2023 ኖቬምበር 21, ማክሰኞ

የአንባቢ ተፈናቃይ ልጆች መርሐግብር

 የአንባቢ ተፈናቃይ ልጆች መርሐግብር 

ደብረብርሃን 


(Read and Get Uniforms, Read and Eat,

Read and Trade)


ውድ የቤተመጻሕፍታችን ቤተሰብ፣

በከተማችን ከሚገኙ የተፈናቃዮች መጠለያ ካምፖች እየወጡ በየመንደሩ ምግብ ስጡን እያሉ የሚዞሩ ልጆችን አስመልክቶ ምን ማድረግ እንዳለብን ስናስብ ቆይተናል። ልጆቹ ወደ ቤተመጻሕፍታችን እየመጡ እንዲያነቡና እንዲማሩ እያደረግን ነው። ከዚህ ጎን ለጎን እስካሁን በምንሰራቸው ሥራዎች በተለይ በአብያተመጻሕፍት ዲጂታላይዜሽን ላይ የሥራ ግንኙነት ካለን ከኢትዮጵያ 2050 ማህበር በኩል ልጆቹን በተወሰነ መጠን ለማገዝ ፍላጎት አለ። ይኸውም በዓመት ለሃያ ልጆች ዩኒፎርም ለማልበስ (በአንድ ልጅ 700 ብር)፣ ስምንት ልጆችን አነስተኛ ስራ ለማስጀመር (ለእያንዳንዳቸው 1000 ብር)፣ በሳምንት መጨረሻ ቀናት አንድ ጊዜ እስከ 600 ብር የሚያወጣ ምግብ ለመመገብ ታስቧል። ከዚህ ጎን ለጎን ከማህበሩ የመጣ ሃሳብ አለ። ይኸውም የደብረብርሃን ህብረተሰብ ይህን ማህበሩ ያገዘንን ያህል በገንዘብ፣ በአገልግሎት (ማስተናገድ፣ ማስጠናት ወዘተ)፣ በዓይነት (ምግብ፣ ልብስ፣ ዕቃ ወዘተ) እንዲሰጥ ነው። ስለሆነም ፍላጎቱ ያላችሁ ወገኖች እንድታናግሩን እንጠይቃለን። 

ቤተመጻሕፍቱ

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...