ሐሙስ 25 ኦክቶበር 2018

ሰከን ካሉ ሰዎች አማራጮች መቅረብ ይኖርባቸዋል

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መግቢያ ወቅት መቃረቡን አስመልክቶ በጸጥታ ስጋት ምክንያት ተማሪዎች ወደ ምድብ ቦታቸው ላለመሄድ እያንገራሩ ነው። ከዚህ ያልተናነሰ ስጋትም አለ። ይኸውም የዩኒቨርስቲ መምህራንም ወደ ትውልድ አካባቢዎቻቸው በዝውውር እየፈለሱ ነው። ይህ ትልቅ ሥጋት ይመስለኛል። ለሚፈናቀሉ ዋስትና ሰጥቶ ተረጋግተው እንዲቀመጡ ማድረግ ያስፈልጋል። ቢያንስ ህብረተሰቡ አለኝታነቱን የሚያረጋግጥበት መንገድ ይቀየስ። የእድር፣ የኃይማኖት፣ የተቋማት ወዘተ መሪዎች "ችግር ቢመጣም ዋስትና እንሰጣችኋለን፤ ልጆቻችን አይነኳችሁም" ብለው መምህራኑን ሰብስበው መለመን አለባቸው። ይህን ማድረግ ካልተቻለ ወይም ዓይነተኛ መፍትሔ ካልተፈለገ ሁሉም ወደ ትውልድ ቀዬው ሲሰበሰብ የባሰ አደጋ ያመጣል። ሠው በሃገሩ ተዘዋውሮ መስራትና መኖር ይሳነዋል። ሰከን ካሉ ሰዎች አማራጮች መቅረብ ይኖርባቸዋል።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የትምህርት አቅጣጫ ወዴት ነው?

 የትምህርት አቅጣጫ ወዴት ነው? ትምህርት አጉል አቅጣጫ እየሄደች ይመስላል። ለዚህ ማሳያ የተወሰኑ ክስተቶችን ላንሳ። ከሰሞኑ አንዲት መምህር እያስተማረች የነበረበት ክፍል ለፈተና ተፈልጎ እንድትወጣ ስትጠየቅ በጥያቄው ተስ...