የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መግቢያ ወቅት መቃረቡን አስመልክቶ በጸጥታ ስጋት ምክንያት ተማሪዎች ወደ ምድብ ቦታቸው ላለመሄድ እያንገራሩ ነው። ከዚህ ያልተናነሰ ስጋትም አለ። ይኸውም የዩኒቨርስቲ መምህራንም ወደ ትውልድ አካባቢዎቻቸው በዝውውር እየፈለሱ ነው። ይህ ትልቅ ሥጋት ይመስለኛል። ለሚፈናቀሉ ዋስትና ሰጥቶ ተረጋግተው እንዲቀመጡ ማድረግ ያስፈልጋል። ቢያንስ ህብረተሰቡ አለኝታነቱን የሚያረጋግጥበት መንገድ ይቀየስ። የእድር፣ የኃይማኖት፣ የተቋማት ወዘተ መሪዎች "ችግር ቢመጣም ዋስትና እንሰጣችኋለን፤ ልጆቻችን አይነኳችሁም" ብለው መምህራኑን ሰብስበው መለመን አለባቸው። ይህን ማድረግ ካልተቻለ ወይም ዓይነተኛ መፍትሔ ካልተፈለገ ሁሉም ወደ ትውልድ ቀዬው ሲሰበሰብ የባሰ አደጋ ያመጣል። ሠው በሃገሩ ተዘዋውሮ መስራትና መኖር ይሳነዋል። ሰከን ካሉ ሰዎች አማራጮች መቅረብ ይኖርባቸዋል።
የጉዞ፣ የንባብ፣ የቤተመጻሕፍት ፣ የሕትመትና ስርጭት ወዘተ ጽሑፎችን ያገኙበታል። I share my views and reports of my activities in this blog.
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ብሔራዊ አገልግሎት ሲነሣ
ብሔራዊ አገልግሎት ሲነሣ ከ2008 ዓ.ም. ያለኝ በኢትዮጵያ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጊዜ የነበረው ብሔራዊ አገልግሎት በሚገባ የተጠና ነው። ከረጅም ዓመታት በፊት በጉዳዩ ላይ መጻሕፍትንና አጫጭር ጽሑፎችን ያነበብኩ ይመስለኛ...
-
6 June 2019 Basic Writing Skills (Sophomore English) Lecture 1.1. Phrases and Clauses 1.1.1. Phrases A phrase can ...
-
'አልፀፀትም' የተባለው የጃዋር መሐመድ መጽሐፍ ወደ መደምደሚያው ዲሞክራሲን በኢትዮጵያ ለማምጣትና አገረመንግሥቱን ከውድቀት ለመታደግ ይጠቅማሉ የሚላቸውን ሐሳቦች ይጠቁማል። ይህን ግን ደጋግሞና በስፋት ካቀረበው...
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ