2017 ፌብሩዋሪ 8, ረቡዕ

ኢትዮጵያዊ ሥም ላላቸው ሠዎች ብቻ የተዘጋጀ የመዝናኛ መርሃግብር በራስ አበበ አረጋይ ቤተመፃሕፍት፣ ደብረብርሃን። (Grand Party for Those of You Who Are Named in Ethiopian Languages)




በዓላማው የምትስማሙ ሁሉ ሃሳቦችን እንድትሰነዝሩ ይሁን። አገርኛ ስም ተጠልቶ ህፃናት ለመጥራት እንኳን የሚከብዱ የውጪ ስሞች እየወጡላቸው ሲሆን ትላልቆችም ስም በመቀየር ዘመቻ ላይ ይገኛሉ። እንደኔ አስተያየት ከአገራችን ስሞች ሁሉ የአማርኛ ስሞች በጣም አደጋ ላይ ናቸው። አንደኛ በአማርኛ አፍ የማይፈቱ ህዝቦች ወደየራሳቸው ቋንቋዎች እየተመለሱ ነው። (ያም አገርኛ ሥም ነው በነገራችን ላይ።) የአማርኛ ስም አዲስ ለሚወለዱ አለማውጣት ብቻ ሳይሆን ነባሮቹም ሲቀይሩ አይተናል። በጣም ወደሚቀናን ቋንቋ መመለስ ብዙም ተቃውሞ ላያስነሳ ይችላል፤ የዘር ጥላቻ እስከሌለው ድረስ። ምንም በማንናገረው ቋንቋ ሥም ማውጣት የምን ይባላል? በአጋም አይዘመዱን በቀጋ! ራሱን ጀምስ ንጉጊ ብሎ ይጠራ የነበረው ኬንያዊ ደራሲ ወደራሱ ቋንቋ ተመልሶ ንጉጊ ዋቲዮንጎ በሉኝ በማለቱ ድንቅ ስራ ሰርቷል፡፡ ይህን ዓይነቱን ነው ወደራስ መመለስ የምለው፡፡ ወላጆቻችሁ በሰየሟችሁ ምክንያት ግን ልንወቅሳችሁ እንደማንችል እዚህ ልብ እንድትሉልን ያሻል!
ስማቸውን ለመቀየር የሚገደዱት ወገኖቻችን ይህን የሚያደርጉት በከፍተኛ የስነልቦና ጫና ውስጥ ሆነው መሆኑን እገነዘባሁ፡፡ የተቃጣብንን ጥቃት መከላከል የምንችልበት ደረጃ ላይ ለመድረስ የነዚህ ወገኖቻችን መልካም ትብብርና ቀና አስተያየት ያስፈልገናል፡፡ ማንንም ለማሸማቀቅ አስቤ ወይንም ምንም ዓይነት የጥላቻ አስተሳሰብ ለማራመድ አስቤ እንዳልሆነም ይረዱልኝ፡፡ ሁላችሁንም እወዳችኋለሁ!
It would be unwise to inform you, my fellow country men and women, that we have been calling ourselves and our loved ones in imported names. Everyone knows that this time around in our country naming oneself or one’s children in local languages has been considered as a grave error. It is we who have to tackle this challenge meant to damage our honor, culture and identity. For this reason, we feel honored to call a party to celebrate our cherished names and denounce the act of systematically imposing other languages and cultures on our people. We know that this causes anger among those people who stand against us, however, we should stress our belief and identity in action.
ይህ ጽሑፍ በፌስቡክ ላይ እንደወጣ የሚከተሉትን ምላሾች አስተናግዶ ነበር
የሀገራችንን ስሞች አደጋ ላይ ከጣልዋቸው ጉዳዮች አንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ይመስለኛል፡፡ በርካታ ሰዎች ለልጆቻቸው፤ ስም ሲያወጡ የስም ምንጫቸው መጽሀፍ ቅዱስ ነው፡፡ በዚህም መሰረት፤ ይዲዲያ፤ ቢታኒያ፤ኑሃሚ፤….. የመሳሰሉ ስሞች በከፍተኛ ፍጆታ እየተጠቀምንባቸው፤ እንገኛለን፡፡ እኔ እንደሚገባኝ መጽሐፍ ቅዱስ፤ የተጻፈው፤ ለመላው ዓለም ክርስቲያኖች በእስራኤልና አካባቢዋ እግዚአብሔርና ቅዱሳን፤ያደረጉትን ተጋድሎና ሩጫ ነው፡፡ ስለዚህ በመጽሐፍ ቅዱስ የነበረው ስምም ሆነ ባህል ድርጊቱ የተፈጸመበትን ቦታ የሚገልጽ፤እንጂ ኢትዮጲያዊ ስምን የሚተካ አይመስለኝም፡፡ ኢትዮጲዊያን ከሌላው ዓለም ልዩ የሚያደርገን የራሳችን በርካታ መገለጫዎች ያሉን በመሆናችን ነው፡ከነዚህ ደግሞ አንዱ ብሔር ብሔረሰቦች የራሳቸውን ባህልና ማንነትን ተከትለው የሚሰየሙባቸው ስያሜዎች ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ በክርስትናም ከሆነ ብዙ ኢትየጲያዊ ክርስትና መሰረት ያደረጉ ስያሜዎች አሉን፡፡ ለዚህ ትልቁ ምሳሌ የበርካታ የትግራይ ክልልና የሌሎች መሰል ክልል ተወላጆች ስም ነው፡፡ ወልደገብርኤል.. /ገብርኤል፣ ለተማርያም፤ገብረእግዚአብሔር፤ተከስተ /ማርME… ታዲያ ይህንን መሰል ኢትዮጲዊ፤ኦርቶዶክሳዊ ስያሜ እያለንን፤ ለምንድነው፤ ፒተር፤ጆን፤ቢዮንሴ፤ማይክል ወዘተ እያል ስማች መጤ የምናደርገው፡፡
ከአማርኛ ስሞች በተጨማሪ የሌሎች ብሔረሰቦች ስያሜዎችም አደጋ፤ላይ ያሉ ይመስለኛል፡፡ ምናልባት አንዳንድ ማስተካከል ሊገቡን የሚችሉ ስያሜዎች ካሉ ማስተካል እንጅ ፈጽሞ መለወጥ ግን የሚገባኝ አይመስለኝም፡፡ ምሳሌ፤ጸጥ አድርጋቸው፤ የመሳሰሉ የመንዝኛ ስሞችን አንድ አድርጋቸው እያልን
የጎጃም አማሮች ሰም አወጣጥ የራሱ ስርዓት አለው፡፡ የልጁ ስም ከአባቱ ጋር እንዲገጥም ወይንም ዘመኑን እንዲገልጽ ተብሎ ይወጣል፡፡ ምሳሌ ፍቅር ይልቃል፡ ፍቅር ይበልጣል፤ አንዱ አምላክ ይበልጣል፡፡ ሸዋም ሲሰይም ወግደረስ፤ አልፎ አውግቸው፡ ወንደሰን፤ ዋሲሁን፤ብዙአየሁ፤ እንቁ እንዲል
ጥሩ ብለሀል ወንድሜ ወግደረስ ሀሳብህን እጋራለሁ ግን በመጽሀፍ ቅዱስ ላይ ያሉ ስሞች ድርጊቱ የተፈፀመበት ቦታ የሚገልፅ ቢሆንም ስማቸው የየራሳቸው ትርጓሜ አላቸው ስለዚህ ብንጠቀምባቸው ጥሩ ነው ባይ ነኝ።
በዚህ ዝግጅት ላይ እንድትሳተፉ የተጋበዛችሁ ሰዎች ደስታ ከተሰማችሁ ከማንም በላይ ማመስገን ካለባችሁ ስማችሁን ያወጡላችሁን ነው፡፡ ክብርና ሞገስ በቋንቋቸው ኮርተው ልጆቻቸውን ለሰየሙ ወላጆችና አሳዳጊዎች!
የምወድህም ለዚህ ነው። People should develop the habit of thinking "in side the box". እንዴት አንጀት የሚያርሱ ባህልን ስብዕናን፣ ኩነትን፣ ታሪክንና የማህበረሰብ ፍላጎትን የሚገልፁ ሀገርኛ ስሞች አሉ መሰለህ መዚ። እንዳልከው የሀገራችን ህዝቦች ለስያሜ ከኢትዮጵያዊነት ይልቅ ጀዊሽነትን እያስቀደሙ ያሁነያ። ያሳዝናል። ውይይቱ በዩኒቨርስቲ ደረጃ ቢካሄድ ደስ ይለኛል። በባህል ማዕከል በኩል፤ በሴሚናር መልኩ።
Go forward, i am always with you!
Most of the youngest play the role change their amharic name in to other context interms of civilization.
እኔ እንደሚመስለኝ በውጭዎች ቋንቋ ( ስም) መጠራት እንደስልጣኔ የመቁጠር የተሳሳተ ግንዛቤ ውጤት ነው::

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...