarians at Ras Abebe Aregay Library, Debre Birhan

 

The librarians at Ras Abebe Aregay Library, Debre Birhan: 

Genet Alemu 

Chief Librarian for three years. She worked for six days a week with passion and discipline! Genet is the one standing on the left.

Ruth Habtemariam 

Ruth was the lunch time librarian. I came to know her when she borrowed books. She accepted the job and did it successfully. Ruth is the one on the right.

I am Mezemir Girma, the library's founder. I am the one standing in the middle wearing a white shirt.


Eyerus Sahle 

Eyerus is the current Librarian. She started working when the COVID-19 pandemic started.




Amakelew Alemshet 

Amakelew was the librarian at our branch library. He was also the leader of a theatre club at Kebele 02. Amakelew is the one standing and smiling in this photo.



Bekele 

Bekele was the volunteer librarian at our branch library. He is seen in this phot wearing the library's shirt, Hailemariam Mamo School's uniform and donating blood.



Tesfamicael Hailu 

Tesfa was a hardworking librarian who started by distributing storybooks to schools with this bike. He also projected storybooks to children. He still comes for the Thursday night discussion sessions.



Fikremariam Gebre Yonannis 

Fikre was the librarian after Genet. He has many memories here including getting his bike stolen and forgetting a candle he lit in the small room. He was about to set the library ablaze.





Emebet 

Emebet was the evening librarian who worked from 6:00 PM to 8:00 PM. She worked at the library while studying English at the university. She is now a teacher.



Kefelegn 
Kefelegn was working at weekends. He worked while studying at the Polytechnic College. He has completed Level 4 and passed the COC.


2021 ማርች 3, ረቡዕ

የራስ አበበ አረጋይ ማስታወሻ ስያሜ ሽሚያዎችን አስመልክቶ የቤተመጻሕፍታችን አቋም

 

የራስ አበበ አረጋይ ማስታወሻ ስያሜ ሽሚያዎችን አስመልክቶ የቤተመጻሕፍታችን አቋም

 

በሁለተኛው የኢጣሊያና ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት ከነበሩ ፈርጦች ግንባር ቀደሙ ራስ አበበ አረጋይ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ በአስር ሺዎች የሚቆጠር ጦር በስኬት በመምራት በዱር በገደል ለአምስት ዓመታት ታሪክ ሲያስታውሰው የሚኖር ፍልሚያ አድርገው የሃገራቸውን ነጻነት አረጋግጠዋል፡፡  በዚያ አስቸጋሪ ወቅት የኢትዮጵያን ባንዲራ ካውለበለቡ ጥቂቶች የጦር መሪዎች አንዱ ናቸው፡፡ የኢጣሊያ ፋሽስት መሪዎች የኢትዮጵያን ህዝብ በብሔርና በቋንቋ ከፋፍለው ለመግዛት ይጥሩ በነበረበት በዚያ ወቅት ራስ አበበ አረጋይ በአንጻሩ በሸዋ የአማራና የኦሮሞ ህዝብን አስተባብረው የተራዘመውን ጦርነት በመምራት ለድል የበቁ ናቸው፡፡

ራስ አበበ አረጋይ በ1953ቱ መፈንቅለ መንግሥት በአረንጓዴው ሳሎን ግድያ ሕይወታቸውን ያጡት ኢትዮጵያን ከሚወዱትና ለምዕራባውያን ከማይመቹት መሪዎች አንዱ በመሆናቸው ነበር፡፡ በ1950ዎቹ ታቅዶ የነበረው ጭሰኝነትን ከኢትዮጵያ የሚነቅል የተባለለት ሰፊ ፕሮጀክትም ሰይፈጸም ቀርቷል፡፡ ከዚያ ወዲህም ሃገሪቱ ወደባሱ ዘርፈብዙ አዘቅቶች በመግባት እድገቷ ቁልቁል እየወረደ መሆኑ ይታወቃል፡፡       

ታሪክን ለማስታወስ እነሆ ዘመኑ ደርሶ ራስ አበበ አረጋይም ሆነ ሌሎች የሃገር ባለውለታዎች በትውልድ እየታወሱ ይገኛሉ፡፡ እኔ በግሌ በታሪክ ትምህርት ስለጀግናው ራስ አበበ አረጋይ ተምሬ አልፌያለሁ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋዎች ጥናት ተቋም በመጀመሪያ ዲግሪ ስመረቅ የመመረቂያ ጽሑፌንም በአርበኞች ተጋድሎ ላይ በተጻፈ ታሪካዊ ልቦለድ ላይ ስሰራ ከዚሁ ፍላጎቴ ይመነጫል፡፡ ከምረቃ በኋላም ታሪካዊ ጉዞዎችን በማድረግ በማስተባበርና የጉዞ ማስታወሻዎችን ጽፌ በማስነበብ አርበኞቻችንና ታሪካችን እንዲታወሱ ጥሬያለሁ፡፡ በ2008 ዓ.ም. ከተርጓሚ፣ ደራሲና የትያትር ሰው አሊሹ ሙሜ ጋር ከአዲስ አበባ ወደ ደብረብርሃን ስንመጣ አካባባውንና ታሪኩን እያነሳን መንገድ መንገዱን ስናወራ አንድ ሃሳብ ተነሳ፡፡ ይኸውም አሊሹ ከዚህ ሁሉ ነገር የሚቆጨው ራስ አበበ አረጋይ ለዚህች ሃገር ይህን ሁሉ ውለታ ውለው አለመታወሳቸው መሆኑን ነገረኝ፡፡ በነገራችን ላይ አሊሹ የሃገራችንና የጥቁር ሕዝብ ትግል የሚስበው በማልከም ኤክስንና የማርከስ ጋርቪን ስራዎች የተረጎመ የጥበብ ሰው ነው፡፡ እኔም በጉዳዩ በመስማማት ደብረ ብርሃንም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱን በእርሳቸው ለመሰየም ተፈልጎ መንግሥት ስለተቀቃወመ መቅረቱን ነገርኩት፡፡ የሆነው ሆኖ ቀድሞ በነበረኝ ፍላጎትና ቁጭት በ2008 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ከተማ የግል ቤተመጻሕፍት ስከፍት ስያሜውን በራስ አበበ አረጋይ ለማድረግ ወሰንኩ፡፡ ይህም ቤተመጻሕፍት ህብረተሰቡን በነጻ እያስነበበ አምስተኛ ዓመቱን አስቆጥሯል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት (ወመዘክር) በደብረ ብርሃን ከተማ ባደረገው የንባብ ሳምንት ወቅት እውቅና ሰጥቶናል፡፡ የግል ቤተመጻሕፍት በፖሊሲ በማይደገፍበተ ሃገር በንባብ ላይ የሚሰራው ቤተመጻሕፍታችን በአፍሪካ ቤተመጻሕፍት ማህበር ንቁ ተሳታፊና በዋና ዋና መርሐግብሮች ኢትዮጵያን የወከለ ነው፡፡ የአሜሪካ ቤተመጻሕፍት ማህበርም በመጽሔቱ ስለቤተመጻሕፍታችን ጸፏል፡፡ ይህ እውቅናና አብሮ የመስራት ፍላጎት ከደቡብ አፍሪካው የርቀት ትምህርት ተቋምና ከሕንዱ ስቶሪ ዊቨርም መጥቶ አብረን እንሰራለን፡፡ በንባብ ላይ ባሳረፍነው አሻራም ምክንያት የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን (ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ዩቱብ ቻነሎችና ጋዜጦች) በቤተመጻሕፍታችን ላይ ዝግጅቶችን በማቅረብ የንባብ ባህልና የቤተመጻሕፍት አገልግሎት እንዲስፋፋ ሰርተዋል፡፡ የቤተመጻሕፍቱ አገልግሎትና ስራ ሰፊ ቢሆንም በዚህ ልቋጨው፡፡

ከተወሰኑ ሳምንታት በፊት በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አዲስ በተሰራው የሕክምና ካምፓስ ውስጥ የሚገኘውን ቤተመጻሕፍት በራስ አበበ አረጋይ ስም ለመሰየም መወሰኑን ይህ ውሳኔ በተላለፈበት ወቅት የነበሩ ግለሰቦች ነገሩኝ፡፡ ይህም ውሳኔ ራስ አበበ አረጋይን ለማስታወስ በማሰብ የተደረገ በመሆኑ አድናቆት ሊቸረው ይገባል፡፡ በፊት አስታዋሽ አጥተው የነበሩትን የሃገር ባለውለታ ዩኒቨርሲቲው ማስታወሱ የሚደነቅ ቢሆንም የራሱ አሉታዊ ጎኖች አሉት፡፡ይኸውም በከተማው ውስጥ በጀግናው የተሰየመ ቤተመጻሕፍት እያለ ሌላ ተጨማሪ መሰየሙ ግርታን የሚፈጥርና አንባቢያንንና ህብረተሰቡን የሚያሳስት ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ቤተመጻሕፍታችንም ምንም እንኳን በአነስተኛ ቦታ የተወሰነ ቢሆንም የራሱን አሻራ እያስቀመጠና በግል ቤተመጻሕፍት ዘርፍ ያለውን ክፍተት በማሳየት በትንሽ ገንዘብ፣ የሰው ሃይልና በውሱን አቅም ትልቅ ስራ መሰራት እንደሚችል እየሳየ ያለ ነው፡፡ መጻሕፍትን በማሳተምና በማከፋፈልም በመላ ሃገሪቱ የንባብና የዕውቀት ትሩፋት እንዲደርስ እየጣረ ያለ ነው፡፡ በመሆኑም ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ይህንን ውሳኔውን እንዲያጤነው ለማሳሰብ እወዳለሁ፡፡ ከተቻለም ቤተመጻሕፍቱ በሌሎች ታዋቂ ደራሲያን፣ ምሁራንና የአገር ባለውለታዎች (ደራሲ ዳኛቸው ወርቁ፣ እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ወዘተረፈ) እንዲሰየም ሊደረግ ይችላል፡፡ ራስ አበበ አረጋይ በብዙ መልኩ እንዲታወሱ ማደረግ ይቻላል፡፡ ግርታን በማይፈጥር መልኩም እስካሁን የታወሱበትንና የተወሰኑ ፍላጎቶችን እናሳይ፡፡ ከላይ እንደተገለጸው በደብረ ብርሃን በግል ቤተመጻሕፍት አስታውሰናቸዋል፡፡ አዲስ አበባ ላይ በስማቸው መንገድና ትምህርት ቤት አለ፡፡ እነዋሪ ላይ ሆቴል ተሰይሟል፡፡ የባንክ ቅርንጫፍም አለ፡፡ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመሰየም ፍላጎት እንዳለም ሰምቻለሁ፡፡ ወደፊት ዩኒቨርሲቲያችን ባለው ተጽዕኖና የሥራ ግንኙነት መሠረት  በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣ በሌሎች ክልሎችም ሆነ በፌደራል ደረጃ ለራስ አበበ አረጋይ ውለታ የሚመጥን ወታደራዊ አካዳሚ ቢሰየም ከእርሳቸው ትክክለኛ ወታደራዊ ጀብዱ ጋር የሚስተካከል ማስታወሻ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ሌሎችም ጀግናውን የሚያስታውሱ ስራዎች ቢሰሩ ለውለታቸው ሲያንስ አንጂ አይበዘባቸውም፡፡

 

መዘምር ግርማ

የራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት ሥራ አስኪያጅ

ሰኞ የካቲት 22፣ 2013 ዓ.ም.

ደብረብርሃን 



 

 

2021 ፌብሩዋሪ 28, እሑድ

የመጽሐፍ ዳሰሳ

 የመጽሐፍ ዳሰሳ

(በዚህ ገጽ የተከፈለበት)



የመጽሐፉ ርዕስ - Marcus GARVEY፣ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አፍሪካ

 ደራሲ - ማርከስ ጋርቪ

 የመጽሐፉ ተርጓሚ - አሊሹ ሙሜ

 ዘውግ - ግጥሞች 

 የገጽ ብዛት - 142

ዋጋ - 69

የታተመበት ጊዜ - 2007 ዓ.ም.

ዳሰሳ ጸሃፊ - ሃይማኖት ክንፈ

የተከበራችሁ ውድ የመጽሐፍ አፍቃሪያን እንደምን ሰንብታችኋል?ሰላም እና ጤና እንዲሁም  ፍቅር ከሁላችሁ ጋር እንዲሆን እየተመኘሁ! ወደ መጸሐፍ ዳሰሳዉ ስገባ:-

ማርከስ ጋርቪ ይባላል የመጽሐፉ ደራሲ ሲሆን በትውልድ የጃማይካዊ ነው። ጋርቪ የጥቁር ዘር መሪ፣ጋዜጠኛ፣ተነግሮ አሳማኝ እንዲሁም ርእዮተ አለማዊ ሰው ነበር። ከዚህም በተጨማሪ ማርከስ ጋርቪ ገጣሚ ሲሆን የደቡብ እና የመካከለኛውን አሜሪካ ግዛቶች ተንቀሳቅሶ ከጎበኘ በኹዋላ በ1912 ወደ እንግሊዝ ሀገር ተጓዘ።በእንግሊዝ ሎንደን ከተማ ሳለ ለአፍሪካ ታሪክ እና ባህል ልዩ ትኩረትን ሰጥቶ የግል ጥናቱን አከናወነ።

 አንደበተ ርቱእ የሆነው ማርከስ ጋርቪ በአሜሪካ የሚኖሩ ጥቁሮችን "በዝርያችሁ ኩሩ፤"ብሎም "ወደ አያት ቅድመ አያቶቻችሁ ምድር ወደ ቅድስት አፍሪካ ተመልከቱ!"እያለ መስበኩን ቀጠለ።

በፓን አፍሪካኒዝም እንዲሁም በፈረንሳይ ሀገር የአፍሪካውያን "ኔግሪቱድ"ንቅናቄና የለንደኑ የምእራብ አፍሪካ ተማሪዎች ህብረት እና ሌሎችም የጥቁር ነፃነት ትግሎች በተነሱ ቁጥር ከነ ኤድዋርድ ዊልመንት፣ክዋሜ ንክሩማ፣ጁሙ ኬንያታ፣ማልኮም ኤክስ እና ሌሎችም ስሞች ጋር ማርከስ ጋርቪ መወሳቱ አይቀሬ ነው።

 ማርከስ ጋርቪ ገና የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ አገዛዝ ቀንበር ባልተላቀቁበት ጊዜ እንኳን "ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አፍሪካ "የሚለውን መሪ ህልም ከአእምሮው አመንጭቶ ታግሎ ያታገለ ጀግና ነው። ጋርቪ የአፍሪካ ዝርያዎችን ወደ አፍሪካ እንዲመለሱ ሆኖ የበለፀገች በራሷ ህዝብ የምትተዳደር ጠንካራና ነፃ የሆነች አንዲት አዲስ አፍሪካን መፍጠር ነበር አላማው።

 በጥሞናዊ የስነግጥም ስራዎቹ ውስጥ የመጀመሪያውን የኢንፔሪያሊስቶች ሽንፈት ከዋኝ የሆኑትን የአድዋ መሪ የሆኑትን አጤ ሚኒሊክ፣ከዚህ ሽንፈት በኹላም በኦጋዴን በኩል የጣሊያን ወረራ ያርበደበዱትን ራስ ነሲቡ ዛማኔልን እና ለኢትዮጵያ የተዋጋው ቱርካዊ ውሂብ ፓሻ አንዲሁም የደቡብ ክንፍ ተዋጊ የነበሩትና ቡታጅራ የተሰውትን ራስ ደስታ ዳምጠዉ የመሳሰሉትን የነፃነት ታጋዮች በስም ለመጥቀስ የመታሰቢያ ግጥሞችን አበርክቶላቸዋል።



 በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን በዘመናዊው ባርነት እየተገዛን ላለነው አፍሪካውያን ራሳችንን እንድንመለከት ያደርገናል። እንዴት? ብትሉ ዛሬም በዲቪ ሰበብ እነሱ የናቁትን የስራ አይነት ወይም ምርጫ በማጣት ሳቢያ ዛሬም በአውሮፕላን ተሳፍሮ፣በመኪና ተሽከርክሮ፣በመርከብ፣በታንኳ፣በጀልባ፣በበቅሎ፣በግመል እንዲያም ሲል በእግሩ ኳትኖ እዚያዉ ስፍራው ድረስ በመሄድ የሁነቱ ሰለባ መሆን እጅግ የሚያሳዝን እውነታ ነው።ይህ መጸሐፍ አይናችንን ገልጠን እውነታውን እንድናይ አመላካች ሲሆን እንደ እንደ አፍሪካዊ ምን ማድረግ አለብን የሚለውን በግጥሞቹ እያነሳሳ ፣እየመከረ እና እየኮረኮመም ያስተምረናል።

 ይህን መፅሃፍ ማን ሊያነበው ይገባል? ይህ የማርከሰ ጋርቪ ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አፍሪካ መፅሐፍ በታሪክም ሆነ በምርምር ተግባር ለተሰማሩ የኢትዮጵያ ወጣቶች ለሀገራቸውና ለህዝባቸው ተቆርቋሪና ታጋይ ዜጋ እንዲሆኑ ከማገዝም ባሻገር ለአንባብያን የንባብ ፍጆ ወይም የዚያን ዘመን ከዚህኛው ጋር በማጣቀስ ምርምር ማድረግ ለሚሹ ሁሉ የጠብታንም ያህል አስተዋፅኦ ያደርጋል።


2021 ጃንዋሪ 21, ሐሙስ

የግል ቤተመጻሕፍት ለመክፈትና ለማንቀሳቀስ ስላደረኴቸው ነገሮች

 


(ፍላጎቱ ያላቸው እንዲጀምሩት በማሰብ የተጻፈ)

1.       መጻሕፍት በሽያጭ የማገኝባቸውን ቦታዎች አወቅሁ፡፡ እነዚህ ቦታዎች በአዲስ አበባ ያሉ የመጻሕፍት ማከፋፈያ መደብሮች ናቸው፡፡ መጀመሪያ ላይ ያገለገሉ መጻሕፍትንም እገዛ ነበር፡፡ በኋላ ግን ሻጩ ከየት አምጥቶ እንደሚሸጥልኝ ስለማላውቅ ትቻለሁ፡፡ ግለሰቦች ሲለግሱም እቀበላለሁ፡፡

2.       ሰፋ ያለ ቤት ተከራየሁ፡፡ ወንበር፣ ጠረጴዛ፣ መደርደሪያና መጻሕፍት አሟላሁ፡፡

3.       ሰራተኛ ቀጠርኩ፡፡ እኔም እሰራለሁ፡፡

4.       ንግድ ፈቃድ ‹‹የጽሕፈት መሳሪያና መጻሕፍት ችርቻሮ ንግድ›› በሚል ዘርፍ አወጣሁ፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ በንግድ ሕጉ ቤተመጻሕፍት የሚል ስለሌለ ይህን ዘርፍ መምረጥ ግድ ይላል፡፡ ግብር የሚተምኑ ሰዎች ሲመጡ የምሰራውን ስራ አይተው ግብር መተመን እንጂ ሌላ ይህን አትስራ የሚሉት ነገር የለም፡፡

5.       ስለቤተመጻሕፍት አሰራር ለማንበብ ሞከርኩ፡፡ በአማርኛ በዚህ ዘርፍ የተጻፈ ነገር ያለው ኮድ ኢትዮጵያ ያዘጋጀው ያልታተመ ሞጁል ነው፡፡

6.       ለቤተመጻሕፍቱ መጀመሪያ ሥራ ማስኬጃ የተወሰኑ አስርት ሺዎች ብር ተጠቅሜያለሁ፡፡ 

7.       የተለያዩ የቤተመጻሕፍት መርሃግብሮችን ጀምሬያለሁ፡፡ ለምሳሌ የውይይትና ሥነጽሑፍ ምሽት፣ የጉዞ መርሐግብር፣ ሥልጠና ወዘተ፡፡

8.       ሥራውን ልጀምር አካባቢ የጠየኳቸው ሰዎች ቢዝነስ ፕላን እንዳለኝ ጠይቀውኝ የነበረ ቢሆንም እኔ ስለቢዝነስ ፕላን የማውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ለማዘጋጀትም አልሞከርኩም፡፡ ይህ ትልቅ ድክመቴ ነው፡፡ የሚጀምር ሰው ቢያዘጋጅ መልካም ነው፡፡

9.       ‹‹ይህን ስራ ስትሰራ ዓላማህ ምንድነው? በትክክል ጥርት ያለ ዓላማ ሊኖርህ ይገባል!›› ያለኝ ሰው ነበር፡፡ ያንንም ጥርት አድርጌ አለማወቄን እንደ ድክመት አየዋለሁ፡፡ ዓላማችንን ካላወቅን ተስፋ መቁረጥ ሊከተልና ስራውም አደጋ ላይ ሊወድቅ ስለሚችል ከመጀመራችን በፊት ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ በእርግጥ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ማድረግ እንደማልፈልግ፣ በነጻ ማስነበብን፣ በቅናሽ ዋጋ ማከራየትንና መሸጥን ያካተተ ስራ እንደምሰራ አውቀው ነበር፡፡ አሁንም በዚያ እንደገፋሁበት ነኝ፡፡ አሁን ላይ ሆኜም ሳስበው ከኪራይ ቤት ብቆይ እመርጣለሁ፡፡ ቤት የመስራትን ጣጣ አልፈልገውም፡፡ የቤት ኪራይ ከከበደ መፍትሔ መፈለግ ነው፡፡ ገንዘብ የማመነጭበትን መንገድ እፈልጋሁ፡፡

10.   መጽሐፍ ስለማከራየት መግለጽ ያለብኝ ነገር ቢኖር በመታወቂያ ማከራየት አክሳሪ መሆኑን ነው፡፡ በቤተመጻሕፍታችን ከ200 በላይ ያልተመለሱ መጻሕፍት አሉ፡፡ በመሆኑም ከሁለት ዓመት አገልግሎት በኋላ ገንዘብ በማስያዝ እንዲከራዩ አድርገናል፡፡ ይህ አሰራር በእርግጥ ገንዘብ የሌላቸው ሰዎች እንዳይከራዩ ያደርጋል፡፡ ይሁን እንጂ ከሚያስከትለው ችግር አንጻር ሁነኛ መፍትሔ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡ መከራየት የማይችል ሰው ቤተመጻሕፍቱ ባቀረበለት በነጻ የማንበብ ዕድል ይጠቀማል፡፡

11.   ‹‹ስራው አትራፊ ነው ወይ?›› ብሎ ለሚጠይቅ ሰው ‹‹አንባቢ ባለበት ከተማ ሊያተርፍ ይችላል›› የሚል መልስ እሰጣለሁ፡፡ ወይም ከአትራፊ ቢዝነስ ጋር በጥምረት ሊሰራ ይችላል፡፡ ስራው የንባብ ጉዳይ ለሚስበውና ቤተመጻሕፍት ኖሮት ለማየት ለሚፈልግ ሰው ጥሩ ጊዜ ማሳለፊያና ህብረተሰብን ማገልገያ መንገድ ነው፡፡

12.   ለተጨማሪ መረጃ ቢጠይቁኝ ለማገዝ ዝግጁ ነኝ፡፡ ምናልባት ስለ ቤተመጻሕፍቱ መረጃ ለሌላችሁ ሰዎች ራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት ይባላል፡፡ መገኛው ደብረ ብርሃን ነው፡፡ መጋቢት 2008 ዓ.ም ተመሰረተ፡፡ ንብረትነቱም የግል ሲሆን፤ በቤተመጻሕፍቱ በነጻ ማንበብ፣ በቀን 1 ብር በመክፈል መከራየትና እንዲሁም መግዛት ይቻላል፡፡

2021 ጃንዋሪ 12, ማክሰኞ

ንባብ ተኮር የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ለሁላችሁም

ከመዘምር ግርማ (mezemirgirma@gmail.com)

ዛሬ ላስተዋውቃችሁ የፈለኩት ጉዳይ ማናቸውም ሰው መጽሐፍ ሻጭ እንዲሆን ለማድረግ የሚቻልበት ዕድል መኖሩን ነው፡፡ ማንም ሰው ከቤቱ፣ ከመስሪያ ቤቱ ወይም ከተመቸው ቦታ ሁሉ ሊሰራው የሚችለው ይህ ሥራ ብዙ መነሻ ገንዘብ የማይጠይቅና የጊዜ ነጻነትም ያለው ነው፡፡ መጻሕፍትን ከደራስያን፣ ከአሳታሚዎች፣ ከሻጮችና አንብበወው ከሚሸጡ ግለሰቦች በመውሰድ ለተጠቃሚዎች ማድረስ ይቻላል፡፡ ይህን ሥራ በሚገባ ለመስራት አዳዲስና ያገለገሉ መጻሕፍት የሚገኙባቸውን ቦታዎች ማጥናት፣ ተፈላጊ መጻሕፍትን ማወቅና አንባቢ መሆን ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ የመጻሕፍትን መገኛ ካወቅንና መጻሕፍቱንም ካነበብናቸው ዳሰሳ መጻፍ፣ ተናግረን ማሳመንና መሸጥ እንችላለን፡፡  ይህ ብቻ ሳይሆን በደንብ ባለመተዋወቃቸው ምክንያት ያልተሸጡ መጻሕፍትን አንብቦ ጥሩ ይዘታቸውን ለማስተዋወቅ ለአንባቢ ማድረስ ይቻላል፡፡  የዚህኛው ዓይነት ሥራ ጠቀሜታው ብዙ ቁጥር ያለውን መጽሐፍ በአንድ ጊዜ ለማግኘትና ከፍተኛ ትርፍ ለማግኘት መቻሉ ነው፡፡ ለምሳሌ ዘአልኬሚስት የተባለው የፓውሎ ኮሊዮ መጽሐፍ በስድስት ወራት ሁለት ኮፒዎች ብቻ ተሸጦ ከብዙ ጊዜያት በኋላ በአንድ አጋጣሚ በሚሊዮኖች ቅጂዎች የተሸጠ መሆኑን ማስታወስ ግድ ይላል፡፡

መጻሕፍትን ለማን እሸጣለሁ የሚለው አንድ አሳሳቢ ጉዳይ ሊሆንብዎት ይችላል፡፡ ይህን እርስዎ እንደ አንድ የቤት ስራ ወስደው እነማን ማንበብ ይችላሉ ብለው እንዲያስቡ ያስፈልጋል፡፡ ማንበብ የሚችሉ ሰዎችን ወደ አእምሮዎ ማምጣት ከቻሉ እንዴት ላስነብባቸው የሚለው ይከተላል፡፡ ማንበብ ጀምረው ከሆነ በዚያው እንዲቀጥሉ የፈለጉትን መጻሕፍት ያቅርቡላቸው፡፡ በየመስሪያ ቤቱና በየሰፈሩ የመጻሕፍት ዕቁብ መስርተውም ለመጻሕፍት ዕቁቡ መጽሐፍ ያቅርቡ፡፡ የማንበብ ልምድ የሌላቸው ከሆኑም ልምዱን እንዲያጎለብቱ አድርገው ወደ ንባብ ዓለም ያስገቧቸው፡፡ ሰዎች በሚፈልጉት ነገር ማንበብ ቢጀምሩ ጥሩ ነው፡፡ ከሚፈልጉት ጋር ማያያዝ ያስፈልጋል፡፡ ወደ ኃይማኖት ዝንባሌ ላላቸው ደንበኞችዎ ከአንድ የመጻሕፍት መደብር የኃይማኖት ማጻሕፍት ስብስብ ያሉ መጻሕፍትን ፎቶ አንስተው ያስመርጧቸው፡፡ የመረጡትንም ያቅርቡ፡፡ የሥራ ፈጠራ ዝንባሌ ላላቸው፣ የስነልቦና መጻሕፍት ለሚወዱ፣ የቴክኖሎጂ ለሚያዘወትሩ ወዘተ እያጠኑ ያቅርቡ፡፡ ለስራዎም ሃያ አምስት በመቶና ከዚያ በላይ ኮሚሽን ያገኛሉ፡፡ በቅርብዎ ያሉትን አንባቢያን ካካለሉ በኋላ በማህበራዊ ሚዲያ፣ በቢዝነስ ካርድ ወይም በሌላ ሁነኛ መንገድ ስለስራዎት ማስታወቂያ ይስሩ፡፡ ይህም ማስታወቂያ ወደ ክፍለሃገርና ወደ ውጪ ሃገር መጻሕፍትን መላክ ያስችልዎታል፡፡ መጻሕፍት ተቀባዮች ያምኑዎት ዘንድ ግድ ስለሚል እምነትን የሚገነቡ ነገሮችን ይመርምሩ፡፡

ሌላው ወሳኝ ነገር የእርስዎ አንባቢት በመሆኑ እርስዎ በቤትዎ የመጻሕፍት ስብስብ ይኑርዎ፡፡ ያንን ስብስብ ለማንበብም ሆነ ድንገት ሲታዘዙ ለመሸጥ ይጠቀሙበት፡፡ በሃገራችን ንባብ ገና ያልተነካና የማደግ እድሉ ሰፊ የሆነ ዘርፍ በመሆኑ ለብዙ ሺ ሰዎች የስራ ዕድል ይፈጥራል፡፡ በትንሹ አዟሪዎችንና አነስተኛ ሱቅ ያላቸውን ወገኖች ይመልከቱ፡፡ ለውጣቸው በየቀኑ የሚታይ ነው፡፡ ከማናቸውም ስራ ጋር የሚያስኬዱትና ትውልድን በማነጽ ላይ ትልቅ ሚና እንዲጫወቱ የሚያስችልዎትን ይህን ዘርፍ ቢቀላቀሉ እንኳን ደህና መጡ ብለን እጃችንን ዘርግተን እንቀበልዎታለን፡፡ ከምረቃ በኋላ ሥራ አጥ ሆነው ቀን በቀን ገንዘባቸውን በመከስከስ ላይ ያሉ ወጣቶች የማንበብ ችሎታ እያላቸው ያንን ኢንቬስትመንት ለምን እንደማይጠቀሙት አይገባኝም! እነዚህ ወጣቶች ዕድሜያቸውን ያሳለፉት በመማር ስለሆነ ያንን ትምህርት ቢያንስ የአንባቢያንን ፍላጎት የሚያረካ መጽሐፍ በመምረጥ መጠቀምና መጽሐፉን ሸጠው ኮሚሽን ማግኘት ይቻላቸዋል፡፡

የኦንላይን ገበያ ወደሃገራችን እየገባ ስለሆነ በቅርብ ጊዜ መጻሕፍትን ማናቸውም ሰው መሸጥ እንደሚችል ከሌሎች ሃገራት ልምድ ማየት ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ አሁኑኑ መጀመር ለወደፊቱ ልምድ እንዲኖርዎ ያስችላል፡፡

ጥያቄ ካላችሁ በአስተያየት መስጫው ላይ ብቻ ጻፉልኝ፡፡ ይህም የጥያቄዎችን መደጋገም ለማስቀረትና ምልልሱን ሁሉም አባል እንዲያየው ማለት ነው፡፡

መልካም ስራ!


በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...