2018 ዲሴምበር 1, ቅዳሜ

Learn Amharic in English

ኦባንግ ሜቶ በደብረ ብርሃን




በመዘምር ግርማ
19.3.2011

-የንግግሩ ሁኔታ የዶክተር ማርቲን ሉተር ኪንግን ይመስላል፡፡
- አማርኛው አድምጡኝ አድምጡኝ ይላል፡፡



ወደ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መጥተው ንግግር እንደሚያደርጉ በግሌ ከአንድ ሳምንት በፊት ሰምቼ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ለዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ በግልጽ ማስታወቂያ የተነገረው መምጫቸው ሲቃረብ ነበር፡፡ ረቡዕ ሕዳር 19. 2011 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ የዩኒቨርሲቲው
ማኅበረሰብ በሰዓቱ ወደ መመረቂያ አዳራሽ መትመም ጀመረ፡፡ ተማሪዎች ብቻ አይደሉም፡፡ የተለያየ ልምድና የትምህርት ዝግጅት ያላቸው ሰራተኞች፣ መምህራንና ተመራማሪዎች የፊተኛውን ረድፍ ይዘው በጉጉት ይጠብቁ ያዙ፡፡ እንግዳው ምን ሊናገሩ እንደሚችሉ ያወጋሉ፡፡
በዕለቱ የዩኒቨርሲቲው የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሰራተኛ የሆነው አቶ ጌታመሳይ አሳልፈው ተማሪዎችን በተመደበላቸው ቦታ ለማስቀመጥ ሲጥርና ይህም ተግባር ሲያስችግረው ያየው መምህር ጌታቸው ገብሩ ከአጠገቤ ተነስቶ ‹‹እኔስ ባስተባብር›› ብሎ ስርዓት አበጅቶ ተማሪዎችን፣ ሰራተኞችንና መምህራንን በየተመደበላቸው ስፍራ ማስቀመጥ ያዘ፡፡ ከዚህም የተማርኩት አንድ ሰው ቆሞ ከመመልከት ይመለከተኛል ብሎ መስራት እንዳለበት ነው፡፡ እኔ ያላደረኩትን ስላደረገ ጌታቸው በዚህ ይለያል ማለት ነው፡፡ ቆይተን እንደምናየው የአቶ ኦባንግም ንግግር ይህን ዓይነት የተግባር ስራ ጅማሮ መልዕክት የተላለፈበት ነበር፡፡
አንድ ሱፍ የለበሰና መነጽር ያደረገ ሰው በሩ ላይ በግርማ ሞገስ ሲታይ ማህበረሰቡ የጠበቀውን በማግኘቱ በአግራሞት ልቡ ወከክ አለ፡፡ እንደኔ ምልከታ ከወትሮው ሰላማዊ የመማር ማስተማር እንቅስቃሴ ውጪ ብዙም የተለየ ነገር በማታይበት ግቢ ንግግር የሚያደርግ እንግዳ መምጣቱ ለሁላችንም አዲስ ነገር ነው፡፡ እስከዛሬ የመጡ ቢኖሩም በአንድ ኬሌጅ የስብሰባ ዝግጅት ወይም ትምህርታዊ ጉባኤ ሊሳተፉ ስለሚሆን ሁላችንንም የሚያሳትፍ ላይሆን ይችላል፡፡
ኦባንግ ሜቶ ከእድሜያቸውም ሆነ ለሰው ካላቸው ቅርበት የተነሳ አንቱ ሊባሉ ሳይሆን እንደ ታላቅ ወንድም አንተ ቢባሉ ይሻላል ብዬ ስለማስብ አንባቢዬን ይቅርታ በመጠየቅ አንተ እያልኩ ጽሑፌን እቀጥላለሁ፡፡ የመድረክ ዝግጅቱ ተደረገ፡፡ በዚህም የቅድመ ዝግጅት ሂደት ድምጽ ማጉያው መስራቱን ለማረጋገጥ ባለሙያው አቶ እጀጌታው በተለያዩ ያገራችን ቋንቋዎች ‹‹ሙከራ 1፣ 2፣ 3›› እያሉ ተሳታፊውን አዝናንተዋል፡፡ ክስተቱ ለየቋንቋዎቹ ተናጋሪዎች ለእናንተም እውቅና እንሰጣለን ዓይነት መልዕክት የተላለፈበት ይመስለኛል፡፡ እዚህ ባይተዋር የለም ማለቱ መሰለኝ ባለሙያው፡፡
የእንግሊዝኛ ትምህርት ክፍል ኃላፊው ዶክተር ታደለ ፈንታው መድረክ መሪ ነበሩ፡፡ ስለ አብሮነት አንዳንድ ነገሮችን እየተናገሩና ስለኦባንግም መረጃ እየሰጡን መድረኩን በሚገባ አስተናብረዋል፡፡ ዝግጅቱ በማህበራዊ ሳይንስና ሰብዓዊነት ኮሌጅ አስተባባሪነት የተዘጋጀ መሆኑን እዚህ ጋ መጥቀስ ያስፈልጋል፡፡ ለወደፊቱም እንደዚህ ዓይነት ዝግጅት ቢካሄድ መልካም ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲውም ለዚህ ተግባራዊነት በዝግጅቱ ላይ ቃል ገብቷል፡፡
አዲስ የተመረጡት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ኃይለማርያም ብርቄ የመክፈቻ ንግግር አድርገው እንግዳውን ጋብዘዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲያችን ትንሿ ኢትዮጵያ እንደሆነችና የጋራ መግባባት ሊኖረን እንደሚገባ ያስገነዘቡት ፕሬዚዳንቱ በኦባንግ ንግግር መርካታቸውን መስክረዋል፡፡ የእንግዳው ማንነትና የህይወት ልምድም በዶክተር ታደለ ቀርቧል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ከመጀመሪያው ጀምረው እስከ ዝግጅቱ ፍጻሜ ድረስ በማወያየትና የአቶ ኦባንግን ንግግር በመከታተል አብረውን ስለቆዩ ማመስገን ይገባናል፡፡ ወደፊትም የእውነት የትምህርት ተቋም ይኖረን ዘንድ የሚያግዙ እንደዚህ ዓይነት ዝግጅቶችን በማቀድ፣ በመፍቀድና በማካሄድ ደብረ ብርሃንን እንደስሟ ብርሃን ያደርጓታል ብዬ አምናለሁ፡፡

አቶ ኦባንግ ሜቶ ንግግሩን የጀመረው በእንግሊዝኛ ነበር፡፡ የተወሰኑ ደቂቃዎችን በእንግሊዝኛ ካቀረበ በኋላ ስለቋንቋ አጠቃቀሙ አንዳንድ ነገር መናገር ጀመረ፡፡ ‹‹ለእኔ የሚቀናኝ እንግሊዝኛ ነው፡፡ በልጅነቴ እስከ ስድስተኛ ክፍል የተማርኩት አማርኛ እየጠፋብኝ ስለሆነ አሁን እንደገና እየተማርኩ ነው፡፡ ምናልባት ወደፊት ጎንደር ሄጄ አማርኛ መምህር ልሆን እችላለሁ›› ብሏል፡፡ ከዚህም በማስከተል ንግግሩን በአመዛኙ በአማርኛና አልፎ አልፎ አንዳንድ ጥቅሶችን በእንግሊዝኛ አቅርቧል፡፡
ውድ አንባቢዬ፣ ይህን ያህል ደጅ ካስጠናሁዎት ዘንዳ አሁን ኦባንግ በደብረ ብርሃን ምን ተናገረ ወደሚለው እንምጣ፡፡  

ማንነቱ
ኦባንግ እንደየሁኔታው የአኝዋክ ተወላጅ፣ ጥቁር፣ ውጪ የተማረ፣ ኢትዮጵያዊ ወዘተ ሊባል ይችላል፡፡ የሰብዓዊ መብት ታጋይ የሚለው ግን እኛም ዛሬ ስለሱ እንጽፍ ዘንድ ያስገደደን ስለሆነ በዚህ ብንጠራው ጥሩ ይመስላል፡፡ ኦባንግ የተለየ ግርማ ሞገስ አለው ሲል ከተናገረው ከዶክተር ታደለ ጋር የማይስማማ ሰው ያለ አይመስለኝም፡፡ እርጋታ፣ ቅንነት፣ ትህትና ወዘተ መልካም ቃላትን ሁሉ ብንደረድር ለኦባንግ ይገባዋል፡፡

አንድ ጣታችንን ሌላ ሰው ላይ ስንጠቁም ሦስቱ ራሳችን ላይ ይጠቁማሉ፡፡ ይህን ጥቅስ በሚገባው ቦታ ተጠቅሞበታል ኦባንግ፡፡ አሁን አገራችን ከገባችበት አጣብቂኝ ለመውጣት ብቸኛ ሙሴ አለ አይደለም የኦባንግ ንግግር፡፡ ሁላችንም ለጠፋው ጥፋት መድህን መሆን አለብን ይለናል፡፡ 
‹‹ከእናንተ እንጂ ዶክተር ዓቢይ አይደለም፡፡ ከእናንተ እንጂ ከዶክተር ኃይለማርያም አይደለም፡፡ ከእናንተ ነው ይህች አገር ብዙ የምትጠብቀው፡፡ ለውጥ ማምጣት የምንችለው 100 ሚሊዮኑ ሲተጋ ነው እንጂ በተወሰኑ ሰዎች አይደለም፡፡›› ይለናል መርፌ ቢወድቅ በሚሰማበት፣ ኮሽታ ባልነበረበት ትልቁ አዳራሽ የተገኘው ጥቁር ሰው!
 ‹‹ይህች ጥንታዊት ከተማ፣ ይህች የእምዬ ምኒልክ እትብት የተቀበረባት ስፍራ፣ ይህች ውብ ስፍራ፣ ደብረ ብርሃን እንደዚህ የሆነችው ደሃ ስለሆንን አይደለም - የአመራር ድህነት፣ የአስተዳደር ችግር፣ የቅንነት መጥፋት ስላጠቃን እንጂ›› ይለናል የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መስራች ኦባንግ፡፡
በአኝዋክ ባህል የመጀመሪያ ልጅ ኦባንግ እንደሚባል ሰምቼ ነበር፡፡ ኦባንግ እውነተኛ የኢትዮጵያ የበኩር ልጅ መሆን አስመስክሯል፡፡ የታሰሩ፣ የተገደሉ፣ የተሰደዱ፣ የተንገላቱ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ እንደሚያሳስበው ብቻ አይደለም የተረዳነው፡፡ አገር ውስጥና ውጪ ያሉትን ኢትዮጵያውያን ጉዳይ እየተከታተለ የሚታገዙበትንና ችግራቸው የሚፈታበትን መንገድ የሚቀይሰው ከአኝዋክ ወይም ከጋምቤላ ስለመጡ አይደለም፡፡ በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር አብረን በመኖራችን ስለሚያውቃቸው እንጂ፡፡ ያስተማረውን ህዝብ ለመካስ እንጂ!
በጃፓን፣ በማልታ፣ በኖርዌይ፣ በሜክሲኮ በበርካታ አገሮች በመዘዋወር ችግር ላይ ያሉና ቀን የከፋባቸውን ኢትዮጵያውያን አግኝቶ አጽናንቷል፡፡ ከጎናቸው እንዳለ አስመስክሯል፡፡ ከሃያ በላይ ሃገር ዞሮ ዜጎቻችንን የሚረዳው ህሊና ስላለው ነው፡፡ ከጎሳ ይልቅ ሰብዓዊነትን እናስቀድም በሚል መርህ የሚንቀሳቀሰውን የኦባንግን ጅማሮ ለማግኘት በበይነመረብ solidaritymovement.orgን መጠቀም ይችላሉ፡፡ ለተጀመረው ተስፋ ሰጪ ጉዞ ሁላችንም አለኝታነታችንን ማሳየት አለብን፡፡ 

ለብሔራዊ መከባበርና መተሳሰብ መንገዱ የተጠረገበት ስብሰባ ዋና ክፍል የኦባንግ ገለጻ ነው፡፡ ርዕሱም THE WAY FORWARD: CAN THE RIGHT CHANGE BE SUSTAINED IN ETHIOPIA? ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ለውጥ ማለትም በውጪ የነበሩ ኦባንግን ጨምሮ በአሸባሪነት የተፈረጁና አገራቸው እንዳይገቡ እገዳ የተጣለባቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋጮች መግባታቸው፣ እስረኞች መለቀቃቸው፣ ከኤርትራ ጋር የነበረው ፍጥጫ ወደ ሰላማዊ ጉርብትና መቀየሩ፣ ሚዲያዎች በነጻነት እንዲሰሩ መፈቀዱ፣ ለሃገራዊ መግባባት መንገድ እየተጠረገ መሆኑ፣ አሁን ያለው አጠቃላይ የለውጥ ተስፋና የዶክተር ዓቢይ ቡድን እያስመዘገበ ያው ውጤት የንግግሩ ማጠንጠኛ ነበር፡፡ እንደዚህ ተገናኝተን ስለ ሰብዓዊነታችን፣ ስለኢትዮጵያዊነታችንም ሆነ ስለችግሮቻችን መነጋገር ወንጀለኛና አሸባሪነት ተደርጎ እንደነበረና መሰብሰባችን በራሱ አሁን ያለው ለውጥ ውጤት እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ይህ ለውጥ ትክክለኛ እንሆነ፣ ልንንከባከበው እንደሚገባ፣ በተለይም ወጣቱ ዋነኛ የለውጡ ጠበቃ መሆን እንደሚኖርበት ኦባንግ አስገንዝቧል፡፡ ይህን ለውጥ ለማምጣትም ሆነ ኢትዮጵያን እንደሃገር ለማቆየት ለተጉና ሕይወታቸው ላለፈ ሁሉ የሕሊና ጸሎት በማድረግ ነበር ዝግጅቱ የተጀመረው፡፡

በበኩሌ ስለሩዋንዳ ዘር ማጥፋት ተርጉሜው የነበረውን መጽሐፍ አንድ ቅጂ ለእንግዳው አበርክቻለሁ፡፡ ለእርቅና ለአብሮነት ለሚያደረርገው ስራ የበኩሌን ለመወጣት ፍላጎትም አለኝ፡፡

ተሳታፊ የነበራችሁ ሰዎች ‹‹እስካሁን ያጠፋነውን በመቶ ዓመት አለንመልሰውም›› ሲል የተናገረውን እንዴት አያችሁት? ‹‹ሳናውቀው የጎሳ አስተሳሰብ ተጠቂ ነን›› ያለውንስ? የዘነጋኋቸውን ነጥቦችም እያነሳሳችሁ ብንወያይበት ጥሩ ነው እላለሁ፡፡

አንድ የኦባንግ አብሮ አደግ በቅርቡ አዲስ አበባ ሻይ ቡና ለማለት በተገኛኑበት ጊዜ ‹‹እኔ ጉራጌ ነኝ፡፡ ጉራጌ ነኝ፡ ጉራጌ፣ ጉራጌ…›› እያለ እንዳስቸገረውና ይህንም ዛሬ ያወቀው ይመስል እንደደጋገመበት ነግሮናል፡፡ የጎሰኝነትን አባዜና የገባንበትን አጣብቂኝ በብዙ ምሳሌዎች አስረድቶናል፡፡ ‹‹በምርጫችን አይደለም ከተፈጠርንበት ብሔር የተፈጠርነው›› ይለናል፡፡ 
ኦባንግ ውጪ ሲማር ከ3000 ተማሪ ብቸኛው ጥቁር እንደነበረ ነግሮናል፡፡ ‹‹ጥቁርነቴ ትዝ አይለኝም፡፡ ቆዳየን ልጆች በአግራሞት ቢነካኩም፡፡ በትምህርት ቤታችን በጣም ጥቁር ልጅ አለ እያሉ ለቤተሰብ ቢናገሩም፡፡›› ይለናል፡፡

ሕገመንግስቱ ስላለበት ችግርም ነጻ አውጪዎች ያወጡት እንደሆነና የኢትዮጵያ ሕዝብ ተሳትፎ እንዳልነበረበት አስገንዝቧል፡፡ ‹‹ነጻ አውጪዎቹ ከማነው ነጻ የሚወጡት - ከኢትዮጵያ ነው፡፡ እነሱ ኢትዮጵያን መሪ ለመሆን በቁና ይህን ሁሉ ጥፋት አመጡ፡፡›› ብሎናል፡፡

ከንግግሩ በኋላ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ ተሳታፊዎችን ከዝግጅቱ በኋላ አናግሬ በዝግጅቱ እንደረኩ ነግረውኛል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ምሳሌ የሚሆን ንግግር ነው፡፡ እንደሱ ዓይነት ኢትዮጵያዊ የለም፡፡ እንደዚያ የምናገር ምሁር ቢኖር አገራችን ትለወጥ ነበር፡፡›› ወዘተ በማለት ለንግግሩ ያላቸውን አድናቆት ነግረውኛል፡፡

ሰላማዊ የትምህርት ሂደት የሚካሄድበት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ስለ እርቅ፣ ሰላም፣ የፍትሕ መመለስ በሃገሪቱ እየተዘዋወረ ከዜጎች ጋር መነጋገርና ያለውን ሁኔታ በመረዳት ላይ ያለውን የሰብዓዊ መብት ታጋይ መጋበዙ ያስመሰግነዋል፡፡

ሰብዓዊነት ይለምልም!

2018 ኦክቶበር 30, ማክሰኞ

The Ethiopian Education Development Roadmap In the Eyes of NGOs



October 18 – 19, 2018
Mezemir Girma
Addis Ababa, Ethiopia

About the report:
This report has been compiled to inform the South African Institute for Distance Education (SAIDE) of the Roadmap. Since the institute is working in Ethiopia, it needs information about the roadmap.

About the compiler:
Mezemir Girma represents SAIDE in Ethiopia in their project African Storybook Initiative (ASb) which can be accessed on africanstorybook.org.

The Roadmap:
It is expected to go operational from 2018 - 2030 to reform “the education sector in accordance with the national vision and national development goals.”  The roadmap was prepared by a team of experts who used “desk review, benchmarking visits and field data on educational practices and implementation.”

Components:
This report focuses on pre-primary education since this is ASb’s main focus. However, one should note that the roadmap covers all aspects of education in the country.

The Procedure of the Workshop:
On the first day, Thursday, October 18, 2018, officials from the ministry of education (MoE) gave a PowerPoint presentation on the overall roadmap. The afternoon of this first day and the morning of the second day were allotted to group discussion. Two groups were formed and the participants had discussions on the contents of the roadmap. In the late morning of Friday, October 19, the two groups met and their chairs presented a summary of the discussion. A report was given to the ministry officials and the meeting was finalized. The discussants did not receive a copy of the roadmap file beforehand. Therefore, the discussion was mainly based on the PowerPoint presentation.

Pre-school Policy and Curriculum:
Non-governmental organizations’ (NGO) representatives inquired if the MoE has a clear policy on KG learning because it should have one. In the report only the New Early Child Care and Education Policy Framework (NECCEPF) (MoE, 2010) which is prepared by a group of ministries is mentioned. As to NGOs the community should be convinced on preschool.

O Class:
The issue of O class has been a point of contention. It is a major challenge as there are disparities and unclear policy guidelines among regions. Also called ‘school readiness program’ it is commendable as it saves children from straight grade one. As in the country pre-primary education has been left for the advantaged few in towns and cities, this scheme is an alternative. “What is the difference between O class and kindergarten?” asked participants.

Teacher Training:
The lack of adequate teacher training on pre-school has also been raised. The roadmap lacks clarity and credibility as there are less tangible plans with an inadequate budget. Participants asked, “Is there any preschool teachers’ training college in the country?”

Medium of Instruction:
The study found out that in pre-school 85 percent of the lesson is in mother tongue and 15 percent in Amharic in emerging regions used. These emerging regions use Amharic as a medium even if it is not the children’s mother tongue.  The roadmap recommends that the teachers should be trained in a language which is the children’s mother-tongue.

Kindergarten Textbooks:
Different organizations, private kindergartens, community schools and others are using their own textbooks. There should be a strict guideline on this.

Age Six:
The NGOs commented, “The suggested grade one starting age of six should be revised or justified as the kids do not cope-up with the lesson. What is your justification?” It was at seven years of age that children enroll in elementary schools. The suggested six years of age is debatable.

School Distance:
Since the farmers need their children nearby to keep their houses or animals, schools should be built at walking distance from home. As 85 percent of the schools in the country are in the rural areas, the roadmap should consider them. 

The Near Future:
The ministry aspires to involve all stakeholders in discussions and improve the document. Some aspects of the roadmap seem to be implemented at this time too.

Conclusion:
The African Storybook Initiative (ASb) recommends the application of well-researched reforms in the education sector. The fact that the reform goes in line with national and international development and educational goals is commendable. We hope that the gaps and shortcomings are addressed.

2018 ኦክቶበር 25, ሐሙስ

በትምህርት ጉዳይ

ሰሞኑን በትምህርት ጉዳይ አንዲት አነስተኛ ጽሑፍ እየጻፍኩ የተለያዩ ሰዎችን አወያይቼ ነበር፡፡ እስካሁን የማላውቀውና አሁን የሰማሁት መረጃ አለ፡፡ ይኸውም በሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ የነበሩት እስከ 12ኛ ክፍል የሚያስተምሩ ትምህርት ቤቶች ተዘግተው ሦስት ብቻ እንዲቀሩ መደረጉን ነው፡፡ ምክንያቱም በአዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ መሰረት የመሰናዶ (ከ11ኛ -12ኛ) ትምህርት እንዲሰጡ የተፈቀደላቸው ሦስቱ ብቻ ሲሆኑ ሌሎቹ እስከ አስረኛ ብቻ እንዲያስተምሩ ተደርጓል፡፡ በዚህም ውሳኔ መሰረት ጥሩ ውጤት ኖሯቸው ደብረብርሃን፣ ሞላሌ ወይም ደብረሲና ሄደው መማር ያልቻሉ ትምህርታቸውን እንዲያቋርጡ፣ ግብርና ኮሌጅ ወይንም ቴክኒክ እንዲገቡ ተደርገዋል ማለት ነው፡፡
የዚህን ችግር ስፋትና ጥልቀት እንገነዘብ ዘንድ በወቅቱ የውሳኔው ሰለባ የሆናችሁ ጻፉልን፡፡
ውሳኔው በሁሉም ክልሎች ብቻ የተደረገ ነበር ወይ?
እስከ 12ኛ የሚያስተምረውን ትምህርት ቤት ለአራት አመታት ዘግተው በ1997 ምርጫ ማግስት ለምን ከፈቱት? ውሳኔው የፖለቲካ እንጂ የትምህርት ባለሙያ ላይሆን ይችላል፡፡

የዓመት ግብራችን እነሆ።


የፍኖተ-ካርታ ውይይት በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ሲሆን፤ አንዳንድ ነጥቦች በተወያዮች እየተነሱ ነው፡፡ ስያሜውም ጥያቄ ውስጥ ገብቶላችኋል፡፡ የፖሊሲ ለውጥ አይመስልም፤ የአፈጻጸም የሚለው ላይ አትኩሮት ተደርጓል፡፡ ስለዚህ ፖሊሲው ችግር አልነበረበትም ማለት ነወይ?
ቋንቋ ላይ ያለኝን ምልከታ በመጠኑ ላስቃኛችሁ።
1. ቋንቋ የተባለው ላይ ልጆች አራት ቋንቋ እንዲማሩ የሚያደርግ አሰራር እየተዘረጋ ሲሆን፤ ትኩረታችን የቋንቋ ፉክክር ላይ ይመስላል፡፡ አማርኛ ብሔራዊ ቋንቋ እንዳይሆን ላለፉት 27 ዓመታት የተሰራው ስራ ላይ ተጨማሪ ነገር እየተሰራ ነው፡፡ የኔን ቋንቋ ካልተማርክልኝ ያንተን አልማርም ነው እንዴ ነገሩ? አማርኛ በታሪክ አጋጣሚ ብሔራዊ ቋንቋ ነው፡፡ ሁለት በተለያዩ ቋንቋዎች አፋቸውን የፈቱ ኢትዮጵያውያን ሲገናኙ የሚነጋገሩት በአማርኛ ነው፡፡ ትምህርትም በዚሁ ቋንቋ የሆነው ለዚያው ነበር፡፡ አሁን የአማርኛ ክፍለጊዜ መቀለጃ ሆኗል፡፡ ትምህርቱን በአግባቡ እንደማይወስዱ የሚያስታውቀው በአማርኛ ሰላምታ እንኳን የማይችሉ ልጆች ዩኒቨርሲቲ ሲደርሱ ነው፡፡ በአፍ መፍቻቸው የተማሩት ነገር ጥሩ ሆኖ ሳለ አሁን እነሱም የማይማሩትን የአማርኛ ክፍለጊዜ ታሳቢ አድርጎ የአማርኛ ተናጋሪውም የነሱን ቋንቋ እንዲማር የሚል አሰራር ሊዘረጋ ይመስላል፡፡
2. ከዚህ በፊት ብሔራዊ መግባባት መቅደም አለበት፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያውያን እርስ በርሳችን በጎሳ እየተለያየን እየተጠቃቃን መሆኑ ለማናችንም ምስጢር አይደለም፡፡ በዚህ አካሄድ የሚመረጡትን ቋንቋዎች (ለምሳሌ ትግርኛንና ኦሮምኛን) ለማስተማር ወደተለያዩ የሃገራችን ክፍል የሚሄደው መምህር ምን በወጣው ይንገላታል፣ ይደበደባል ባስ ሲልም ይገደላል! ቋንቋዎቹ እንደሚያስፈልጉን ጥርጥር የሌለው ቢሆንም ቅድሚያ መግባባቱ ይቅደም፡፡ ሰው መሆናችን ይቅደም፡፡
3. አሁን የኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች የግዛት ማስፋፋት ዘመቻ ላይ ባሉበት ወቅት ቋንቋቸውን ተምረን ማንነታችንን ብናጣስ? ከድሮውም አማርኛ የሚባል አልነበረም አይባል ይሆን? ማረጋገጫውም ይሄው እናንተ ቋንቋችንን ትችላላችሁ፡፡ ከፈለጋችሁ አገራችንን ለቃችሁ ውጡ፤ ያለዚያ ባህላችንንም ቋንቋችንንም አክብራችሁና ተከትላችሁ ኑሩ የሚል ጣጣ ቢመጣስ?
4. የውጪ ቋንቋ የተባለው ላይ አረብኛና ኪስዋህሊ ቢካተቱበት ጥሩ ነው፡፡ አረብኛ ልጆቻችን ትምህርት ሲጨርሱ ወደ አረብ አገር ስለሚሄዱ ሲሆን ኪስዋህሊ ደግሞ የአፍሪካን አካባቢያዊ ትስስር አስመልክቶ ነው፡፡ አሁን ደቡብ አፍሪካ የደረሰ ቋንቋ ነው፡፡
ዝርዝሩ ብዙ ነው፡፡ የዚህ የፍኖተ-ካርታ ጥናት በጠ.ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ዘመን የጀመረ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡
ምግቦቹ የተለጠፉት ባለፉት ዓመታት ተችቼው የነበረውን አራተኛውን የከፍተኛ ትምህርት ዓላማ አስመልክቶ ነው። መማር ማስተማር፣ ጥናትና ምርምር፣ ማህበረሰብ አገልግሎት በማለው ላይ ደግሶ ማብላት መጨመሩን አብስሬ ነበር።
ተጨማሪ ጽሑፍ ለማግኘት
mezemirethiopia.blogspot.com

ሰከን ካሉ ሰዎች አማራጮች መቅረብ ይኖርባቸዋል

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መግቢያ ወቅት መቃረቡን አስመልክቶ በጸጥታ ስጋት ምክንያት ተማሪዎች ወደ ምድብ ቦታቸው ላለመሄድ እያንገራሩ ነው። ከዚህ ያልተናነሰ ስጋትም አለ። ይኸውም የዩኒቨርስቲ መምህራንም ወደ ትውልድ አካባቢዎቻቸው በዝውውር እየፈለሱ ነው። ይህ ትልቅ ሥጋት ይመስለኛል። ለሚፈናቀሉ ዋስትና ሰጥቶ ተረጋግተው እንዲቀመጡ ማድረግ ያስፈልጋል። ቢያንስ ህብረተሰቡ አለኝታነቱን የሚያረጋግጥበት መንገድ ይቀየስ። የእድር፣ የኃይማኖት፣ የተቋማት ወዘተ መሪዎች "ችግር ቢመጣም ዋስትና እንሰጣችኋለን፤ ልጆቻችን አይነኳችሁም" ብለው መምህራኑን ሰብስበው መለመን አለባቸው። ይህን ማድረግ ካልተቻለ ወይም ዓይነተኛ መፍትሔ ካልተፈለገ ሁሉም ወደ ትውልድ ቀዬው ሲሰበሰብ የባሰ አደጋ ያመጣል። ሠው በሃገሩ ተዘዋውሮ መስራትና መኖር ይሳነዋል። ሰከን ካሉ ሰዎች አማራጮች መቅረብ ይኖርባቸዋል።

አገር በቀል የሌብነት እና ዝርፊያ ዘዴዎችስ?

Inside the mind of a thief (የሌባው አስተሳሰብ)
በሚለው ዝግጅት ይህ ሌባ ምክር ይለግሳል። ለረጅም ጊዜ ሳይያዝ ሲሰርቅ የኖረ ሲሆን አሁን ፖሊስ እጅ ላይ ወድቋል። ከሃያ እስከ ሠላሳ ዓመት እስርም ይጠብቀዋል ተብሏል። የሚጠቀማቸው የስርቆት ዘዴዎች የሚከተሉትን ከግምት ውስጥ ያስገባሉ፦
ሀ. የውሾችን መኖር አለመኖር
ለ. የአላርምን ሁኔታ (ዋየርለስ ነው?)
ሐ. ቀን ወይም ማታ
መ. በፊት ለፊት ወይስ በጓሮ
ሠ. ከደጅ የተቀመጠ ፖስታና መልዕክት ወይም ያደገ ሳር ካለ ሩቅ አገር ሄደዋል ማለት ነው
ረ. መብራት ካበሩ (የውጪውን ወይም የውስጡን)
ሰ. ቀድሞ የተቀረጸ ድምጽ ከለቀቁ (የውሻ ወይም የራሳቸውን)
ሸ. ጎረቤት እዩልን ካሉ
ወዘተ
አሁን የዚህ መረጃ አስፈላጊነት ወዲህ ነው። በየአካባቢው ሌቦች፣ ዘራፊዎች እና ወንጀለኞች እየተበራከቱ ስለሆነ ለቅድመ ጥንቃቄ ይረዳ ዘንድ የማጥቂያ ዘዴዎቻቸውን እንነጋገር። እንዴት እንከላከል? እርስዎ ምን ዓይነት ዘዴ ሠሙ?
የምትነግሩኝን አጠናቅሬ ለሁላችንም ደህንነት ስል እጽፋለሁ። መልካም ቀን!

2018 ኦክቶበር 1, ሰኞ

My Memories: A Story of the Visit I made After 14 Years - A developing story


In an eventful sunny Sunday in September 2018, I showed up at an event at a certain place. Where? Just a place very familiar to me. None other than the school where I spent four years! The event was a discussion session to strengthen an amateur art club set up by students of the school. This club is just two years old and they are making paramount undertakings in promoting art in town. Named Debre Tibeb, literally meaning ‘A Mountain of Art’, the club has satisfied the founder, an Amharic teacher at the school, and all art lover teachers in town. Let me just take you to this main issue of my today’s scribbling.

Do you just aspire to read what I am going to write about my observation of the school now? No, I think you prefer to know what I remember of my days at the school.  Lived experiences would attract you more, won’t they?

It was in September 2000 that I came from my home village to Debre Birhan town, 92 kilometers or just four hours’ drive from home. The coming attracts you more than the arrival. There were just trucks that transported goods and people to and from Sasit, my place that has a place in my heart as I spent my formative age there. The trucks, owned by a local fortune-teller, who has passed away a few years ago, were our sole means of transportation. The drivers had to play hide and seek with road traffic controllers that they transported us at nights. It was not my first ever drive to Debre Birhan town then. I had paid a visit to my uncles studying in town a year back.

A few days before coming to Debre Birhan, all my grade eight classmates  and I went to Debre Sina on foot. It was 42 Kilometres which we walked at night. Our purpose? To fetch our grade eight national exam certificate. It was direct from there that we headed to Debre Birhan where we stayed for long begging for enrollment. The reason? The director said that we belonged to Debre Sina School than Debre Birhan. We explained to the authorities at the zonal administration and the school that there were no cars to transport us and our provision to Debre Sina town. The school in Debre Birhan, Hailemariam Mamo Senior Secondary School, even if it were found farther, was accessible by car from our place. Thanks to the fortune-teller who bought four cars to transport people and goods.

After a long time of begging and compliant we were allowed to enroll at the school except for Hailu Hailemariam and Tensay Weldehna, who were rejected. Hailu went to Debre Sina. Tensay left learning for good and headed back home to practice agriculture. If I met him by a sheer coincidence, I would ask him whose life brought satisfaction – mine or his.

We were 25 at grade eight. Among us a few completed grade 12. To name a few, Gizaw Hulumyikir, Wolde Girma, Hailu Negese, Gebriye Zenebe, Workagegnehu Zewdu and me. Grade nine would start. A totally new school system started. We were educated in the new educational and training policy that was being newly experimented on our seniors and us. Unlike the previous regime and policy, education was made in our mother-tounge, Amharic, throughout elementary school. Starting with grade nine, all subjects except Amharic were delivered in English. Some had to wonder how this language worked. Even if we took English as of grade one, many found it hard to understand or hold conversations in it.

Let me come to my story, sir/madam. I was a small boy of fourteen. How come? There was no kindergarten then. My father who liked to take ‘his children’ to school at a young age took me to the school at Sasit when I was only six. The school was nearby that I went and came back. Until grade four I almost knew nothing. This hugely affected my learning. How did my father take me to school at that tender age? He did that without taking my older half-brother to school. An evil deed! I paid the price and by having to shoulder education bigger than my level. I was fourteen at grade nine. Small and emaciated for that level that I was a laughing matter. And also a victim of bully that I had to experience bad encounters almost every day.

How did I live? I had two uncles who were also studying at the same school. We shared a room. I am thankful for them. How did we get food? The tracks would transport us provisions from home. This was for free and also I am thankful for them.

Grade nine passed as it may. ‘Bemote!’ I would die if I pass this grade without telling you some memories. There would emerge a group or pair of foreigners from any conspicuous corner and I would run to talk to them. This is a mentality that was in my mind then until I later left talking to strangers. Even those who were in upper grades than me called me to talk to the visitors. I tried and tried.

Memories of Grade ten follow. Under the new curriculum, we sat for national exam at grade ten. Some of us went to grade eleven, which led to university. Others headed to agricultural, teachers’ and technical colleges. There were also those who failed and had to stay at home and sit for the exam next year. Grade eleven and twelve were said to replace university first year that there was frustration and confusion among us. All this passed and we completed grade twelve.

While grade nine and ten was half day, grade eleven and twelve were full day. At this level, there were students from the entire North Shewa Zone, which consists of millions of people. I learned the reason for this last week while I was interviewing someone for an article on financing higher education. The schools these students came from were prohibited not to deliver lessons at grades eleven and twelve. People say that the government wanted to ‘avenge’ the Shewan elites who they say were their enemies they overthrew. For this dominant ignorance, thousands of students had to either come to the three centers found in Debre Birhan, Molale or Debre Sina or leave school altogether whether they had the pass mark or not. This happens at their tender age of sixteen.

Our School’s Current Condition
I was at the school half an hour before the meeting. At 2:00 pm I appeared at the majestic gate of Haile Mariam Mamo Preparatory School, as they call it at this time. Since it was Sunday, there were no students at the place. Only two young guards chatted there. Unlike the ones at our time, these were young and friendly. The ones at our time had a fierce look that intimidated any wrongdoer and an innocent one alike. They let me in. It was my fear of the guards that kept me away from my school for such a long while.

The administrative offices are to the left of the gate, the library to the right. At both wings of the entry, there stood the old statues of patriots, one of which may be of the hero the school is named after.  When we were students there were two lines of old tid tree leading to the morning meeting place. Now they are decimated. On my way to the meeting place I saw the former workshop rooms. Metalwork, woodwork etc workshops are left after technic schools were opened instead. The place where the national anthem is hoisted is the center of the school. I sat there. What came across my mind follows in the next paragraph.

 I remembered my classmates with all their deeds, features and bravado. The guys who came together from the farthest and remotest of places and accomplished goals unthinkable. How they kept victories in the battles of poverty and chills. This town that is famous for the chills is where the brave young hearts of Shewa were tried.

I reminisced of the exceptional teachers we had. A young teacher Berhe taught chemistry. How he was friendly is still lingering in my eyes. Later he won DV lottery and headed to the one and the only – the USA. Teacher Guesh, Zinabu, Talefe and a female teacher were also from chemistry. Many I remembered.

The incidences are also unforgettable. The hide and seek the guards played with boys who came jumping the school walls is worth mentioning. The big gourd threw rocks at boys jumping walls. The morning advices given by the director or his deputy were filled with narratives about Haile Mariam Mamo’s patriotic deeds. We were taught to emulate him. If you went astray, you would be reprimanded.

As I was alone at that spot, I felt really touched by the memory itself. What happened to those guys who had memories with me? No one can possibly tell about most of them. If they had a chance to meet on that day at that place, I think they would not be able to talk among themselves for a while. They would listen to themselves and calculate what they lost and profited from life after their school years.

Some of the students and teachers I knew died. I had to remember them and their deeds. Some are living abroad and most of the others in the different parts of Ethiopia.
After this long time of thinking, I resumed my visit. There were the 25 water barrels hanging on an old wooden structure. They were from the Italian times in the 1930s. Two new huge water containers have also been set in place. The graceful school has buildings that were built by Italians who occupied the country. The hall’s exterior and interior is still a work of beauty. There are also classrooms that are remnants of the old days.

Behind the school playground where we have fading memories, a new two storey building is under construction. I appreciate the school’s endeavors. All in all, the school is getting older and older. An idea struck my mind and I thought it better to renovate the old Italian buildings that are also treasures that remind us of the occupation and its history.

The three emperors:
Before I depart I should tell you that the pictures of the three Ethiopian emperors are drawn in the school. This happened when I was in grade 10. The pictures are still there and I should thank the people behind the idea because reconciling the historical narratives behind Emperors Minelik, Tewodrs and Yohannes is a great idea. Reconciliation comes this way!


2018 ሴፕቴምበር 30, እሑድ

የእንስሳት ሕክምና ወግ



አሰናጅ - መዘምር ግርማ
መስከረም 17፣ 2011፣ በመስቀል ዕለት ማለዳ በናታን ሆቴል፣ ደብረ ብርሃን፣ አንድ እንግዳ አገኘሁ፡፡ እንግዳው ዶክተር ዮሐንስ ሙሉነህ ይባላል፡፡ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ረዳት ፕሮፌሰር ነው፡፡ ለረጅም ጊዜ ለቃለመጠይቅ ስመኘው ነበርና ዕድሉን ተጠቀምኩበት፡፡ ወዲያውኑ ባለ ሃምሳ ሉክ ደብተርና እስኪርቢቶ ገዝቼ ጥያቄዬን ጀመርኩ፡፡ አጠያየቄም እንደ የሸዋ ፀሐይ ጋዜጣ ሪፖርተርነት ነው፡፡ በቆይታችን ያወጋነውን እንደሚከተለው እንድታነቡ እጋብዛችኋለሁ፡፡

የሸዋ ፀሐይ፡ የት ተማርክ?
ዶክተር ዮሐንስ፡ አርበኞች ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ ዩኒቨርሲቲስ?
ዶክተር ዮሐንስ: አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረዘይት፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ ስለዩኒቨርሲቲው እስኪ ንገረኝ፡፡
ዶክተር ዮሐንስ፡ ነባርና ለረጅም ዓመታት በብቸኝነት በእንስሳት ጤና ዘርፍ ያስመረቀ ዩኒቨርሲቲ ነው፡፡ ሌሎቹ ዩኒቨርስቲዎች ከ2000 ዓ.ም በኋላ ነው ማስመረቅ የጀመሩት፡፡ ትምህርቱን የሚያጠናክሩ ልምምዶች፣ ስልጠናዎችና ጉብኝቶችን የምንወስደው እዚያው ደብረዘይት፣ አዲስ አበባ ዙሪያና እንደየአስፈላጊነቱ በሌሎችም የሃገሪቱ ክፍሎች ነው፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ ለምሳሌ የት ሄዳችኋል?
ዶክተር ዮሐንስ፡ ብዙ ቦታ፡፡ ለምሳሌ ስለ ገንዲ በሽታ ምልከታ ለማድረግ ወደ ጊቤ በረሀ ሄደን ነበር፡፡ ምክንያቱም በሽታው በአካባቢው የተለመደ ስለሆነ ነው፡፡ ደብረ ብርሃንም የበግ እርባታውን ለማየት መጥተን ነበር፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ የመጨረሻ ዓመት ልምምድ የት ተመደብክ?
ዶክተር ዮሐንስ፡ ኤክስተርንሽፕ የተመደብኩት እዚያው ደብረዘይት ሲሆን፤ የሰራሁትም የጋማ ከብቶች ላይ ነው፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ ወደ ሥራው ዓለም እንምጣ፡፡
ዶክተር ዮሐንስ፡ አላጌ TVET ኮሌጅ ነው ስራ የጀመርኩት፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ ሕጻናት አምባ የነበረው?
ዶክተር ዮሐንስ፡ አዎ፡፡ በሻላና አቢጃታ ሐይቆች አካባቢ ያለ ከመላ ሐገሪቱ ተማሪዎችን የሚቀበልና በግብርና ሚኒስቴር ስር የሚተዳደር ነው፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ የማስተርስ መመረቂያህን በምን ዙሪያ ሰራህ?
ዶክተር ዮሐንስ፡ በወተት ላሞች በሽታ ላይ ነው፡፡ Mastitis የወተት ላሞችን የሚያጠቃ በሽታ ሲሆን የወተት ምርትን በመቀነስ ትልቅ የኢኮኖሚ ተጽዕኖ የሚያሳድር ነው፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ ወደ ደብረ ብርሃን መቼ መጣህ?
ዶክተር ዮሐንስ፡ ከሁለተኛ ዲግሪ በኋላ አላጌ ለአንድ ዓመት አገልግዬ ነው ወደ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በ2006 ክረምት ላይ የመጣሁት፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ እዚህ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በናንተ የትምህርት ዘርፍ ያለው እንቅስቃሴ ምን ይመስላል?
ዶክተር ዮሐንስ፡ እዚህ የምናስተምረው የእንስሳት ሳይንስ ተማሪዎችን ሲሆን እኛ የጤና ኮርሶችን እንሸፍናለን፡፡ እንስሳት ጤና ላይ ብንሰራ ለአካባቢው ጥቅም ይኖረዋል፡፡ የእንስሳት ጤና ትምህርት ክፍል ቢከፈት በመቶ ሃምሳና ሁለት መቶ ኪሎሜትር ርቀት አካባቢውን ማገልገል ይቻላል፡፡ እስከ አፋርም ድረስ መሄድ ይቻላል፡፡ ለተማሪዎች አንዳንድ የተግባር ምልከታዎችን ወደ ምርምር ማዕከላት በመሄድ እናሳያቸዋለን ፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ አካባቢው ምን ያህል አቅም አለው በእንስሳት ሐብት?
ዶክተር ዮሐንስ፡ እንደሚታወቀው ዞኑ በእንስሳት ሐብት የተሻለ አቅም አለው፡፡ የውጭ ዝርያ ያላቸው  የወተት ላሞች፤ የመንዝ በግ ዝርያ፤ በደጋው አካባቢ በብዛት የጋማ ከብቶች (ፈረስና በቅሎ) ሲገኙ በዞኑ የቆላማ አካባቢዎች ደግሞ ከዳልጋ ከብትና በግ በተጨማሪ ከፍተኛ የሆነ የፍየል እና የግመል ሐብት አለ፡፡ ከዚህ አንጻር የደብረ ብርሀን ዩኒቨርስቲ የደጋ ከፍታ ግብርናን  ቀዳሚ ሴንተር ኦፍ ኤክሰለንስ አድርጎ መምረጡ የዞኑን የእንስሳት ሐብት ለመጠቀም የተሻለ ስራ ለመስራት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ በሃገራችን በእናንተ ሙያ ዘርፍ ምን ያህል ተሰርቶበታል?
ዶክተር ዮሐንስ፡ ካለን የእንስሳት ቁጥር አንጻር በቂ ስራ ተሰርቷል ብዬ አላምንም፡፡ ነገር ግን የተወሰኑ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ ለምሳሌ የደስታ በሽታን (Rinder pest) ከኢትዮጵያ ከማጥፋት አንጻር ስኬት ተገኝቷል፡፡ በአጠቃላይ በሽታዎችን ከመከላከልና የህክምና ስራዎችን ከመስራት በተጨማሪ በዚህ ዘመንም በተመረጡ በሽታዎች ላይ (pest des petitis ruminants/ PPR) የማጥፋት ስራ እየተሰራ ነው፡፡ በዚህ ስራ ላይ የሃገር በቀል እና የውጪ ድርጅቶች በዘርፉ በጋራ እሰሩ ይገኛሉ፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ ጥሬ ስጋ መብላትን አስመልክቶ የምትለን ነገር ካለ፡፡
ዶክተር ዮሐንስ፡ እንደ ባለሙያ ጥሩ አይደለም ባይ ነኝ፡፡ የበሽታ ጉዳይ ስላለ አይበረታታም፡፡ እንደ ባህል የተለመደ ሊሆን ይችላል፡፡ በመሰረቱ ንጹህ ስጋ ከሆነ መብላቱ ችግር ላያመጣ ይችላል፡፡ ነገር ግን እርድ በብዛት በየቤቱ ስለሚካሄድ ንጽሕናውን ማረጋገጥ ስለማይቻል አስቸጋሪ ነው፡፡  
የሸዋ ፀሐይ፡ የቲቢ በሽታ ጉዳይ ከወተት ጋር እየተያያዘ የሚነሳ ሆኗል፡፡ የችግሩ መጠን እንዴት ነው?
ዶክተር ዮሐንስ፡ አስቸጋሪ በሽታ ነው፡፡ ከሰው ወደ እንስሳ ከእንስሳ ወደ ሰው የሚተላለፍ ነው፡፡  በአብዛኛው በትንፋሽ የሚተላለፍ በሽታ ነው፡፡ በወተትም ይተላለፋል፡፡ ወተቱን በተገቢው መንገድ ማፍላትና መጠቀም አንዱ የመከላከያ መንገድ ነው፡፡ በ72 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ለ15 ደቂቃ ቢፈላ ወይም ፓስቸራይዝድ ቢደረግ ሊጠፋ ይችላል፡፡ እንስሳቱን ማስመርመር ያስፈልጋል፡፡ በሽታው ካለባቸው መዳን ስለማይችሉ ማስወገድ ያስፈልጋል፡፡ ከእንስሳ ጋር የሚኖረን ቀረቤታ በአብዛኛዉ ጥንቃቄ ያለበት መሆን ይኖርበታል፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ የውርጃ በሽታም ተመሳሳይ ተፈጥሮ አለው ይባላል፡፡
ዶክተር ዮሐንስ፡ አዎ፡፡ የውርጃ በሽታ ወይም ብሩሴሎሲስ እንደ ሳንባ ነቀርሳ ሁሉ ሰውንም እንስሳትንም ያጠቃል፡፡ በወተትና በንክኪ ወደ ሰው ይተላለፋል፡፡ ሰውንም ሆነ እንስሳትን መሃን ያደርጋል፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ እንስሳትንና ሰውን በአንድነት የሚያጠቁ በሽታዎች መጠን እስከምን ድረስ ከባድ ይሆን?
ዶክተር ዮሐንስ፡ እነዚህ ሰውንና እንስሳን የሚያጠቁ በሽታዎች Zoonotic disease ይባላሉ፡፡ ከ75% በላይ የሚሆኑት የዓለማችን በሽታዎች Zoonotic ናቸው፡፡ ሰማንያ በመቶ በሽታዎች ከእንስሳት ወደ ሰው የሚተላለፉ ናቸው፡፡ ከ Zoonotic disease መካከል እንደ የእብድ ዉሻ በሽታ(Rabies)፡ አባሰንጋ ( Anthrax) የሳንባ ነቀርሳ (Tuberculosis ) የውርጃ በሽታ(Brucellosis) እና የኮሶ ትል (Taeniasis) መጥቀስ ይቻላል፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ ሙያችሁ አስፈላጊው እውቅና ተሰጥቶት የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ይወጣ ዘንድ ምን መደረግ ይኖርበታል?
ዶክተር ዮሐንስ፡ በእርግጥ አርብቶአደሩ በተወሰነ ያውቀዋል፡፡ አስፈላጊነቱም ምንም አያጠያይቅም፡፡ በመንግስት ልዩ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡ ያው ለብዙ ጉዳይ መንግስት ይባላል እንጂ ሁሉም አካላት ሚና ይኖራቸዋል፡፡ ካለን ሃብት አንጻር መጠቀም አለብን፡፡ ባለሙያው ተገቢውን ድጋፍ ካገኘ ብዙ ስራ መስራት ይችላል፡፡ የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች እና የላቦራቶሪ እቃዎች በየወረዳው መሟላት አለባቸው፡፡ በተጨማሪ ክትባት ለተወሰነ ጊዜ የሚቀመጥበት ያስፈልጋል፤ ለዚህም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ይፈልጋል፤ ይህ ደግሞ በወረዳዎች ላይ አስቸጋሪ ነው፡፡ ክትባቶች በተገቢው ሁኔታ ካልተቀመጡ እና ተገቢውን የሙቀት መጠን ካላገኙ ይበላሻሉ፡፡ ይህ ደግሞ የሀብት ብክነትን ከማስከተል በተጨማሪ በሽታዎች እንዲስፋፉ እድል ይሰጣል፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ በእንስሳት ህክምና ዘርፍ ከተመደቡ በኋላ ሰዎች የሚሰማቸውን ነገር ታዝበህ ይሆን?
ዶክተር ዮሐንስ፡ ሳይፈልግ የሚገባ ይኖራል፡፡ ከገባ በኋላ ግን መውደድ ይኖርበታል፡፡ ስትመረቅ ደስ ብሎህ መውጣት አለብህ፡፡ ሳይፈልጉት ገብተው ነግር ግን ወደውት ጠንክረዉ ሰርተው የተሻለ ውጤት እያገኙ የሚመረቁ ብዙ ናቸው፡፡ ሙያውን ስታውቀው ነው መውደድ የምትችለው፡፡ ዘርፉ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ ወደፊት ምን ይደረግ?
ዶክተር ዮሐንስ፡ መሟላት ያለባቸው ነገሮች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ የአቅም ውስንነት ቢኖርም በተቻለው አቅም ጥረት መደረግ አለበት፡፡ የውጪ ድርጅት እገዛ ያስፈልጋል፡፡ ይህ ግን መንገድ ያስይዘናል እንጂ ሁሉንም ነገር መስራት አይችሉም፡፡ በህብረተሰብ ውስጥም ብዙ ግንዛቤ መፍጠር ያስፈልጋል ከ Zoonotic disease ፤በሽታን ከመከላከል እና እንስሳትን ከማሳከም አንጻር፡፡  ብዙ የሚቀረን ነገር አለ፤ ያንን ለማሻሻል ከሰራን ለውጥ ማምጣት እንችላለን፡፡
የሸዋ ፀሐይ፡ አመሰግናለሁ፡፡
ዶክተር ዮሐንስ፡ እኔም አመሰግናለሁ፡፡


በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...