2023 ዲሴምበር 22, ዓርብ

ስለ ኢየሱስ እንደኔ የተሰቃየ የለም!

 ስለ ኢየሱስ እንደኔ የተሰቃየ የለም!

እውነተኛ ታሪክ

ምግብ ላዘጋጅ ስራ ስጀምር ትመጣለች። በርጩማዋን ይዛ ትቀመጥና ነገር ትጀምረኛለች። "ኢየሱስ ያድናል!" ትለኛለች። ዝም እላለሁ። ከምግብ ዝግጅት በፊት ሳነብ የነበርኩትን ለማሰላሰል ዕድሉን ትነሳኛለች። የማበስለው በቡታ ጋዝ ስለሆነ ወደ ቡታ ጋዙ አያለሁ። ለመኮረኒ መቀቀያ ወደማፈላው ዉኃም አያለሁ። ከሰዓት ስለማቀርበው አሳይመንት እንዳላስብ ትከለክለኛለች። ሽንኩርት መክተፍ ስጀምርም አትተወኝም። "ሃሌ ሉያ" ትለኛለች። ጆሮዬ ስር መጥታ ትጮህብኛለች። ስመገብም አታቆምም። በልጅነቴ ስናደድ ክፉ ልጅ እንደነበርኩ ትዝ ይለኛል። ድንገት ይሰውረኛል። እነሱ ዲፓርትመንት መምህራን ውጤት የሚሰጡት በብሔር ነው ይባላል። አያጠኑም። እኔን ግን አጥንቼ መመረቅ ከለከለችኝ። ስለሷ ጩኸት ሳስብ ውዬ አድራለሁ። "ኢየሱስ አዳነ አላዳነ እኔ ምን ቤት ነኝ!" ብዬ ስመልስላት አትሻሻልም። ይብስባታል። መናኸሪያ ያሉ ሰዎች የሚሳደቧቸውን ዓይነት ፀያፍ ስድቦች መሳደብ ጀመርኩ። በጨዋ ደንብ ያደግሁትን የገጠር ልጅ ባለጌ አደረገችኝ። ሊመልሳት አልቻለም። 

አንዳንዴ ቤተመጻሕፍት አድራለሁ። ለሰዎች ስለአድራጎቷ ስናገር እሷ እንደማትጮህና ድምጿ እንደማይሰማ ይነግሩኛል። በምን ምክንያት አብረን ለመኖር እንደወሰንን በአግራሞት ይጠይቁኛል። ኖኪያ ስልኬ ድምፅ ስለማይቀርጽ አንድ ቀን ስትጮህብኝ ለጓደኞቻችን ደውዬ አሰማኋቸው። ተገረሙ። ቆማ "ውስጥሽ ሰይጣን አለ" ትለኛለች። "ኢየሱስ ጌታ ነው!" ትለኛለች። አንድ ዓመት ተኩል ታገስኳት። በየቀኑ 12:00 ከኦሮምኛ ዜና ጀምራ በየቋንቋው የሚደጋገመውን ፕሮግራም ስታይ ታመሽና ምሽት 4:30 ኢቲቪ የሱማሌኛ ዜና ሲጀምር ትተኛለች። ሰራተኛ ስለቀጠረች ምግብ እንኳን አትሰራም። በደሞዝ ትበልጠኛለች። ቀድማኝ ስትተኛ ክፉ ነገር ታሳስበኛለች። ተስፋ ስትቆርጥና ሳኮርፋት እኔ ክፍል ጠረጴዛ ላይ ቤቱን ለቅቄ እንድወጣ የሚያዝ መልዕክት ተወችልኝ። "እህቴ" በሚል የሚጀምረውን መልዕክት ሳይ ቃሉን የተጠቀመችው ጠላቴ ጠላቴ ለማለት ነው ብዬ ተረዳሁት። ቀጥሎ ምን ወሰንኩ? መቼም ያለፈ ታሪክ ስለሆነ ችግር የለውም። እስኪ ገምቱ። 

"ኢየሱስ ጌታ ነው"፣ "ኢየሱስ ያድናል" ወዘተ የሚል ጥቅስ ስሰማ ያን ክፉ ጊዜ በንዴት አስታውሳለሁ። 

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...