2017 ኖቬምበር 7, ማክሰኞ

ማስታወቂያ




ደብረብርሃን የንባብ ከተማ!
ቀድመው ሊመዘገቡበት የሚገባ ትምህርታዊና ጥበባዊ ዝግጅት በራስ አበበ አረጋይ ቤተ-መጻሕፍት፣
የዚህ ሣምንት የዕለተ-ሐሙስ (30/2/10፣ 12፡00 – 2፡00) ዝግጅታችን ሃያ አምስት ሰዎችን ብቻ ስለሚያስተናግድ፤
በርካታ ሰዎች የመሳተፍ ፍላጎት ሊኖራቸው እንደሚችል በመገመቱ፤
በምንነጋገርበት ርዕሰ-ጉዳይ ላይ ወደፊት ሰርተው ከየተሻለ ጥቅም ሊያመጡ የሚችሉትን ሰዎች ለማሰባሰብ በማሰብ፤
ቀድማችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡ የምዝገባው ሁኔታ፣
በቤተመጻሕፍቱ በስራ ሰዓት በመገኘት፣
በስልካችን (0970381070) የጽሑፍ መልዕክት በመላክ ወይንም በመደወል፣
በፌስቡካችን መልዕክት በመላክ ይሆናል፡፡
የዕለቱ ትምህርት ርዕሶች፡- 1. ‹‹ልሳነ - ግዕዝ››
                  2. ‹‹የማናውቀው፣ ጨለማው፣ 96 በመቶውን የሚሸፍነው የበይነ-መረብ ክፍል ምን ይዟል?›› የሚሉት ናቸው፡፡
በዕለቱ የተለመደው የስነጽሑፍ ስራ እንደሚኖር ግልጽ ነው፡፡ ከሰሞኑ ያነበብነውን የምናጋራበት ዝግጅትም እንዲሁ፡፡ የጥበብ ስራ ቀድመው ለሚያስገቡ እና/ወይም ከሰሞኑ ያነበቡትን መጽሐፍ በአጭሩ ለሚገልጹ ተሳታፊዎች ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡ ተሳታፊ የሚበዛ ከሆነም ሌሎች የማጣሪያ ዘዴዎችን የምጠቀም ይሆናል፡፡
ጥቂት ስለ አቅራቢው፡-
አቅራቢው ቤተመጻሕፍቱ በተቋቋመ ወቅት ጎብኛችን የነበሩ፣ አሁን ቀረት ቀረት ያበዙ ናቸው፡፡ ዛሬ ምሳ ሰዓት ተገናኝተን ለኔ የሚያስረዱኝ ነገር አብዛኛው ከአቅሜ በላይ ስለሆነና ለቤተመጻሕፍቱ አባላት ቢያስረዱልን ይጠቅማል ስላልኩ ጋበዝኳቸው፤ ያለ ምንም ማቅማማት ተቀበሉኝ፡፡
የዚያው ሰው ይበለን፡፡

2017 ኦክቶበር 25, ረቡዕ

ብድር ማስመለስ ተሳነን፤ ወይ ማስያዣ አልያዝን!





‹‹አበዳሪው ምን ያርግ ብሩ እንዲወልድለት
ተበዳሪው ምን ያርግ ልጆቹ እንዲያድጉለት
እኔስ የገረመኝ የዋሱ ሞኝነት››
ለአሁኑ ችግራችን የሚሆን የህዝብ ግጥም ስላጣን ይህን ተያያዥ ግጥም በመጋበዝ ጀመርን፡፡
1. በክፍል ጓደኛ መጭበርበር
2003 በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኤፍ ካምፓስ የሚማርና በአንድ የምስራቅ ኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ የሚያስተምር ቆንጆ ልጅ ነበር፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በድባብ መናፈሻ ሁሉም ጓደኞቹ ፀሐይ እየሞቁ ክፍለጊዜ እስኪደርስ ያሙታል፡፡ ከነዚህ ጓደኞቹ አንዱ ጓደኛዬ ስለነበር አጠገባቸው ሆኜ አዳምጣለሁ፡፡ አንዱ ልጅ ይህ ጓደኛቸው ስልክ አስደውለኝ እንዳለውና እንዳስደወለው፤ ካስደወለው በኋላ ሲያይ ግን ጓደኛቸው በስልኩ ውስጥ ገንዘብ እንደነበረው ይረዳል፡፡ ቁጭቱን በሆዱ ያዝ አድርጎ ዝም! ሁሉም የተነጠቁትን ገንዘብ እየተናገሩ ተደመረ፡፡ ብ ….. ዙ ብር ሆነ፡፡ ልክ የአገራችን ብሔራዊ ዕዳ በአሁኑ ሠዓት እንደበዛው ካቅሙ በላይ ሆነ፡፡ ይህ ልጅ ለመበደሩ ምክንያቱ ምን ይሆን? አመል ሳይሆን አይቀርም፡፡ ትምህርታቸው ስለገንዘብ ነገሮች በመሆኑ አንድ ቀን መምህራቸው ስለብድር አመላለስ ሲያስተምሩ እያቃለዱ ጠየቁ አሉ፡፡ እንዲህ በማለት "ከዚህ ክፍል ተበድሮ የማይመልስ አለ?" በማለት፡፡ ተማሪው ሁሉ ወደዚያ ዞረ አሉ፡፡ "ያልመለሳችሁ ቶሎ መልሱ ብድራችሁን" ብለው ትምህርቱን ቀጠሉ መምህሩ፡፡ ተማሪው በሳቅ!
2. በሰፈር ሰዎች መታለል
ዛሬ ከዚህ ያልተናነሰ ዚቅ ደብረብርሃን ተከሰተ - በሰባት ዓመቱ፡፡ ጓደኛሞች ተሰብስበን አንዱ ደወለልኝ፡፡ "ይህን ስልክ አላነሳም፤ 1000 ብር ነጥቆኛል" ብዬ ተናገርኩ፡፡ ከዚያም በቅደም ተከተል ገንዘብ የቀሙኝን በምሬት ዘረዘርኩ፡፡ ‹‹ጥሬ ገንዘብ ቆጥሬ ሰጥቼ!›› ተጀመረ ምክንያታዊ ቡጨቃ! "እኔንም ይሄን ያህል አስቀርቶብኛል! ከኔም ስንትና ስንት ብር ነጥቃኛለች! ደሞ ክህደቷ፡፡ እኔማ በኔ ሞኝነት እንዳልወሰደችው ነግሬያታለሁ፡፡ ሰጥቼሻለሁ የምትለው ደሞ!" መባባል ተጀመረ፡፡ የተበደሩባቸው የውሸት ግን ለጊዜው አሣማኝና አሣዛኝ ምክንያቶች ተነሱ፡፡ የጋራ ንግድ እንጀምር በማለት፣ የእቁብ ገንዘብ ሳይከፍሉ ከፍያለሁ በማለት፣ እቃ ወስዶ ባለመክፈል፣ የማትፈልገው ብር ካለህ ነገ እመልስላሃለሁ በማለት …. ፈልጌህ ነበር ብሎ ረፍት ነስቶ አገር የተሸበረ አስመስሎና ስትመጣ ጉዳዩን እነግርሃለሁ ብሎ ከስራ ቦታ ድረስ አሯሩጦ በማስመጣት፣ በቁልምጫ በመጥራትና የገሬ ልጅ እያሉ በማባበል፣ በርካታ ፈጠራ የተሞላባቸው ምክንያቶችን በመደርደር፡፡ ምን ነበር ጓደኝነትን ለሚያጠናክርና ለመልካም ነገር ፈጠራ ቢፈልጉ?
ለማስመለስ የተደረጉ ጥረቶች ተወሱ፡፡ በሞባይል ሜሴጅ ምላሽ የሚሰጡ አሉ፡፡ ‹‹አንቺ ጥሩ ልጅ አልነበርሽም ወይ? ለዚች ብር ምን እንደዚህ ያደርግሻል! ካገር አልጠፋ! አክስታችን ሞታ አገር ቤት ሄጄ ነው፡፡ (ሦስት ደርዘን አክስት ያላ ይመስል በየቀኑ አንድ ትገድላለች!)›› የትዳር አጋሮቻቸው አማላጅነት እንኳን አለመስራቱ ተወሣ፡፡ ባልና ሚስት ካንድ ‹አጭበርባሪ› ባህር ይቀዳሉ እንዲሉ፡፡ ያላበደሩት ሰዎች ምን አለባቸው! ዛሬም መልካም ጓደኝነታቸውን አስቀጥለዋል፡፡ ወጥመዱን እንዴት እንዳለፉት ያወሳሉ! ያበደርን ግን ወይ ምስጋና የለ፣ ምን የለ! ተበድረው ቤታቸውን ያደራጁ እንዳሉ ሁሉ በብሩ የተዝናኑበትም አይጠፉም፡፡ ነገ ብዙ ጓደኞቻችን ሲመጡና የአውጫጭኙን መጀመር ሲረዱ የየራሶቻቸውን ታሪኮች በቁጭት ያወጋሉ፡፡ ለማሸማቀቅ ብፈልግ እነዚህን ተበዳሪዎች ታግ አደርጋቸው ነበር፡፡ ገጠመኝ ካላችሁ ተጨማሪ የማጭበርበሪያ መንገዶቻቸውን ንገሩን፡፡ እስከዚያው የናንተን ገጠመኝ ፃፉልኝ፡፡ ወስደው ያስቀሩባችሁንም ኮሜንት ላይ ስማቸውን ጽፋችሁ መልሱልኝ በሉ፡፡
3. አጥማጅ የስራ ባልደረቦች
እስከ 2005 ድረስ ለበርካታ የስራ ባልደረቦቼ አበዳሪ ነበርኩ፡፡ ደሞዝ እስኪመጣ ድረስ ማን ጋ ስንት ብር እንዳለኝ ሳስብ እከርማለሁ፡፡ እንትና ጋ 65፣ እንትና ጋ 1200፣ እንትና ጋ 2000፣ እንትና ጋ 34 ወዘተ፡፡ ወይ አልጽፈው! ወይ ባንክ አይደለሁ! ወይ ባይመልሱ ማስያዣ አልያዝኩ! ደሞዝ ሲመጣ የሚመልሱ አሉ፡፡ የማይመልሱም አሉ፡፡ ስድስት ወር አቆይተው የሚያመጡም አሉ፡፡ ባገኙኝ ቁጥር ‹‹ብርህን ሳልመልስ፤ ቆይ ደሞዝ ሲመጣ›› የሚሉኝ አሉ፡፡ ከተበዳሪው በላይ ስሳቀቅ ቆየሁ፡፡ ዓይናቸውን አየት ሳደርግ ብሬን አምጣ የሚል አስተያየት እንዳይመስልብኝ ስሰጋ እቆያለሁ፡፡ ‹‹ከባለፈዋ ጋር የሚመለስ 200 ብር ጨምልኝ›› እባላለሁ፡፡ ከባንክ አውጥቼ ሰጥቼ ሲመልሱልኝ ባንክ አላስገባውም፡፡ አባክነዋለሁ፡፡ ቢመልሱም የቆብኩትን አስጠፉኝ ማለት ነው፡፡ ቆይቶ ተበዳሪዎቼን ማራቅ ጀመርኩ፡፡ አንዱ ገንዘብ ቸገረው፡፡ መሄጃ አጣ፡፡ በየወሩ የማበድረው እኔ ነበርኩ፡፡ አትምጣብኝ ብዬዋለሁ፡፡ ከነጓደኛው ‹‹ክፉ ሰው›› የሚል ስም አውጥተውልኛል፡፡ ታዲያ ክፉ ሰውን እንዴት አበድረኝ ይበል፡፡ ምላሼንም ይገምታል፡፡ ሌላ ጓደኛውን ጠይቆት ኖሯል፡፡ ያ ጓዳኛው ደግሞ ምንም ሱስ የሌለበትና ተበድሮኝ የማያውቅ ነው፡፡ ‹‹ኤቲኤም አልሰራ አለኝ፤ ነገ ሰኞ የምሰጥህ 300 ብር ስጠኝ›› ሲል ጠየቀኝ፡፡ ሰጠሁት፡፡ ወዲያውኑ አብሮን ለነበረው ለዚያ ጓደኛችን ሰጠው፡፡ እሱም ‹‹እኔ ከሱ አልፈልግም፤ ይቅርብኝ›› አለ፡፡ በልምምጥ ተቀበለው፡፡ ገንዘብ ቆጥብ ስለው የማይሰማኝ ሰው ለምን ገንዘብ ይጠይቀኛል ብዬ ስለማምን ነበር በሱ ላይ ያን ውሳኔ የወሰንኩት፡፡ ወስዶም ለሱስ ነው፡፡ ተበድሮኝ አያውቅም፡፡ ጓደኛ ራሱን እንዳያሻሽል መንስኤ መሆንም ይመስለኛል ማበደር፡፡ አሁን የስራ ባልደረቦቼን የአበድረኝ ጥያቄ ፈጽሞ አስቀርቻለሁ፡፡
ለመሰናበቻ፡፡ ምን ጊዜም ስንጽፍ የልጅነታን ነገር ትዝ ይለናል - ያለፈው፡፡ ሳሲት ከተማ ላይ አንድ ደግ ሰው አለ፡፡ ባም ጋባዥ ነው፡፡ ሰዎች ስለሱ ሲያወሩ የሰማሁት ነገር ይገርማል፡፡ ‹‹ጋሼ እኮ ከተበደረም አይመልስም፤ ካበደረም አይጠይቅም›› ያሉት ነገር ገርሞኛል፡፡ የማይመልሰው እየረሳው ሳይሆን አይቀርም፡፡

2017 ኦክቶበር 5, ሐሙስ

የቱ ግቢ?


ግቢ የሚለው ቃል ሲነሳ በእርስዎ አእምሮ ምን ይመጣል?
ጽሑፉን ከማንበብዎ በፊት አስተያየት መስጫው ላይ ይጻፉልኝ፡፡
ሁለት ዲያቆናት ግቢ ሲሉ የቤተክርስቲያኑን ቅጥር ግቢ ለማለት ይሆናል፡፡
ሁለት ሸኮች የመስጊዱን
ሁለት እስረኞች የእስር ቤቱን
ሁለት ኮማሪቶች የሆቴሉን
ሁለት ዳኞች የፍርድ ቤቱን….
በዕድሜ መስመር ወደ ኋላ ሄጄ ሳስብ ‹ግቢ› አንድ ትርጉሙ ይታየኛል፡፡ ይኸውም የብረታብረትና የሸክላ ስራ የሚሰራባቸው ስፍራዎች ግቢ ይባሉ ነበር፡፡ አንድ ሰው ‹‹እስቲ ግቢ ልሂድና ማጭድ ላሰራ፣ አያ ታችበሌ›› ሊል ይችላል፡፡ እነዚህ የዕደጥበብ ሰራተኞች ተገልለውና የራሳቸውን ሰፈር መስርተው የሚኖሩበት ቦታ ግቢ እንደሚባልና ልጆች እንደማይሄዱበት እናውቃለን፡፡ ተከብሮና ተፈርቶ የሚኖር አካባቢ ነው፡፡ ለመንደሩ ምስረታ መነሻ የሚሆነው ግን ሰዎቹ በማህበረሰቡ መገለላቸው ነው፡፡ እነሱም ወደ ሌላ ሰፈር እንዲሄዱ አይፈለጉም፡፡ ማህበር፣ እድር፣ ጋብቻም ውስጥ አይካተቱም፡፡ ዉበት አላቸው ቢባልም አይቀርቧቸውም፡፡ ሰውን አተኩረው ካዩ ‹ቡዳ› ተብለው ይሰደባሉ፡፡ ሲደነግጡ ‹አይበሉም› ስለሚባል - መብላት ብሎ ጣጣ! አሁንም ይህኛው የግቢ ትርጉሙ ነው በአእምሮዬ የሚመጣው፡፡ ‹‹ማጭድ ላላሰራ ወይ ቢላዋ፤ ግቢ አልሄድም›› ዓይነት ሃሳብ በውሳጤ ይመላለሳል ግቢ በተነሣ ቁጥር፡፡
ጊዜ ያነሣቸው ቃላት
ግቢ የሚለውን ቃል አሁን አሁን በተደጋጋሚ መስማቴ በፊት የነበሩ አንዳንድ ዘመን - አመጣሽ ቃላትን እንዳስታውስ ያደርገኛል - በሰፈርም ሆነ በፖለቲካው ዘንድ ሰው ሙጭጭ የሚልባቸው ቃላት ነበሩ፡፡ አሁንም ወደፊትም ይኖራሉ፡፡ ‹‹እንደ ወረዳ፣ ከዚህ ጋር ተያይዞ፣ ቀላል፣ አደል…›› የመሳሰሉትን አስታወስኩ፡፡ ‹‹እንደ ወረዳ›› ሲሉ ‹‹እነዚህ ሰዎች ይህ ወረዳ ለአቅመ-ወረዳ አልደረሰም ማለታቸው ነው፤ ወይስ ወረዳ ተብዬ ማለታቸው ይሆን እላለሁ›› ጥሬ ቃሉን ብቻ እያሰብኩ፡፡ ድንገት ቦግ ያለች አጠቃቀም ነች፡፡ ቃሉ ሳይበረዝ በፊት ‹‹እንደ እህት ሆና አስታመመችኝ›› የመሳሰሉትን አባባሎች አስታውሳለሁ፡፡
‹‹ተው አትሽጥ ሲሉት በሬውን ሸጠና
ተው አትግዛ ሲሉት ምንሽር ገዛና
ደሞ እንደ ወንዶቹ ቆላ ወረደና
ሲነፋጠጥ መጣ ነጠቁኝ አለና››
በሚለው የቃል ግጥም ውስጥ ‹እንደ ወንዶቹ› ከሚለው አንጻር እዩልኝ እንደ ወረዳን - አስፋልት-የለሽ ወረዳ - ማለታቸው ይመስለኛል፡፡
የዩኒቨርሲቲ መምህራንስ?
በዚህ ጉዳይ ላይ ውይይት እንዲነሳ አድርጌ ነበር፡፡ ለማ ሚደቅሳ ‹ግቢ› ከበፊትም የነበረ እንደሆነና የሱ ታላላቆች ሳይቀር ይጠቀሙት እንደነበር ትዝ ይለዋል፡፡
አማን ቃዲሮ ግን ‹‹ግቢ ዩኒቨርሲቲን አይወክልም፡፡ የምን ግቢ ነው የሚወራው? ግቢ ኮምፓውንድ ነው እኮ፡፡ ስለ ካምፓስ ስለሆነ የምናወራው አንድ በሉኝ›› ይለናል፡፡
ለማ በበኩሉ ‹‹‹ግቢ እንገናኝ› ይባላል፤ ማለትም - ካምፓስ - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ - 6 ኪሎ - 5 ኪሎ መሆኑ ነው›› ሲል ይቀጥላል፡፡ ሁለት ከምፓስ ሲኖር ዋናው ግቢምሚባ ነገር አለ፡፡ አአዩ ለዚህ አንድ ምሳሌ ነው፡፡ ‹‹በሌላ በኩል ሰፈራችን ውስጥ የያንዳንዱ ሰው ቤት ግቢ ነው››፡፡
አሁን ግቢ በጣም ዝነኛ ከመሆኑ የተነሣ አንድ ግቢ በሚል ቃል የሚጀምር አደረጃጀት አለ - ግቢ ጉባኤ ይባላል፡፡ ሰለግቢ ጉባኤ የሰማሁት ከዐሥር ዓመት በፊት ስለነበር ይህ ቃል እውነትም የቆየ ይሆን እንዴ አሰኝቶኛል፡፡ በተያያዘ ዜና ‹ግቢ› ቤተመንግስትንም ያመለክታል፡፡ ግቢ ገብርኤል የተባለው ለዚያ ይመስለኛል፡፡
እኔ ስማርም አልፎ አልፎ ቃሉ - ግቢ - ጥቅም ላይ ይውል የነበረ ይመስለኛል፡፡ ኦሮሞ ጓደኞቼም በቋንቋቸው ሲያወሩ ‹ሞራ› የሚለውን ቃል ይጠቀሙ ነበር፡፡ የግቢ ትርጉሙ መሆኑ ነው፡፡
አጋጣሚዎችም አሉኝ ግቢን አስመልክቶ፡፡ ራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻህፍት በዚህ በክረምት ስሰራ ተጠቃሚዎች መታወቂያ አስይዘው መጽሐፍ ስለሚዋሱ መጽሐፉን ሲመልሱ ምን ዓይነት ቀለም ነው መታወቂያው ስላቸው ‹‹የግቢ ነው›› ይሉኛል፡፡ ተማሪዎቹ በየዩኒቨርሲቲው የሚማሩ የደብረብርሃን ልጆች በመሆናቸው የተለያዩ ዓይነት መታወቂያዎች በየዩኒቨርሲቲው አሉ፡፡ ስለዚህ በኔና ነሱ መሃል ግቢ የሚለው ቃል ሊያግባባ አይችልም፡፡
በሌላ አጋጣሚዬ የመኪና ረዳት የሆነ ልጅ ባለፈው ከአዲስ አበባ ስንመጣ አንዲቱን ተማሪ ተዋውቋት ወሬ ጀመሩ፡፡ ከወሬው የሰማሁት ‹‹የት ነሽ ግቢ?›› የሚለው ጥያቄው አሰቆኛል፡፡ ግቢ ለሱ ምኑ ነው፡፡ ምናባት ለሱ ግቢ ተብሎ መጠራት የሚችለው መናኸሪያው መሆን ነበረበት፡፡ ከዩኒቨርሲቲ ውጪ ላለው ግቢ ምኑ ነው? ተማሪዎች ‹‹ግቢ እንደዚህ አድርገን›› ሲሉ ሲሰማ ‹‹እኔም ከናንተው ቡድን ነኝ›› ለማለት የሚጠቀምበት ይሆናል፡፡ ስለ ትምህርት ቤታችሁ አውቃለሁ ማለቱ ይሆናል፡፡ እንደሷ ግቢን እንደሚያውቅ በማሳየት በመካከላቸው ያለውን ርቀት ለማጥበብ የተጠቀመበት ዘዴ ይመስለኛል፡፡
ዩኒቨርሲቲ የሚለውን መጥራት ካለመቻል?
ለኔ ከዋነኛ የግቢ ዝነኝነት ምንጮች ውስጥ አንዱ ይህ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲን አስተካክሎ መጥራት የሚችለው ሰው ከቀን ወደ ቀን እየቀነሰ መሄዱን ታዝቤያለሁ፡፡ ስለዚህ ግቢ ጥሩ መደበቂያ ነች፡፡ በር ላይ በጉልህ የተጻፈልንን ማንበብ ካልቻልን ለሌላ ዕውቀት ምን ዓይነት በር እንከፍታለን? ተመልካችነታችን የታለ?
ከዩኒቨርሲቲው ዉጪ ሆነው ስለ ዶርም፣ ካፌ፣ ክላስ፣ ላብ፣ ሳይሆን ባጠቃላይ ስለ ግቢ ነው የሚያወሩት፡፡ አፍ ላይ ደስ ይላል ልበል? አዎ፣ በእርግጥ ቅለትም አላት፡፡ ሁለት ፊደላት ናቸው፡፡

2017 ኦክቶበር 1, እሑድ

The African Storybook Initiative in Ethiopia

The initiative has been undergoing a phenomenal literacy work in the continent. Recently, Ethiopia has been selected as one of the countries to benefit from African Storybook’s (ASb) activities. The purpose of this blog is to assess what is going on.
Partnerships:
ASb partnered with governmental, non-governmental and private institutions to achieve the goals set in promoting early childhood literacy. As far as I know, due to these endeavors, mobile applications have been developed for Amharic and Afaan Oromo, students have been invited to assist in translation, writing and promoting, and story development workshops have been held. Such synergistic coalitions shall improve the quality and quantity of what is being done in Ethiopian languages.
Visits:
Lisa, Dorcas and Fatima visited Ethiopia and facilitated the activities held. The frequent visitor is Dorcas, who is from Kenya, a neighbor of Ethiopia. The explanations these visitors give, the friendly atmosphere they create during meetings and throughout their encounters with people here, has made ASb popular, at least among people who heard of it. I was also invited to a workshop in South Africa to learn about the new and updated website. This eye-opening visit made me appreciate the efforts everyone at ASb exerts! As young people, I and my friends should learn from the persistence of everyone at ASb.
Published:
Stories written by participants of workshops and story writing competitions in Ethiopia have been published on the website (africanstorybook.org). This hopefully encourages both the writers and others who take them as role models. There are many more writers, stories, ideas and concepts to use in the country. It is the amount of the trainings, reading and practice that should be focused up on to tap our potentials.  
Translations:
As stories should cross borders of various kinds, translation is of a paramount importance. Unquestionably, though, these translations should be thoroughly evaluated before they reach the children. Let me mention my own encounter. Last summer, I gave the librarian at Ras Abebe Aregay Library, Debre Birhan, my translation of ‘Greedy Kiundu’. I changed the names of people and places to local ones to familiarize the story with the children who read in the target language. When the librarian, a young girl of 21, was done with reading, she asked me if I mean the residents of the village I mentioned were as gluttonous as Mr. Kiundu. I explained the reason why I used the name of that place and she calmed down. Since books cannot answer all readers’ questions once they fly out of our hands, care should be taken. The collection of translated stories mainly in the three major Ethiopian languages is growing. This will have a huge impact on the children who read them.
Original Ethiopian Stories:
Ten Tigrigna stories are being processed for publication. In addition to this, their English translations are also available. This is a fruit of a workshop held at Adwa and supervised by the ASb delegation mentioned above. I hope stories from the other languages will also be made available in the future. I say this because stories are best appreciated in their original forms than in translation. Some stories written in English were also published. ‘Petros and his dog’ is one of them. This encourages the writers who have to grapple with the medium, a foreign language, and the content suitability of the stories. We may see these children among the writers of their country in the time to come. Guess what I say to them when I hand them copies of their stories! “You are just like Achebe or Ngugi – you are a published African writer!”
Accessibility:
I wish I wrote this in gold. As to me, it is an issue of urgency. Obviously, I am happy that the stories are published, translated and assessed by a number of volunteers, commissioned people and ASb staff. But the question that everyone of us should worry about is whether our ultimate objective is met. I know I shouldn’t give up just here because it may improve in the future. Should we wait until it improves or should we take proactive measures? Let me make this point clear. The stories for which everyone of us strived to get published are not reaching the target children! The children do not have mobile phones, tablets or computers. They cannot access these fancy apparatuses. The laptop and projector donated to our library, for example, are doing a great job. If many of them are distributed among schools, the scenario would change for the good. Can anyone afford to buy these? We may not. What about distributing hard copies? I think this is feasible. So, we should find a means like this to achieve our goal and reach the children. I tried to distribute CD copies of the stories to schools in Debre Birhan town by going there. On the other hand, my effort to get the stories printed at the Debre Birhan Uuniversity, with whom we signed an MOU, is still awaiting some officials’ willingness. I have some working plans which I may mention in my next blog.

2017 ሴፕቴምበር 2, ቅዳሜ

ደጋ…ግሞ ማዳመጥ  የታከተው መምህር




ከትምህርት ተመልሶ ተገናኘን፡፡ ከኔ ጋር ያወራነው በመሃላችን ብዙም የተለመደ ወሬ አይደለም፡፡ ስለ ፍጥነት ንባብ ነበር፡፡ በዚህ ጉደይ ላይ ከዚህ ውይይታችን በኋላ አስፈላጊውን ዶሴ በአድራሻው ልኬለት አመስግኖኛል፡፡

‹‹የጥበብ ሰዎች ሳይቀሩ በቴሌቪዥን ላይ ተመሳሳይ የዱሮ ወሬ ማውራት ልማዳቸው ነው፤ ምክንያቱም ሌላውም ጓደኛቸው ሲደጋግመው ስለሚውልና ስለማይሳታቸው ነው›› አለኝ፡፡ የወሬ መደጋገም አሰልችቶታል፡፡ ከመገናኛ ብዙሃን እስከ መስሪያቤት፣ ከቤተሰብ እስከ ጓደኛ ሁሉም አዲስ ነገር አልባ ሆነውበታል፡፡

‹‹ጓደኛህን አግኝተኸው ባለፈው ያወራህን ተመሳሳይ ወሬ ያወራሃል፡፡ ‹እሱን እኮ ባለፈው ነግረኸኛል››› ስትለው አይሰማህም፡፡ ‹‹ለምንድነው ግን ሰዎች አዲስ ወሬ ያጡት›› ሲል አማረረ፡፡  

ይህን የወሬ መጠንዛት የታዘቡ ታዝበዋል፤ የተማረሩ ተማረውበታል፤ የሰለቻቸውና ድፍረቱን ያገኙ አልፈው ተናግረዋል፡፡ አዲስ ወሬ ከየት ሊገኝ እንደሚችል ነጋሪና መካሪ ያሻቸው ይሆን? ሳይሆን አይቀርም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን ደጋግመወው ቢያወሩ የማሰለቹ አሉ፡፡ የመንግስቱ ለማን ፍጡር አለቃ መክፈልትን አስታወስኩ በግሌ፡፡

‹‹ስለችግርህ ማውራት ስትችል ለምን ከዱሮ ጋር ትንገታገታለህ፤ ከራስህ ጋር ስታወራ ነው መፍትሔ የሚመጣው፡፡ ለራሳችን የማሰቢያ ጊዜ ሲኖረን ነው መፍትሔና ለውጥን የምናመጣቸው፡፡ እስኪ የቅድመ ምረቃ ትውስታ ማውራት ለኛ ምን ይጠቅመናል?››

‹‹ወሬኛ ሰው ደግሞ ያለ ምንም ዳራ ያወራሃል፡፡ ሲፈልገው ቤቱ ሊበላኝ ነው ይልሃል፡፡ አሁን ነገሩ ያው ወጣቱንም ያየህ እንደሆነ Noshall ሆኗል፡፡ – without social life የሚኖር ነው - በቅርቡ የሳማሁት ጥሩ አገላለጽ ነው፡፡ ምናልባት ያለ የሌለ ወሬ ማዳመጥ ሲሰለቸው ሊሆን ይችላል፡፡ ስለችግርህ ለበርካታ ቀናት ቤት ዘግተህ ተቀምጠህ መነጋገር ትችላለህ፡፡ ቤት ካልዘጋህ እኮ ማንበብ አትችልም፡፡ ገለባ ነው የምትሆነው፡፡ ዘፈኖች ራሱ ይገርሙኛል፡፡ ጨፍር ተዝናና ይሉሃል፡፡ አዲስ ነገር አይታይባቸውም፡፡››

ወንድሜ ጽናቱን ይስጥህ፤ አዲስ ወሬም አይንሳህ፤ የድርሻህን ለመወጣትም ሞክር እላለሁ!

2017 ኦገስት 21, ሰኞ

‹‹ይሄ የማነው ቤት የደራ የኮራ የምኒልክ ነዋ የዚያ የቀብራራ!››



በመዘምር ግርማ የተጻፈ የጉዞ ትውስታ

ጠባሴ፣ ደብረብርሃን፡፡

14.12.2009 ዓ.ም.



ወጧ የጣፈጠላት ባልቴት መስለናል



ብዙዎቻችን ይህችን ቀን ስንናፍቅ የነበርን ሰዎች ወጣችን ጣፍጧል፡፡ ጠባሴ፣ ደብረብርሃን፣ በራስ አበበ ቤተመጻሕፍት ተመዝግበው በዕለተ-እሁድ 14.12.2009 ወደ እንቁላል ኮሶ፣ አንጎላ፣ ጉዞ ያደረጉ 75 ወዳጆቻችንን የፈካ ፊት ስናይ ነው የዋልነው፡፡ በስፍራው የተገኘው ህዝብ የነበረው የአብሮነት ስሜት፣ የአገርና የንጉሥ ፍቅር ብርቱ ስሜትን የሚያጭር ነው፡፡




የአንጎለላ አድባር መርቃችኋለች፡፡



ሰውኛ ፕሮዳክሽን፣ መገዘዝ መልቲሚዲያ፣ ደብረብርሃን ዩነቨርሲቲ፣ የባሶ ወረዳ፣ የሰሜን ሸዋ ዞን፣ የተለያዩ ግለሰቦች፣ ድርጅቶችና ለዚህ ክብረ-በዓል መስመር የተጉ ወገኖቻችን ባይኖሩ አኛም ለዚህች የደስታ ብስራት ባልበቃን ነበር፡፡ እናመሰግናለን - ባያሌው፡፡ የወጣችሁና የወረዳችሁትን የምታውቁት እናንተ ስለሆናችሁ እኛ ድካማችሁ መሉ በሙሉ አይገባንም፡፡ 



የዝግጅቱ ሂደት



አንዳንድ ወገኖቻችን ከአዲስ አበባ በፌስቡክ የተለቀቀውን ቅስቀሳ አንብበውና አዘጋጆቹን አነጋግረው በአጤ ምኒልክ፣ በእቴጌ ጣይቱና በፊታውራሪ ገበየሁ ልደት አከባበር ላይ እንድንሳተፍ ይወተውቱን ገቡ፡፡ እንኳንም አነቁን፡፡ አንዱ ዳምጠው አድማሱ ነበር፡፡ ወጣቱ የሒሳብ አያያዝ ምሩቅ ሚኪያስ ካሣዬ በአንጻሩ ‹‹እኛ በያመቱ እዚህ ደብረብርሃን ስለምናከብር ለምንድነው ሌሎች ባዘጋጁት ዝግጅት ላይ የምንሳተፈው?›› የሚል ተቃውሞ አንስቶ ነበር፡፡ ሚኪዬ ምን መሰለህ? ለብቻህ የምታደርገውና ተሰባስበህ የምታደርገው ነገር ውጤቱ ይለያያል፡፡ ያንንም ዛሬ የታዘብክና የረካህ ይመስለኛል፡፡

ይህ ምክክር የተካሄደው ከዝግጅቱ አንድ ሳምንት በፊት በነበረው ሐሙስ ነበር፡፡ ለነገሩ የፌስቡክ ማስታወቂያውን እኔም ሳላየው ቀርቼ አይደለም፡፡ ያዘናጋኝ ነገር ቢኖር የቤተመጻሕፍቱ ባልደረቦች በጉዞ እየተቀዛቀዝን መሄዳችን ነበር፡፡ ባላፈው ወደ ግድብ እንደናደርግ በተቀጣጠርነው ጉዞ ላይ ስምንት ሰው ብቻ መገኘቱ ያልተጠበቀ ነገር ስለነበረ አሁንም ጉዞ ጠርተን የሚቀረው ይበዛል ብዬ ነበር፡፡



ዘንድሮም እንዳምናው

ምን አዚም እንደያዘን አላወቅም፤ ባለፈው ዓመት ከዘንድሮው የላቀ ዝግጅት አድርገን ዘንድሮ ግን ተቀዛቅዘናል፡፡ የጓደኞቻችን ውትወታ ባይኖር በዓሉ ተቀዛቅዞ ባለፈ ነበር፡፡  ባለፈው ዓመት እኮ ከዩኒቨርሲቲ የአዳማ ልጅ የክረምት የታሪክ ተማሪ ጋብዘን ነበር በደማቅ ውይይት ያከበርነው፡፡ ቦታ ጠቦ መሬት ላይ ተቀምጠን አታስታውሱም? ባለፈው ሐሙስ በነበረን ሳምንታዊ የውይይትና የስነ-ጽሁፍ ምሽት የሦስቱን ጀግኖና የራስ አበበ አረጋይን ልደት አክብረናል፡፡ ራስ አበበን ግን አትርሱብን!

ባለፈው አርብ ዕለትም በጌትቫ ሆቴል የልደት አከባበሩ በደብረብርሃን ወጣቶች ተካሂዶ ነበር፡፡ ወድንኳኗ ውስጥ ያደረግነው ውይይት የሚዘነጋ አይደለም፡፡ አሁን ዶክተር አዲሱ ይህን በፌስቡክ ስላስታወስከኝ አመሰግናለሁ፡፡




 የዛሬ ውሏችንን እነሆ!



ከማለዳው 12፡00 ከእንቅልፌ ተነስቼና ባጭር ጊዜ ዝግጅቴን ጨራርሼ ወደ ቤተመጻሕፍቱ በማቅናት ቤቱን አሳምር ጀመር፡፡ ወንበሮችን በሙሉ ወደ ውጪ አውጥቼ አስቀመጥኩ፡፡ መጻሕፍቱን አውደ-ርዕይ በመሰለ መልኩ ደርድሬ በቤቱ ላይ ውበት ዘራሁበት፡፡

ልክ እንደትናንተቱ ስልኬ አሁንም አሁንም ይጮሃል፡፡ እኔም መልስ እሰጣለሁ፡፡ እየረፋፈደ ሲሄድ ተጓዦች ይሰባሰቡ ጀመር፡፡ የቲሸርት ያለመኖር ችግር ሁሉንም ያስቆጨ ስለሆነ ለብዙዎቹ ቅሬታ ምንጭ ሆኗል፡፡ ከአዲስ አበባ ይመጣል የተባለው ሳይመጣ ስለቀረ ነው የኛ መቀዛቀዝ እንጂ እዚሁ ማሰራት በተቻለ ነበር፡፡ እድሜ ለኢሳይያስ ፍቅሬ - 30 ቲሸርት አሰርቶ ለተወሰኑት ሰዎች አምጥቶልናል! ተዘጋጅቶ ቢሆን ኖሮ በመቶዎች የሚቆጠር ቲሸርት ሊሸጥ እንደሚችል እተማመናለሁ፡፡

ተጓዦች በአቅራቢያችን ባሉ ካፌዎችና በቤተመጻሕፍቱ በበረንዳ ቡናና ሻይ ሲጠጡ፣ ሁለቱ መኪናዎቻችን መጥተው ቆሙ፡፡ ደረጀ ጌታቸው እነዚህን መኪኖች በጥሩ ዋጋ ስላመጣልን አመሰግናለሁ፡፡ ክፍያው በሰላሳ ብር በነፍስወከፍ ስለሆነ ለዳቦና ለለስላሳ ገንዘብ ተርፎን ለስላሳ ለሌሎችም ተሳታፊዎች ለመጋበዝ ተችሎናል፡፡ ይህን ግብዣ ላስተባበረችው ለጌጤ ፈለገ ምስጋና ባያሌው!

ከጠዋቱ 1፡30 እንነሳለን ብዬ የቀጠርኳቸው ሰዎች ተሟልተው (ግማሹ በስልክ ጉትጎታ) ከጠዋቱ 3፡00 አካባቢ ተነሳን፡፡ ጉዞ ወደ አንጎለላ፡፡ ስፍራው ስምንት ኪሎሜትር ስለሚርቅ የደረስንው በአንድ አፍታ ነበር፡፡ የክረምት ልምላሜው የሚያስደስት መስክና ማሳ ይታየናል፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ወደ ኩሳዬ ትምህርት ቤት፣ ጅሩ፣ ወደ ራስ አበበ አገር ለወላጆች በዓል ስሄድ እንደጻፍኩት ይህን መስክ እነራስ አበበ አረጋይ ያባረሩት ፈረንጅ እንዳያይብን ጸልዩ ብያችሁ ነበር፡፡ ጸሎታችሁ ከደመና በታች ቀርቶ ይሁን ጨርሶ ሳትጸልዩ ረስታችሁት ይህ መንገድ ግራና ቀኙ ዓይን እየበዛበት ነው፡፡ ዓይን ብቻ አይደለም፣ ገመድም ተመትሮበታል!



‹‹ይሄ የማነው ቤት የደራ የኮራ

የምኒልክ ነዋ የዚያ የቀብራራ!››



እንዲህ እያልን በሆያ ሆዬ ወደ አንጎለላው ክሊኒክ ግቢ ስንቃረብ የነበረውን ትዕይንትና የስለት ስምረት ስሜት የነበራችሁ ታስታውሳላችሁ! በቅርቡ በአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ትብብርና ጥረት እንደገና ስራ እንዲጀምር የተደረገው ይህ ክሊኒክ ዛሬ አምሯል፡፡ በባንዲራ አሸብርቋል፡፡ በብርቅዬ አርቲስቶቻችን፣ በምሁራን፣ በአካባቢው ማህበረሰብ አባላት፣ በመንግሥት ተወካዮችና በበርካታ እንግዶች ተሞልቷል፡፡ የአጤ ምኒልክና የእቴጌ ጣይቱ ምስል ያለባቸውን ቢጫ ቲሸርቶች የለበሱ ሰዎች በግቢው ውስጥ ይታያሉ፡፡ ፎቶ መነሳት፣ ስራ ማስተባበር፣ በዓል ማክበር ይዘዋል፡፡ በወርቀዘቦ ጌጥ የተሰራ ጥቁር ቲሸርት የለበሱም አሉ፡፡ አጤ ምኒልክ እንደሚያደርጉት ሁሉ በነጭ ጨርቅ ራሳቸውን ያሰሩ ሰዎች ይታያሉ፡፡ ባዶ እግሩንም የሆነ አይቻለሁ፡፡ የኛ የደብረብርሃኑ ቡድንም ቀይ ቲሸርት ለብሶ መቀላቀሉ የበለጠ ድምቀትን አመጣ፡፡ ሁሉም በደስታ ስሜት ፎቶ ይነሳል፣ ይጨፍራል፣ ይዘምራል፡፡ ዝግጅቱ ጀመረ፡፡

ለበዓሉ ከዞኑ፣ ከወረዳውና ከዩኒቨርሲቲው የተጋበዙት እንግዶች አጤ ምኒልክን በብዙ የአሀኑን መንግሥት በመጠኑ አሞገሱ፡፡

አጤ ሚኒልክ፣ እቴጌ ጣይቱና ፊታውራሪ ገበየሁ ልደታቸው ሲከበር የታወሱ ግጥሞች አሉ፡-

‹‹ባቡሩም ሰገረ ስልኩም ተናገረ

ምኒልክ መልዓክ ነው ልቤ ጠረጠረ››

ምኒልክ ተወልዶ ባያነሳ ጋሻ

ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ጊዜ አበሻ
ትዝ ይሉኛል፡፡



ሽልማትና ችግኝ ተከላ

ለበዓሉ ስምረት አስተዋጽኦ ላደረጉ ግለሰቦችና ድርጅቶች የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተ፡፡ በፈረስ ጉግስ ውድድር ላሸነፉ ሰዎችም ሽልማት ቀረበ፡፡ ይህም ሽልማት የዳቦና የፎቶ ነበር፡፡ ፎቶዎቹ በጥሩ ሁኔታ የተሰሩ የአጤ ምኒልክና የእቴጌ ጣይቱ ነበሩ፡፡ ዕውቅናው ለወደፊትም የሚያበረታታ በመሆኑ ያስደስታል፡፡

ከህብረተሰቡና ከተሳታፊው የተመረጡ 12 ሰዎች የንጉሡ እትብት በተቀበረበት ስፍራ የኮሶ ችግኝ ተከሉ፡፡ ቦታው እንቁላል ኮሶም አይደል! ቦታውን አሳምረው ያሳጠሩትን የእምዬን ወዳጆች ማመስገን ይገባል፡፡




የመጨረሻው መጀመሪያ

ዝግጅቱ ሊያላልቅ ሲል ዝናቡን አመጣዋ! አብዛኞቻችን ከድንኳን፣ ሌሎቻችን ደግሞ ከክሊኒኩ በረንዳ ተጠለልን፡፡ በዝግጅቱ ላይ አንድ ዘፈን እንዲያቀርብልን የፈለግነው የኛ ቡድን አባል መምህር ታደለ አንባዬ እንዲያቀርብ ብጠይቅም ጊዜ የለንም አሉ እንጂ ጣዕመ-ዜማም እንሰማ ነበር፡፡ እጅግ የተደሰትንበት ይህ ዝግጅት አልቆ ወደየመኪናዎቻችን አቅንተን ያለንን ዳቦና ለስላሳ ቀማምሰን ጉዞ ወደ ደብረብርሃን ሆነ፡፡ ግማሾቹ ጎብኝዎች ወደ አንጎለላ ኪዳነምህረት ሄደው የንጉሥ ሣህለሥላሴን ቤተመንግስት ፍርስራሽና የፊታውራሪ ገበየሁን አጽም ሳይጎበኙ አልቀሩም፡፡ እኛም በመጪው ዓመት ማየት ይኖርብናል፡፡ ምንም እንኳን እኔና የተወሰንነው ጓደኞቼ በየካቲት የዓድዋን በዓል በማሰብ በየዓመቱ በምናደርገው ጉዞ እየጎበኘነው ቢሆንም፡፡ ሌሊት በመነሳቴ ስለደከመኝ የጥናትና ምርምር መድረኩ ላይ በሕይወት ሆቴል ባልገኝም አስተማሪ መድረክ እንደነበር የተገኙ ወዳጆቼ ነግረውኝ ተደስቻለሁ፡፡

ከዚህ ዝግጅት ብዙ ትምህርት ቀስመናል፡፡ ለወደፊቱም የምናደርጋቸውን ጉዞዎች (የአንኮበሩን የየካቲት 23ቱን ጨምሮ) እንደዚህ ማቀናጀት ይኖርብናል፡፡ ለዝግጅቱ ብዙ ወጪ ያወጡት ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የገንዘብ ድጋፍ ሳናደርግላቸው ይህን ዝግጅት ስላደረጉልን ብዙ መስዋዕትነት ሳይከፍሉ አልቀሩም፡፡ ለወደፊቱም ደብረብርሃንም የራሷን ብትወጣና ከስፖንሰር የጸዳ የበዓል አከባበር ብናደርግ ደስተኛ ነኝ፡፡ ራስን የመቻልን ትምህርት ምኒልክ ሳያስተምሩንም አልቀሩ!



ማሳሰቢያ

አጤ ምኒልክን የማይወዱ ሰዎች አለመውደዳቸውን በደንብ እንዲመረምሩት አሳስባለሁ፡፡ እንደባለፈው ሳምንት ሁሉ ይህንን ጽሑፍ በአሉታዊ አስተያየት እንዲያበላሹብኝ አልፈልግም፡፡ ቢጽፉም የማይሆን ምላሽና ስድብ አትመልሱላቸው፡፡ አሉታዊ ነገር ሲበዛ ዓላማችንን ስለምንስት፡፡ ከፌስቡክ ወዳጅታቸውም ባትሰርዟቸው - የሐሳብ ብዝሃነት ስለማይከፋ፡፡   

ስለጉዞው የዘነጋሁትን አናንተ ሙሉልኝ፤ ፎቶዎቻችሁንም በአስተያየት መስጫው ላይ አስገቡልኝ፡፡    

2017 ኦገስት 14, ሰኞ

ጥርሠ-ፍንጭቱ ከበርቴ ይመክራችኋል


(ማህበራዊ ሚዲያችን ለምን የምንፈልገውን ሰው ብቻ ማሰባሰቢያ ሆነ?) እና ሌሎችም
የጽሑፉ ርዝመት 1496 ቃላት፤ የሚፈጀው ጊዜ በአማካይ 10 ደቂቃ

ስትራይቭ ማሲይዋ  ይባላል፡፡ ዝምባብዌያዊ ቢሊየነር፣ ሥራ ፈጣሪና በጎ አድራጊ ነው፡፡ ዕድሜው 57 ዓመት፡፡ በቅርቡ ወደ ዳሬ ሠላም ብቅ ብሎ ከወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ጋር የንግግርና የምክር ቆይታ አድርጓል፡፡ እኔም እንግሊዝኛ ለምትረዱ ቪዲዮውን አጋራችኋለሁ፡፡ በትናንትናው ማለትም ሐምሌ 7፣ 2009 ምሽት ከሌሊቱ 8፡20 ድረስ ያስቆየኝ ስራ የዚህን ሰው የመድረክ ቆይታ ማድመጥና ማስታወሻ መውሰድ ነበር - ሰባት ገጽ ማስታወሻ በደብተሬ ወስጃለሁ፡፡ ለኔ በጣም ያስደሰተኝና ፍላጎቴ የተነቃቃበት ይህ ትምህርት እናንተን እንዴት እንደሚያደርጋችሁ አላውቅም፡፡ በስራ ፈጠራ፣ በቢዝነስ፣ በበጎ አድራጎት ምን ደረጃ ላይ እንዳላችሁ የምታውቁት እናንተ ስለሆናችሁ፤ በትምህርቱ ላይ የሚኖራችሁን ፍላጎት እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይቻልም፡፡
ጥቁር ሀብታም ሁሉ ናይጀሪያዊ ነው ብዬ ላመንኩት ለኔ ስትራይቭ ናይጀሪያዊ ነበር፡፡ ዛሬ ይህን ጽሑፍ ለማዳበር ስል የቃኘሁት አንድ ድረ-ገጽ ግን ግምቴ መሳሳቱን አስረዳኝ፡፡ ይሁን እንግዲህ፣ ማነው ናይጀሪያ ብቻ ትበልጽግ ያለው? አላሙዲን፣ ዳንጎቴ፣ ኖህ ሰማራ፣ ጃክ ማ፣ ቢል ጌትስ፣ ዋረን ባፌት፣ ኦፕራ፣ ትራምፕ እያልኩ ቢሊየነሮችን እግር በእግር እየተከታተልኩ ያለሁት ለምን ይመስላችኋል? መልሱን ከንባቡ በኋላ ልትገምቱት ትችላላችሁ፡፡
በዝምባብዌ፣ በዛምቢያና ስኮትላንድ የተማረው ይህ ሰው እናቱን የስኬቱ አርአያ ያደርጋቸዋል፡፡ ‹‹በሌሊት እየተነሳች የምትሰራበት ትጋቷ አርአያ ሆኖኛል›› ይላችኋል፡፡ የእርስዎስ እናት እንዴት ነበረች? እኔ ምናልባት አያቴ ልትሆን ትችላለች ትጉህ፡፡ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት በፊት እነሱ ቤት አይተኛም፡፡ ‹‹የርቀት ብትማሪ እኮ ዶክትሬት ትይዢ ነበር›› እላታለሁ ለአያቴ፡፡
በዝምባብዌ ይሰራበት የነበረው የቴሌኮም ድርጅት ስራ ወጣቱን የ26 ዓመት መሐንዲስ ሊያረካው አልቻለም፡፡ አንድ ሰው በአማካይ ስልክ ሊገባለት የሚችለው ካመለከተ ከ14 ዓመታት በኋላ መሆኑ ስላበሳጨው ስራ ለቀቀ፡፡ ለዚህም የስልክ ችግር መፍትሔ ይፈልግለት ገባ፡፡ ያም እንዴት እንጀራ እንደፈጠረለት ታያላችሁ፡፡
እኔኑ ራሴን ‹‹አሁን ባለሁበት ሁኔታ በትምህርት፣ በጊዜ አጠቃቀም፣ በሕይወት ዓላማ ልረካ ያልቻልኩት ለምንድነው?›› አስባለኝ፡፡ ‹‹አለመርካት የለውጥ መነሻ ነው›› ይላችኋል፡፡
ከመድረክ ላይ ለምትጠይቀው የታንዛኒያ ተወላጅ ምላሽ በመስጠት መድረኩን የተቆጣጠረው ማሲይዋ ትዊተር የለውም፡፡ ፌስቡኩ ግን በዛሬዋ ዕለት 2 473 163 አባላት አሉት፡፡ ‹‹ትዊተር ከፍቼ እንድትከተሉኝ ሳይሆን የጋራ መድረክ እንዲኖረንና እንድንነጋገር እንዲሁም እንድንሰራ ነው የምፈልገው›› ይላል፡፡ ፌስቡክ በማሳተፍ መጠኑ ከፍተኛ ያለው ይህ ገጹ በርካታ የስራ ፈጠራ ምክሮችና ውይይቶች የሚስተናገዱበት ነው፡፡ እሱ የሚለጥፋቸው ብቻ ሳይሆኑ እሱ በለጠፋቸው ምክሮችና ጽሑፎች ላይ የሚንሸራሸሩት መልሶች፣ ውይይቶችና ክርክሮች በአባላቱ ተሳትፎ ከማናቸውም የፌስቡክ ተጠቃሚ በላይ ያደርገዋል፡፡ ፌስቡክንና ስራውን እንዴት እንዳመጣጠነ ሲናገር ከአንድ ዩጋንዳዊ የዕድሜ ባለጸጋ ያገኘውን ምክር እንደ ሕይወት መርህ መጠቀሙን ያነሣል፡፡ ይህም ‹‹ለአስፈላጊዎች ነገሮች ጊዜ ፈልጉ፤ በጣም አንገብጋቢ ለሆኑ ጉዳዮች ግን ጊዜ ውለዱ›› ይላል፡፡ ለእናንተ ስል ጊዜ እወልዳለሁ፤ ጊዜ አድኜ አመጣለሁ›› ይላቸዋል፡፡
ወገኖቼ፣ ለኔና ለእናንተ አስፈላጊውና ጊዜ ልንወልድለት የሚገባው ገር ምንድነው?  ለእርሱ እኛን ማስተማርና ማሰልጠን ግድ የሚለው ነገር ሆነ - የደረሰበት የአስተሳሰብ ደረጃ! ድፍን አፍሪካን ያስተምራል፡፡
‹‹እናንተ ባለሐብት ለመሆን ሳይሆን የአፍሪካን ችግሮች ለመቅረፍ ተነሱ እንጂ ገንዘቡ ከዚያ ለራሱ ይጨነቃል›› ይላችኋል፡፡ ‹‹በርካታ ፍላጎቶችና ችግሮች ያሉባት አፍሪካ ትፈልጋችኋለች፡፡››
የዓለም አቀፉ የቴሌኮም ድርጅት የኢኮኔት ዋየርለስ መስራችና ስራ አስፈጻሚ የሆነው ይህ ሰው አፍሪካ ወደ ኋላ የቀረችባቸው ነገሮች ያሳስቡታል፡፡ ይህ የታላላቆቹ ስራ ፈጣሪዎች የታናናሾቹን ማሰልጠንና መደገፍ ጉዳይ በአሜሪካ እጅግ የታወቀና የተሰራበት ቢሆንም እኛ ጋ ገና ነው፡፡ ‹‹እስከዛሬ እንዲህ ስላልተደጋገፍን ቀኑ ዛሬ ነው›› ይላል፡፡ መቼ ማለት ብቻ! - በተግባርም ዘምቷል፡፡
‹‹መጽሐፍ ከምጽፍ ይልቅ በማህበራዊ ሚዲያ ብጠቀም እናንተን የተሻለ እንደማነቃቃ ስላወቅሁ ነው እዚያ የምንገናኘው›› ለሚላቸው ወጣቶች ጥያቄዎቻቸውን የሚመልሰውና ጽሑፎቹን የሚጽፈው ራሱ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ‹‹ብፈልግ ግማሽ ደርዘን ወጣት መቅጠር እችል ነበር›› ሲል ሌላውን የማያሰራ አቅጣጫ ያሳየናል፡፡
‹‹እናንት የአፍሪካ አሊባባ፣ ጉግል … መስራች የምትሆኑ ወጣቶች ትልቅ ድርጅት ስትመሰርቱ ግን ስሙን አፍሪካዊ አድርጉት - ልክ አንኔው ክዌሲ ቴሌቪዥን፡፡ የአስተሳሰብ አድማሳችሁን አስተካክሉ፡፡ የተለያዩ ዳራዎች ያሏቸው 54 አገሮቻችን የናንተን የተለየ የአስተሳሰብ አድማስና አተያይ ይሻሉ፡፡››
ወጣቶች ወደፊት በምን ዘርፍ ይሰማሩ ትላለህ?
‹‹እኔ በዚህ ስሩ በዚህ አትስሩ አልልም፡፡ የማህበረሰባችን ችግሮች ምንድናቸው የሚለውን አጥንታችሁ ተንቀሳቀሱ ነው የምላችሁ፡፡ የለውጥ ዕድሎች ያሉት ችግሮቹ ላይ ነው፡፡ ዕውቀቴና ክህሎቴ የትኛውን ችግር ለመፍታት ይጠቅማል የሚለውን ግን አትርሱ፡፡ ከዚህ በስተቀረ ሁሉም ዘርፍ የየራሱ ጥንካሬ አለው፡፡ በየትኛውም ዘርፍ ትልቅ ገንዘብ አለ - ግብርና፣ አይቲ፣ ሱፐርማርኬት …. ››
አሞራ በማዕበል የሚለው ለረጅም ጊዜ በፌስቡክህ ላይ በተከታታይ በተስተናገደው ጽሑፍ ላይ እስኪ ትንሽ ነገር በል፡፡
 ‹‹አሞራ እኮ ማዕበል ፈርታ ዛፍ ላይ አትወሸቅም፡፡ በማዕበሉ አልፋ ታድናለች፡፡ ከማዕበሉ ምን ተማርኩ ብለሽ ማሰብ አለብሽ፡፡ አፍሪካም ወደ ማዕበሉ እየመጣች ነው፡፡ አስደማሚ ለውጦች፣ ማዕበሎች፣ እርማቶች ይጠብቁናል፡፡ በዚያ ሁኔታ ውስጥ እንታገላለን እንጂ ሁኔታውን ራሱን አንታገለውም፡፡ ታላላቆቹ የምዕራቡ ዓለም ድርጅቶች የተመሰረቱት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት መሆኑን ልብ በይ፡፡ ታላቅ ማዕበል!››
አሁን ስትራይቭ ማሲዋ ወደኔ የአስተሳሰብ ደረጃ መጣልኝ - መዘምር ነኝ -
ባለፈው ስለ ስራ ፈጠራ ንግግር ሳደርግ ስራ ፈጣሪ ለመሆን ‹አይሰሩ - ሰሪ› መሆን አለባችሁ›› ብዬ ነበር፡፡ ይቺን አሁን ደገመልኛ! ‹‹ስትጀምሩት እኮ ምን ነካው ይህ ሰው ነው የሚያስብላችሁ›› አለ፡፡ ተቺዎች መቼም አሉ፡፡ በለንደን ፓርላመንት አደባባይ ያሉት ሐውልቶች ሲሰሩ የተቹ ነበሩ፡፡ አሁን ሐውልቶቹ አሉ፤ ተቺዎቹ ግን የሉም፡፡ ጭብጨባ!!!
‹‹ግትር ሳልሆን ችግርን ተቋቋሚ ነኝ፡፡ ማንም ሳይሰራው ለኔ የሚታየኝ የስራ ዕድል አለ፡፡ ስራ ፈጣሪነት ደግሞ በዘር ማንዘር አይመጣም፤ በስልጠና ነው - አንቺው ራስሽ ራስሽን አሰለጥኚው - እልሻለሁ፡፡ ፌስቡክ፣ ዋትዛፕ፣ የምንጠቀምበት ካፌ ሁሉ ስራ ፈጠራና ቢዝነስ መሆኑን ልብ በሉልኝ፡፡
‹‹ታዲያ ደግሞ ስራ ፈጠራ፣ ብር ማባዛት ብቻ አይደለም - ሰብዓዊ ነገርም አይጥፋ -
በስራ ፈጠራችን የህዝቡን ችግር መፍታት አንድ ነገር ሆኖ ማህበረሰባዊ ለውጥ አራማጆች የሚባሉም ሌሎች አሉ፡፡  ችግሮቻቸውን በለጋሾች ሳይሆን እዚሁ እኛው በኛው በቋሚነት እንድንፈታ የሚያስችሉ ጠንካራ ሰዎች፡፡    

ስትራይቭ ማሲይዋ፣ ዝምባብዌያዊው ቢሊየነር፣ ትንነት እንደተነጋገርነው መድረክ ላይ ቃለ ምልልስ እያደረገ ነበር፡፡ ጠያቂዋ የጠየቀችው ቀጣይ ጥያቄ፡-
ወጣቶች ሀብት እንጂ እዳ እንዳይሆኑ ባለድርሻ አካላት ምን ማድረገ ይጠበቅባቸዋል?
የዚች አህጉር ትልቁ ሀብት የህዝቧ አእምሮ እንጂ ሌላ ስላልሆነ እሱን የምንጠቀምበትን መንገድ መዘርጋት ግድ ይለናል፡፡ በአፍሪካ ደግሞ ከህዝቡ ስድሳ በመቶ ወጣት ስለሆነ ያንን ዕድል ተጠቅመን መለወጥ ይኖርብናል፡፡
በአሁኑ ሰዓት እኮ በሳምንት 500 አፍሪካውያን አውሮፓ ለመግባት ሲሞክሩ ሜዲትራኒያን ባሕር ገብተው ይቀራሉ፡፡ ስራ ፍለጋ አውሮፓ የሚሄዱትን እነዚህን ወገኖቻችንን ወደ ታንዛኒያ ነው ማምጣት ያለብን፡፡ ስራ አንፍጠርና ከሰሐራ አናስቀራቸው፡፡ ይህ አጣዳፊ ችግር እያለብን መተኛት አይታሰብም፡፡ ለዚያ ነው እኔ እዚሀ የመጣሁት፡፡ ይህን ስናደርግ እንደ አባቶቻችን እንደነ ጁሊየስ ኒሬሬ ታላቅ ታሪክ መስራት እንችላለን፡፡
ሌላ ነገር ደግሞ በዚህ ዘመን አያንዳንዱ ከናንተ የሚወጣ ነገር ይመዘገባል፡፡ አስኪ ፌስቡኩንና ጉግሉን እዩት - ወረቀት የያዘውን አይለቅም እንደሚባው፡፡ የምትናገሩትን ነገር መጠንቀቂያው አሁን ነው፡፡ ቀጣሪዎች እኮ ሲቀጥሯችሁ የማህበራዊ ሚዲያችሁን ንገሩን ይላሉ፡፡ ያኔ አሁን የማይሆን ነገር ከተናገራችሁ ችግር ይመጣል፡፡ የናንተ የዛሬ ቃል እንደ ንግድ ስማችሁ ነች ማለት ይቻላል፡፡
እኔ ጸሎተኛና መንፈሳዊ ሰው ነኝ፡፡ እስኪ እርስ በእርሳችን ትዕግስትና አክብሮት ይኑረን፡፡ በእጅጉ የተሳሰርን ነን፡፡ አንድ ሳልናገር የማላልፈው ነገር ግን አለ፡፡ ማህበራዊ ሚዲያችን ለምን የምንፈልገውን ሰው ብቻ ማሰባሰቢያ ሆነ?
መሰሎቻችንን ስናሰባስብ ነው የምንውለው፡፡ እስኪ የሚቻቻል አህጉር ይኑረን፡፡ ለጎረቤታችን ስፍራ ይኑረን፡፡

የተሳታፊዎች ጥያቄዎችና የስትራይቭ መልሶች (ተመልሰውም አልተመለሱም ይሆናል)
የፈጠርከውን ስራ ለማቆም ስታስብና ካጠገብህ የፈጠርከውን ስራ የሚብቁ ሲኖሩ ምን ታደርጋለህ?
የፈጠርከውን ስራ ትተህ ተጨማሪ ገቢ ፍለጋ ወደ ሌላ ለመቀየር ስታስብ አንዴት ነው በነባሩ ላይ የምታተኩረው?
ማህበራዊ ሚዲያንና ስራን እንዴተ ታመጣጥናለህ?
80 በመቶ ድርጅት እንደተጀመረ ይጠፋል፤ ይህን መጥፋት እንዴት እንከላከል?

ጓደኞቻችሁና ወዳጆቻችሁ የፈጠራችሁትን የሚያበረታቱ ይሁኑ፡፡ የስራ ፈጣሪዎች መረብ ይኑረን፡፡ ለዚህ ደግሞ ኢንተርኔት አለልን፡፡ እርስ በእርሰ ተደጋገፉ፡፡ ጎረቤታችሁ የሚሰራውን ማወቅ ጥሩ ነው፡፡ ምናልባት ዳንጎቴ የሚሰራን ከማወቅ በበለጠ አጠገባችሁ ያለው ሊጠቅማችሁ ይችላል፡፡
80 በመቶ የተፈጠሩ ስራዎች በተፈጠሩ ሰሞን ይጠፋሉ፤ ቢሆንም እናንተ መስጋት የለባችሁም፡፡
ያለብን ችግር ስራፈጠራ ሳይሆን ያለንን ድርጅት ምን ያህል እናሳድገው የሚለው ነው፡፡
ሕይወትንና ስራን እንዴት ታመጣጥነዋለህ ለሚለው እጅግ ጊዜ የሚየስፈልገውን ነገር እለያለሁ፡፡ ጊዜዬን እቆጣጠራለሁ፡፡ ሌላው የቀጠራችሁት ሰው የሚሰራውን ለዩለት፡፡ ስራዎቹን ቅድሚያ የሚገባውንና የማይገባውን ለዩ፡፡

ከሌላ ድርጅት ጋር ጥምረት ማድረግ የማይኖርብንና የሚኖርብን መሆኑን እንዴት እናውቃለን?
የአህጉሩን ትልልቁን ድርጅት የምትመሰርቱ ስለሆናችሁ ብቻችሁን አትሰሩትም፡፡ 90 በመቶ ውድቀትም ሆነ እድገትን ያመጣልና ግን በጥንቃቄ ይሁን፡፡ ከመግባታችሁ በፊት አጥኑ፡፡ ምን ዓይነት ክህሎት እንደሚያስፈልጋችሁ እወቁት፡፡
ሰራተኞቻችሁ ስራቸውን አነዲሰሩ ፍጹም ነጻነት ስጧቸው፡፡ የራሳችሁን ስርዓት ለድርጅቱ ንደፉ፤ በዚያም መሰረት ስሩ፡፡  የማያስፈልግበት ቦታ እየገባችሁ አታስቸግሩ፡፡ ባለሙያዎችን ከቀጠራችሁ በኋላ እምነት አትንፈጓቸው፡፡

ዝግጅቱ በኢንተርኔት በቀጥታ ይተላለፍ ስለነበር ከዚያም የመጡ ጥያቄዎች ነበሩ፡-
ከቻይኖች ጋር ስላለው ፉክክር ምን ትላለህ
እናሸንፋቸዋለን፡፡ እንድናሸንፋቸው ግን እንረዳቸው፡፡ እኔ ለአንድ ወር ቻይና ሄጄ ሳጠናቸው ነበር፡፡ የቻይናም የአሜሪካም አጋሮች አሉኝ፡፡ የእነዚህ ጥንካሬ ምንድነው ብሎ ማጥናት ያስፈልገናል፡፡ ዘ ፕሮፊት የተባለውን የቴሌቪዥን ፕሮግራም ገዝቼ በክዌሲ ቴሌቪዥን እያሰራጨሁ ነው፡፡ ስለስራፈጠራ የተሻለ ስለሚያስረዳንና እነሱን እንድናውቅ ስለሚያግዘን ነው፡፡ ሰዎች፣ ምርቶችና ሂደቶች የሚለውን ዝግጅት ብታዩት እንዴት ደስ ይለኛል መሰላችሁ፡፡ ሂደት የሚባለው አወቃቀራችንና የዘረጋነው ስርዓት ሲሆን የኛ ድርጅት ለምሳሌ በጥሩ ሁኔታ ስለተዋቀረ አንድ ሰራተኛ ሊሰርቅ ሲያስብ እንደርስበታለን፡፡

ቢዝነስና ህይወት እንዴት ይጣጣምልሃል?
የአጎቴ ልጅ ገንዘብ አበድረኝ ብሎ መጣብኝ ባለፈው፡፡ በየሚዲያው ሃብታም ነው ሲባል ሰምቶ ይሄ ሁሉ ድርጀት ስላለህ እባክህ ተቸገርልኝ አለኝ፡፡ እኔ ደግሞ ያ ገንዘብ የድርጅቱ እንጂ መች የኔ ነው አልኩት፡፡ ድርጅቱም እናንተም ህይወት ይኑራችሁ፡፡ በነገራችን ላይ የምኖረው እንግሊዝ ነው፡፡ ልጆቼም የክፍል ጓደኞቻቸው ሃብታም ነው ሲሉ ስለሚሰሙ ይጠይቁኛል፡፡ እኔ ግን እንደ አባት እንጂ እንደ ስራ አስኪያጅ ልጆቼንም ሆነ ባለቤቴን መቅረብ ስለማልፈልግ ድንበር አበጅለታለሁ፡፡

ቅን ነህ፤  ለሌላው ታስባለህ፡፡ በዚህ አህጉር ያለውን ማሳደድ እንዴ አለፍከው?
የአፍሪካ ምርት የአህጉሩን ፍጆታ ሸፈኖ ጥራት የሌለውን የውጪ ምርት መተካት የሚችለው እንዴት ነው?
ወጣቱ ሊሰማራበት በሚፈልገው የስራ ዘርፍ ዕውቀቱና ክህሎቱ ላይኖረው ይችላልና ምን ትመክረናለህ?
አፍሪካ የደኸየችው በእምነተ ሰበብ ነው ይባላል፡፡ እንተ ታዲያ አማኝ ሆነህ እንዴት ልትለወጥ ቻልክ ?
ከተሳታፊዎች የተጠየቀ ነበር፡፡

ገበያ ስለማጠያየቅ፣ መረጃ ስለማፈላልግና ሃሳብህን ለኢንቬስተር ስለማካፈል ስለጻፍኩት ጉዳይ የጠየቃችሁት ልከ ነው፡፡ ጥንቃቄ ብዙ ትርፍ ያመጣልናል፡፡ ባለፈወ ሰባት መቶ ሚሊየን ዶላር አስይዤ የላኳቸው ሰራተኞቼ በዓለም ታሪክ በግል ባለሀብት የመጀመሪያውን ታላቅ ቦንድ ሊገዙ ነበር አካሄዳቸው፡፡ ስንትና ስንት ሰው ጠይቀው ላለመግዛት ወስነው መጡ፡፡ እንዲህ ያለ ጥንቃቄና ንቃት ያሻል፡፡
ጥራቱ የወረደ ምርትን አስመልክቶ በተጠየቀው ላይ ሁሉም አካላት፣ መንግስት፣ መያዶች፣ ተጠቃሚዎችም ሆኑ ስራፈጣሪዎች የተሳተፉበት አሰራር መኖር ይኖርበታል፡፡ አካባቢያችንን የጠበቀ፣ ቀጣይነቱን ያረጋገጠ፣ ደህንነታችንን የጠበቀ የፈጆታ እቃዎች ስርጭት ሊነረን ይገባል፡፡ ግንዛቤው ማደግና ስርዓቱ መዘረጋት አለበት፡፡ ታማኝነት ትልቁ ሀብት ነው፡፡ እሱን ወደ ስርዓታችሁ ካስገባችሁ ….
እምነት ከስኬት ጋር ይያያዛል ወይ ብለን ከጠየቅን ማናቸውንም እምነት አከብራለሁ፡፡ ብዙ የተለያየ እምነት ካላቸው ሰዎች ጋር እሰራለሁ፡፡ አሁን በምናገርበት ርዕስ ግን ሁላችንም የየራሳችን አተያዮች አሉን፡፡
ስራ ፈጣሪዎች ብዙ ነገር መስራት የለባቸውም፡፡ አንዱን አድምታችሁ ብትሰሩት ጥሩ ነው ባይ ነኝ፡፡
ለወጣቱ አቅጣጫ እንድናሳየው እንጂ ገንዘብ እንድንሰጠው አያስፈልግም፡፡
100 000 ልጆችን እረዳለሁ፡፡ ከነዚህ ውስጥ 40 000ዎቹ ወላጅ አልባዎች ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ስራ ፈጣሪ ማህበራዊ ሃላፊነተም አንዳለበት አይዘንጋ፡፡
አፍሪካን በኢኮኖሚ ነጻ እናውጣት፡፡
https://www.facebook.com/strivemasiyiwa/

2017 ኦገስት 7, ሰኞ

The Rude Shepherd



Based on a true story told by Gebriye Zenebe

Writer: Mezemir Girma

The sheep are busy grazing, whereas the cattle are sleeping beside the river above the historic Engidwasha Cave. Two siblings are in charge of all these animals.

“Kasa, it is your turn to bring those sheep back here before they go to that farm. You know the owner will punish us today too,” said Kelem.

“Hey! I will hit you! You go bring them!” he said waving his stick.

“No! No! You deny? It is your turn. I will not go another time. I will bring them only now and you will go for two rounds. If not, I will tell Baba in the evening.”

“You tell him and tomorrow I will hit you,” he threatened her.

Kelem went murmuring and brought the sheep.

Kasa threatens his sister as such. Sometimes he punishes her. He has also a habit of abusing other people and running towards his parents or elder brothers for protection. At this particular moment, along the road from the side of the church comes a passerby.  

Kasa told his sister that he will insult the man. His sister warned him that the man would punish him. Kasa insists that he will insult the passerby. He could not listen to the advice of his sister. He even threatened to hit him by a sling.

The man approached. Seeing that he wore a lowlanders’ gabi Kasa shouted, “Lowlander wanderer! Lowlander robber! You dirty lowlander!” However, the man kept walking as if he didn’t hear what that boy said. Kasa kept insulting the man until the man went down the road and disappeared from sight. Kasa laughed happily over his small victory.

“He heard what I said. He kept quiet only because he is afraid. Lowlanders are cowards,” said Kasa to his sister who looked indifferent.

As he was bragging, a man emerged from the side the previous man went to. This man hid his hands towards his back. As he approached the children, it was difficult to know he was the previous man since he held the gabi he wore in his armpits.

“Hello children. How are you? Can you show me where Asrat’s home is?” asked this man. Kasa told him that Asrat is his father and their home is nearby. “But, you know, my parents went to a distant farm. You cannot find them now,” said Kasa.

“Ok, good! Are you his children? Come, greet me children,” said the man.  The man approached Kasa and immediately held his two hands together by his left hand. It was a stick that this man held in his hands. The man started to flog Kasa, who kept crying. None of Kasa’s family members were around to save him.

As soon as the man left, Kasa began to throw stones towards the man using a sling. He narrowly missed the man two, three times. The man tried to avoid the flying stones and started to run towards the boy. He caught him and punished him for the second time. He pinched him sending his hands under his shorts. He slapped him with his hard hands.

 His sister, Kelem, observes what happens to Kasa and learns that insulting people causes such punishments. After the man punished Kasa and told him he would punish him more if he hears he insults other people, the man went down the road. This time Kasa didn’t insult the man. He just murmured “I would tell my father if he were here.” This single incidence made Kasa a boy who respects young and old people alike.

Moral: Abusing people causes troubles.


Camel Narratives




I grew up in a highland. The animals I knew as a child include cows, oxen, sheep, goats, donkeys, horses and mules. I saw a picture of camels only in books. Some people told me what a real camel looked like. Even there is a story of a certain highlander who went to a lowland area and was confused about this animal. Then, he is quoted to say, “Some people do not know that.” Then, they would ask him if it were the camel and he responded affirmatively. In this wise way he learnt the name of that new creature. Welela, a beautiful woman I knew as a high school student related what she knew about camels. “After they told me camels weep when they discover that they are going to be slaughtered, I stopped eating camel meat altogether,” says this woman. Her cousin Mrs. Merima told me how camels could be aggressive and attack people. A few years ago I came to discover that its back legs fold twice – what a unique creature! It was during my visit to the Lalibela rock-hewn churches that I saw camels. Yordanos, a guy who went with me said that this animal looked like a dried tree when seen from afar. The most recent time I saw a camel is last year. It was in Adama, Nazareth, that I had a closer look at this beast. In the culture I was brought up in, we neither eat camel meat nor drink its milk.

መጽሐፍ ስናነብ መምረጥ አለብን?






የመጸሐፍ ነገር ከተነሳ በዓለማችን እስካሁን ስንት መጻሕፍት ለህትመት በቅተዋል የሚለውን ጉዳይ እንይ፡፡ ጉግል ወደ መቶ ሠላሳ ሚሊዮን የሚጠጉ መጻሕፍት ለሕትመት እንደበቁ ያስረዳናል፡፡ ይህ የሆነው አንድ ደራሲ በአንድ ወቅት ያወጣውን መጽሐፍ አንድ ብለን ቆጥረን እንጂ ያሳተማቸውን የመጽሐፍ ቅጂዎች ብዛት ቆጥረን አይደለም፡፡ ብዛቱ ያስደምማል - በዓመት ዐሥር ሺህ ገዳማ መጻሕፍት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ብቻ ይታተማሉ፡፡ ቁጥሩ ብዙ የተጋነነ እንዳይመስላችሁ - ግዕዝም በሕይወት ዘመኑ በዐሥር ሺዎች መጻሕፍት ታትመውበታል፡፡



‹‹ኩሎ አመክሩ ወዘሠናየ አፅንዑ›› ባይ ተከራካሪዎች በዕለተ እሁድ 16/11/2009 በደብረ ብረሃን ከተማ በተምሳሌት ኪነጥበባት የኪነማዕድ ዝግጅት ላይ ‹‹መጽሐፍ አንዴት ተደርጎ ይመረጣል?›› ሲሉ ሞግተዋል፡፡ ‹‹አንብበን አተረጓጎማችንን ማስተካከል እንጂ እንዴት ይህን አላነብም ይህን አነባለሁ ብለን ማዕቀብ እንጥላለን?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ‹‹መጥፎውን ካላነበብህ ጥሩውን ልታውቅ አትችልም፡፡ የተነሱት ሐሳቦች የማይመቹን ከሆነ መተው አንችልም ወይ?›› ብለው ሞግተዋል፡፡ ወንፊት እንደሚያጠለው ሁሉ ከተነበበ በኋላ የመምረጥ ችሎታ ጠቃሚነቱ ታይቷቸዋል፡፡ ባጠቃላይ ለነሱ መጽሐፉ ሳይሆን አወሳሰዳችንና አተገባበራችን ከግምት ውስጥ መግባት አለበት፡፡ ከመራጮች ወገን በተደጋጋሚ የተነሣው ደራሲ ማን ይመስላችኋል? ‹‹የሱን መጻሕፍት ካነበባችሁ ጉዳችሁ ፈላ! እንደሱ ዓይነቶቹን ችላ በሏቸው! ያለዚያ ወዮላችሁ፤ ሰማይ ይደፋባችኋል!›› ትባላላችሁ፡፡ ኦሾ ጉድህ! ሰውን ለማስፈራራትና ከዚህ መጽሐፍ ታቀቡ ለማለት አይደለም የኛ ክርክር መሆን ያለበት፡፡ ነገሩ ወዲህ ነው!



የንባባችን ዓላማ ምንድነው? ለመዝናናት፣ ለምርምር፣ ክህሎትን ለማዳበር፣ መረጃ ለማግኘት፣ አመለካከትን ለማነጽ፣ ለማጥናት? በዚህ ምክንያት ምርጫ ማድረግ ግድ ይለናል፡፡



በኛ አገር የህብረተሰቡ አንባቢ ያለመሆንና የብዙ መጻሕፍት ያለመዳረስ ችግር አለ፡፡ ስለዚህ የህብረተሰቡ አካላት ምናልባት ወደ ንባብ ከመጡና መጻሕፍትን ማግኘት ከቻሉ የየምርጫቸውን መጻሕፍት ማንበብ አለባቸው፡፡ በባለፈው የንባብ ፌስቲቫላችን በተሰጠ የዓይን እማኝነት ከጀርመኖች፣ ከጣሊያኖችና ከሌሎችም ህዝቦች ጋር ሲነጻጸሩ አንባቢዎች በተባሉት አሜሪካውያን ዘንድ እንኳን ሁለት ሦስተኛው ህዝብ በዓመት አንድ መጽሐፍም አያነብም ተብሏል፡፡ በጣም አንበቢው ሰው አነበበ ቢባል እንኳን አምስት ሺሀ ገደማ መጸሕፍትን በሕይወት ዘመኑ ሊያነብ ይችላል ብለው አስተያየት የሰጡ ጸሐፊ አሉ፡፡ ዳቢት፣ ንቃይ፣ ታናሽ፣ ታላቅ፣ ወርች፣ ሽንጥ፣ ሳልገኝ፣ ጎድን (ሳብራዳ)፣ ፍርምባ፣ ጭቅና፣ ኪርኪሳ፣ ፍሌቶ፣ ደንደስ፣ ሻኛ፣ ሹልዳ፣ ነብሮ እያለ የሥጋ ዓይነቶችን ሲቆጥርና ሲበላ ወይም ሲመኝ ለሚውል ሰው እንደ አብዛኛው አሜሪካዊ ንባብ የሕይወቱ አካል ስላልሆነ የምንነጋገረው ከተወሰነው የህብረተሰብ አንባቢ ልምድና ተግባር በመነሳት ይሆናል፡፡ የንባብ ልማድ ከልጅነታችን ስላልዳበረ ነው ንባባችን ችግር የገጠመው፡፡ ምናልባት ኦባሳንጆ እንደሚሉት መልሰን መማር ባይኖርብንም ቀለል ባሉ ንባቦች ራሳችንን ብናላምድ መልካም ነው፡፡ ባህላችን ጭራሹኑስ ማንበብን ያበረታታል ወይ? ብላችሁ ብትጠይቁ ማንበብና መጠየቅ የሚበረታታ አይመስለኝም፡፡ የሃይማኖት መጻሕፍትን እንኳን የሚያነበው አማኝ ስንት ነው? ከሚነበቡት ነገሮች ተደራሽነት ባሻገር የመጻሕፍት እገዳ፣ የአንባቢያን የቋንቋ ችግር ወዘተ. የየራሳቸው ተጽዕኖ እንዳላቸው በማስረገጥ ወደ ቀጣዩ ምክንያት እንሂድ፡፡



አንባቢያን የንባብ የምቾት ቀጠና አላቸው፡፡ ዘውግ ይመርጣሉ፡፡ ልቦለድ፣ ስነልቦና፣ የሕይወት ታሪክ፣ ግጥም፣ ፍልስፍና፣ ሙያዊ ነገር፣ ወዘተ. - ከአንዱ ይሆናል ፍላጎታቸው፡፡ በተያያዘ ወሬ ማሰባጠር ጥሩ እንደሆነ ለአንባቢያን ማስገንዘብ ይኖርብናል፡፡



በውይይታችን ላይ ጨርሶ አላነብም ላሉ ግን መልዕክት አለኝ፡፡ ታሪክን የማያነብ ታሪክን የመድገም ዕድል አለው፡፡ ከትናንት ካልተማርን ዛሬንና ነገን በትክክል ለመኖር እንቸገራለን፡፡ ‹‹እንዴት እናንብብ›› የሚል መጽሐፍም ስለወጣ ብታነቡት አይከፋም፡፡ ‹‹ምን ዓይነት ቃላት ቢይዝ ነው የሚያሳብደው›› ያልሽው ልጅ ንባብ ብዙ ጉልበት ስላለው አንብበሽ ድረሺበት፡፡ መቀመጥ መቻልም ማንበብን ለማዳበር ወሳኝ ነገር ነው፡፡ መጽሃፍ ሲወፍር ደግሞ ደስ ይበላችሁ እንጂ ለመቼ አልቆልኝ አትበሉ፡፡ ደራሲው ጉዳዩን በጥልቀት ዳሶታል ማለት ነው፡፡



አንብበን እንደ ወንፊት እናጣራ በሚለው ብዙም አልስማማም፡፡ የምናነበው ነገር ስብዕናችንን ስለሚቀርጽ የተገኘውን ማንበብ የለብንም፡፡ በተዘዋዋሪ ሳናውቀውም ቢሆን በጥሩም ሆነ በመጥፎ ተጽዕኖ ስለሚያሳድርብን መምረጥ ይኖርብናል፡፡



የምንመርጠው በባህልና በቤተሰብ በተቀረጽንበት ስብዕና መሰረት ሊሆን ይችላል፡፡ መሆን ያለበት የሚመስለኝ ግን እንዲህ ነው፡፡ ራሳችን የራሳችንን የነገ ህይወት መቅረጽ ግድ ይለናል፡፡ እንስሶች ናቸው ከአካባቢየቸው ጋር ተስማምተው የሚኖሩት፡፡ ሰዎች ግን አካባቢያችንን መቅረጽና መለወጥ አለብን፡፡ የህይወታችንንም መንገድ ራሳችን መጥረግ አለብን፡፡ ከዚያ የሕይወት መርሆ ጋር የሚሄድ ንባብ ማንበብ ይኖርብናል፡፡ ለመምረጥ የሚያስገድደን እርሱ ነው፡፡



ካላነበብን ጥሩውን እንዴት እናውቀዋለን ለሚለው ሀሳብ የተወሰኑ ምክሮች አሉኝ፡፡ የምናምናቸውን ሰዎች ምክር መስማት፣ ዳሰሳዎችን ማንበብ፣ ደራሲውንና ይዘቱን ማገናዘብ ወዘተ ጠቃሚ መንገዶች ናቸው፡፡



ስለንባብ ያሉ የተሳሳቱ አመለካከቶችም አሉ፡፡ ጫት እየቃሙ ማንበብ ጥሩ ነው የሚሉ አሉ፡፡ ስህተት ነው፡፡ የተወሰኑ አንባቢዎች የተሳሳተ ነገር ያደርጋሉና እኛም እነዚያን ነገሮች ማድረግ አለብን ማለት አይደለም፡፡ አንብቦ ጨርቅን መጣልም ጥሩ አይደለም፡፡

ለመሰናበት ያህል ማንበብ የመርሳት በሽታን ይከላከላል፤ ለመረጃ ቅርብ ያደርጋል፤ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡




በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...