2015 ጁላይ 20, ሰኞ

Cave Guard

Teshome Hailegnaw, the guard of the cave, explains its history. Location - Sasit, 90 kms from Debre Birhan. Promoter- Mezemir Girma- mezemir@yahoo.com

Engidwasha Cave, 90 kms from Debre Birhan

This cave is the heritage we are proud of. To find out more follow us at Segenet Ethiopia on fb and twitter!

2015 ጁላይ 3, ዓርብ

አርበኛዋ ግራር

የጉዞ ማስታወሻ በመዘምር ግርማ mezemir@yahoo.com ሚያዝያ 27፣ 2007 ዓ.ም. ሁለት መምህራን የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማሀበር ወደተመሰረተበት ስፍራ ተጉዘን ነበር፡፡ ጉዟችን በመስሪያ ቤታችን በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መኪና ሊሆን ቢታሰብም መኪኖቹ በሌላ ስራ በመያዛቸው በህዝብ ትራንስፖርት እንድንጓዝ ሆነ፡፡ አምና ሰባት ሆነን ወደ ስፍራው ስንጓዝ የገጠመን በየደቂቃው የሚበላሽ መኪና እና ስንመለስም የነበረችው መኪና ውስጥ የምትወልድ ሴት ዓይነት ያልታሰበ ነገር ስላላጋጠመን የዘንድሮው ጉዟችን የተሻለ ነበር፡፡ የጉዟችን ዓላማም በበዓሉ አከባበር ላይ መሳተፍና የስፍራውን ታሪክ መጻፍ ነበር፡፡ ከደብረ ብርሃን እስከ ጣርማበር ባለው 50 ኪሎሜትር አስፋልት ሸለቆውን እየቃኘን ሄድን፡፡ ጣርማበር ከተማ ስንደርስ መኪናችን ውስጥ የምግብና ፍራፍሬ ሻጮች አጥለቀለቁን፡፡ ‹‹ጦስኝ፣ ቆሎ፣ ኩኪስ፣ አገዳ፣ ሙዝ›› ሲሉ ለጆሮ እንደሙዚቃ ይጥማሉ፡፡ ከዚያም 22 ኪሎሜትሩን ፒስታ መንገድ ቁልቁል በስተ ምዕራብ ሰላድንጋይ ድረስ መንገጫገጭ ግድ ይላል:: እዚያች ታሪካዊ ከተማ ሰላድንጋይ ላይ ቆም ብሎ አጼ ምንሊክ የቆረቆሩት የቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን እና የቅድም አያታቸው የልዕልት ዘነበወርቅ ሰገነት በከተማው ዳርቻ ጎን ለጎን ለፍልሚያ የተዘጋጁ አውራ ዶሮዎች መስለው ተረተር ላይ ቆመው ተፋጠው ሲጠባበቁ እያዩ ዘመናዊው ምስራቅ ሆቴል በረንዳ ላይ ሻይ ቡና ማለት የቤተክህነትንና የቤተመንግስትን ተጠባብቆ ኑሮ ያስገነዝባል፡፡ የሞጃና ወደራ ወረዳ ትልቋ ከተማ የሆነችው ሰላድንጋይ ከተማ ከመቼውም በላይ ተውባ ጠበቀችን፡፡ ከመብራት እንጨቶች በአውራ መንገዱ አግድም ከዳር እዳር ረጃጅም የኢትዮጵያ ባንዲራ ሶስት ወይንም አራት ቦታዎች ላይ ተንጣሎ አየን፤ ፎቶም ተነሳን፡፡ ይህ ሁሉ ባንዲራና ድምቀት ግን የአርበኞች በዓልን ለማሰብ መስሏችሁ እንዳትሳሳቱ፡፡ የህዳሴው ግድብ ዋንጫ ወደ ወረዳው በማግስቱ ስለሚመጣ አቀባበል ለማድረግ ነው፡፡ ይህ የግድብ ዋንጫ በሚዞርባቸው ከተሞች ሁሉ ለቦንድ ቃል ይገባል - ይፈጸምማል! ሰላድንጋይ ከተማ ላይ በአንድ ቤት በር ላይ ሳልፍ ስለአርበኞች በሬድዮ ሲወራ ሰማሁ እንጅ ምንም የበዓል አከባበር በከተማዋ አላየሁም፡፡ በነገራችን ላይ እርስዎም ጓድ መንግስቱ ኃ/ማርያም እንዳሉት ‹‹ሰላድንጋይ ምንድነው?›› የሚሉ ከሆነ ግን ከተማዋ ያላትን ታሪክ ብቅ ብለው ይጎብኙ እልዎታለሁ፡፡ ወደ ሳሲት የሚወስድ መኪና በየሰዓቱ ስለማይጠፋ ጠብቆ መሳፈር ይቀጥላል ከዚህ በኋላ፡፡ ይችን የሳሲት 20 ኪሎሜትር መንገድ በእግራችን ስንትና ስንት ጊዜ ፉት እንዳልናት! መኪና ደግሞ ወደ ደብረ ብርሃን ተመላሿ ጠዋት ካመለጠችን ሰላድንጋይ ላይ ማደር ግድ ይል ነበር፡፡ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከአስር ዓመት በፊት አልነበረም፡፡ ስልክ ደግሞ አንድ የህዝብ ስልክ ቤት ነበረች፡፡ ውሃውም መጠነኛ ነበር፡፡ አሁን ግን እየተሻሻለ መጥቷል፡፡ ከብሄራዊው ኬክ ጠርዝ ሞጃዎች ትንሽ እየላሱ ነው ለማለት እችላለሁ፡፡ ሞጃዎችን እኮ ጃንሆይ አሳደዋቸዋል፡፡ ልጆቻቸው መንግስቱ እና ግርማሜ ነዋይ ‹አስቀይመዋቸው› ሞጃ የተባለን ሁሉ ከስራ አባረዋል፡፡ ያ አልፏል፤ አሁን ግን ከመንግስት ጋር ታርቀዋል፡፡ ለማናቸውም ሳሲት የሚሄደው መኪና ላይ እኔ፤ ሳለአምላክ ጥላሁን እና እሙዬ አረጋ (ጊፍቲ እኔ እንደምጠራት) (ይቺ ልጅ አምና አብራን ለአርበኞች በዓል ስትሄድ የአባቷን የጋሼ አረጋን ሞት በስልክ አርድተዋት እነዚህም አባቶቼ ናቸው ብላ አርበኞቹን አይታና ለልጆቻቸው ትምህርት ቤት እንዲቀመጥ የገዛችላቸውን የመጻሕፍት ስጦታ ሰጥታ ነበር የመጣችው) ተሳፈርን፡፡ የሳሲትን መንገድ ሳጋምሰው ከሰላድንጋይ ወደ ሳሲት በእግሩ የሚወርድ አንድ ጉብል ተቀኘ ያሏት ግጥም ትዝ አለችኝ፡፡ እነሆ- ሰላድንጋይ ውዬ ባር ሜዳ መሸብኝ ላጨርሽው ፍቅር ምነው ጀመርሽብኝ! ከሰላድንጋይ ወደ ሳሲት ስንሄድ ያገኘሁት የወረዳው ሰራተኛና የትውልድ ስፍራው አንዲት ግራርን አልፎ ጋውና ላይ የሆነው አቶ ሶሎሞን አበበ ‹‹ይህ በዓል አርበኞች አገሪቷን ከጠላት ወረራ ለመከላከል ያደረጉትን ተጋድሎ ለማስታወስ ሲባል የሚከበር በዓል ነው፡፡ ሰራተኛው እንጅ ተማሪው እና አርሶ አደሩ የምን በዓል እንደሆነ አያውቁትም - ሚዲያ ስለማይከታተሉ፡፡ መድረክ በየቀበሌው እና በየወረዳው ቢዘጋጅ ብዙ ሰው ያውቀዋል፡፡ በአርበኞቻችን ኩራት ይሰማኛል፡፡ ስለበዓሉ ግን በትምህርት ቤት ምንም የተማርኩት ነገር አልነበረም፡፡›› በመኪናችን ውስጥ ለቀስተኞች ተቀምጠዋል፡፡ የየራሱን መንገድ የሚሄደውን ያደርሳል ሹፌሩም፡፡ ሳሲት ደርሰን በደጓ በወይዘሮ ዘነበች አስፋው ቤት ስንጋበዝ ይህችን ተዘውታሪ ግጥም አስታወስኩ - ኧረ ሳሲት ሳሲት ትንሿ ከተማ የሚበላው ስንዴ ጉዝጓዙ ቄጠማ ! ከዚች ከተማችን ወደ መዳረሻችን የሚወስደን መኪና እስኪገኝ ቡና መጠጣትና ምሳ መብላት ያዝን ያውም ሁለት ቤት ገብተን፡፡ ‹‹በእግራችን አስር ኪሎሜትሩን እንሂድ›› ስል አብራን ያለችው ልጅ ‹‹አልችልም›› አለችና ቀረን፡፡ የአርበኞች መታሰቢያ የሆነው የግራር አምባ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አሰፋ አስታጥቄ ናቸው የዘንድሮ መርሃ ግብር አዘጋጅ፡፡ መሪነቱ ወደ ትምህርት ቤቱ መተላለፉ በዓሉ የወላጆች፣ የመምህራንና የተማሪዎች ስለሚሆን ቀጣይነቱን ያረጋግጣል፡፡ ከእርሳቸው ጋር ስልክ እየተደዋወልን እየመጣን እንደሆነ ነገርናቸው፡፡ ሌሊቱን ሙሉ መብራት ጠፍቶ አድሮ የኔም ስልክ ዘግቶ ስለነበር በጓደኞቼ ስልክ ነበር የደወልኩላቸው፡፡ ከቤታችን ስንነሳና እርስ በእርስ ስንቀሳቀስም በአካል ሄደን ነበር እንጅ የስልክ ነገር ልይቶለት ነበር፡፡ ወደ ግራሯ ለመሄድ መኪና ስንፈልግም ኮንትራት 600 ብር ክፈሉ ተባልን፡፡ በዚህም ወቅት ከዘነበች ቤት ተሰናብተን ሄደን በታላቅ ወንድሜ ቤት ቡና እያስፈላን ስለነበረ መኪና ካልተገኘ እዚሁ ሰብሰብ ብለን እናክብር የሚል ሃሳብ ሰነዘርኩ፡፡ ከሳሲት ወደ አንዲት ግራር የሚወርዱ አምስት የሳሲት ነዋሪዎችም ስለነበሩ ነው እዚሁ እናክብረው ማለቴ፡፡ ህዝቡ መጀመሪያ የወላጆችን በዓል በግራር አምባ ትምህርት ቤት አክብሮ ወደ ግራሯ መጥቶ እየጠበቀን እንደሆነ በመስማታችን ከህዝቡ ጋር ለማክበር ወደ ግራሯ ለመሄድ ጓጉተን ነበር፡፡ ግራር አምባ ትምህርት ቤት የወላጆች በዓል ሚያዝያ 27 መከበሩ አያኮራዎትም? እውነትም የአርበኞች መታሰቢያ ትምህርት ቤት! በመሆኑም አንድ የወረዳው የስራ ሃላፊ በስልክ ደውለው መኪና አስመጥተውልን ፒክ አፕዋ ላይ ከውስጥም ከላይም ሆነን ወደ ስፍራው አመራን፡፡ የእለቱ ልዩ እንግዳና ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ስፍራውን ያየው የበላይ ዘለቀ ያገር ልጅ መምህር ሳለአምላክ ጥላሁን በሳሲት የቤቶቹ መጠጋጋትና የህዝቡ መጎሳቆል አሳዝኖታል፤ አስገርሞትማል፡፡ እኔ ግን እዚያው ተወልጄ ስላደግሁ ምንም አልመሰለኝም ነበር፡፡ ወደ አንዲት ግራር በሚወስደው መንገድ ስንሄድ የገጠር ቤቶችንና የእርሻ ማሳዎችን እንዲሁም አልፎ አልፎ የሚታዩ የግራር ዛፎችን እያየን ነበር፡፡ የአማራ ክልል ኤፍ ኤም ባለፈው ዓመት በአንዲት ግራር ተገኝቶ የዘገበውን ዘገባ ዘንድሮ በድጋሚ እያቀረበው ኖሮ በመኪናው በተከፈተው ራድዮ ስናደምጠው ወረድን፡፡ ድንቅ ዝግጅት ነበር፡፡ በዚህ ዓመት አቶ ሕላዌ ዮሴፍና አቶ አዲሱ ለገሰም ግራሯን እንደጎበኙ ሹፌራችን ኤርሚያስ በጨዋታ መሃል ነግሮኛል፡፡ ከጥቂት ዓመታት በፊት ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን ባለውቃቢ ወፋ ነገሰን ለመጠየቅ ከሃገራችን የተለያዩ ክፍለ ሃገራት የሚመጡት ባለጉዳዮች በእግራቸው ወደ እርሳቸው መንደር ለመሄድ መንገዱን ሲጠይቁ የሳሲት ነዋሪ ‹‹ዝም ብላችሁ መኪና መንገዱን ተከትላችሁ ስትሄዱ አንድ ትልቅ ግራር ሜዳው ላይ ታገኛላችሁ፡፡ ከዚያ ወደ ቀኝ ታጥፋችሁ ትንሽ ሄዳችሁ እርሳቸው ቤት ትደርሳላችሁ፡፡›› የሚሏቸው ትዝ አለኝ፡፡ በእርግጥ ገንዘብ ለሚከፍል ተጓዥ መንገድ የሚያሳዩና ሻንጣ የሚሸከሙ ወጣቶች ሳሲት አይጠፉም ነበር፡፡ ይህ የሚሆነው የመሬሬው ጥቁር ጭቃ መኪና በማያስገባበት በክረምት ወቅት እንጅ በበጋማ በጭነት መኪና ተጭኖ የሚሄደው ሰው በአንድ ጊዜ ወደ መቶ ይጠጋ ነበር፡፡ አሁን ሳስበው የሚያናድደኝ አንድ ከተሜ በልጅነቴ አይቻለሁ፡፡ ተስተናግዶ ሲጨርስ ወፋ ነገሰ ቤት አቅራቢያ ያሉ አርሶ አደሮችን ‹‹ታምሜያለሁና በቃሬዛ ተሸክማችሁ ሳሲት ድረስ አውጡኝ ፤ ባይሆን ገንዘብ እከፍላችኋለሁ›› ብሎ ተሸክመው ይዘውት መጥተው ገንዘቡን ከፍሎ እየሳቀ ከተሸከሙበት አልጋ ሲወርድ አይቻለሁ፡፡ ቅኝ ገዥዎች የአፍሪካ ህዝብ ላይ እንዳደረጉት ያለ ለህዝቡ ያለውን ንቀት የሚያሳይ ድርጊት ነው፡፡ አሁን ወደ አርበኞች በዓላችን እንመለስ፡፡ ጥላሁን ጣሰው የመጀመሪያው በኢትዮጵያ ውስጥ የተመሰረተው ዲሞክራሲያዊ ማሕበር የሆነው የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር የተቋቋመበት አንዱ ምክንያት ለአርበኛው ድርጅት ማስፈለጉ ግልጽ በመሆኑ ነበር ይሉናል፡፡ የማህበር ማቋቋሙ ሂደት ግን ፈተናዎች እንደነበሩበት ታሪክ ያወሳል፡፡ ከእነርሱም ውስጥ በአርበኞች መካከል አለመስማማት፣ እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ማለት እና ወደ ጠላት መክዳት ይጠቀሳሉ፡፡ ‹‹የነጻነታችን መሰረት አንዲት ግራር›› በሚል ርዕስ የሞጃና ወደራ ባህል እና ቱሪዝም ጽ/ቤት ያዘጋጀው ግንቦት 2007 የተዘጋጀ ያልታተመ ጽሑፍ እንደሚያትተው ‹‹የሚንቀሳቀሰውን የወራሪ ጦር መደምሰስ የሚያስችል ሌላ የጦር ስልት ለመንደፍ በባላምባራስ በሻህ ኃይሌ አመራር ሰጭነት በየዱር ገደሉ የነበሩት አርበኞች ያስከተሉትን ጦር በመያዝ ጥር 1፣ 1931 በእንግድ ዋሻ ቀበሌ፣ አንቀላፊኝ ሜዳ፣ አንዲት ግራር ስር እንዲሰበሰቡ ትዕዛዝ ተሰጠ፡፡ በትዕዛዙ መሰረት ሁሉም የጦር አለቆች ያስከተሉትን ጦር በመያዝ በተባለው ቦታ እንዲገኙ ተደረገ፡፡ ወደ ስፍራው ከመጡት መካከል ዋና ዋናዎቹና ይመሩት የነበረው የጦር ሃይል ብዛት ራስ አበበ አረጋይ - 1600 ጦር ልጅ ግዛቸው ኃይሌ - 800 ጦር ባላምባራስ በሻህ ኃይሌ - 600 ጦር ደጃዝማች ተሰማ እርገጤ - 600 ጦር ፊታውራሪ ታደሰ በላይነህ - 600 ጦር ልጅ ከፈለው ወልደጻድቅ - 500 ጦር አቶ ፀሐይ እንቁ ሥላሴ - 750 ጦር ራስ መስፍን ስለሺ 1600 - ጦር ›› (3) ነበር፡፡ ሰነዱ ሲቀጥልም ‹‹እነዚህን የነጻነት አባት አርበኞችን ሊዘክር የሚችል ሃውልት በቦታው ተሰርቶ ጥር 1፣ 2002 ዓ.ም. በጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ ተመርቋል፡፡›› (4) ይለናል፡፡ አርበኞች የተሰባሰቡባት የሰፊው ሜዳ ጌጥ የነበረችውን አንዲት ግራር ለመጀመሪያ ጊዜ ያየኋት በ1990 የ6ኛ ክፍል ተማሪ ሆኜ ሲሆን አጥር የነበራትም ይመስለኛል ያኔ ሳያት፡፡ አድባር ነበር የመሰለችኝ፡፡ ታሪኳን አሁን ነው እየተረዳሁት የመጣሁት፡፡ አሁን ግን ነሐሴ 6 በጣለው መብረቅ የቀላቀለ ዝናብ ምክንያት መብረቅ መትቷት ወድቃለች፤ ህዝቡም እንደሰው ቁርባን እንዳቆረበላት እና ውለታዋን እንዳልዘነጋ ይታያል፡፡ ግራሯ ወዴት ወገን ወደቀች፤ እንዴት ወደቀች እየተባለ የራሱ የሆነ ትንታኔ በአካባቢው ነዋሪዎች ተሰጥቷል፡፡ አንድ ትልቅ ሰውም ይወድቃል የሚል ስጋት ጥሎባቸው ነበር፡፡ የቀድሞው የሰሜን ሸዋ አርበኞች ሊቀመንበር ባላምባራስ በየነ ይህ ስፍራ አርበኞች ማህበር በመመስረት ትግሉን ያጠናከሩበት የቃል ኪዳን ቦታ ነው ይሉናል፡፡ አርበኞች ከአራት ኪሎው ዋና ጽ/ቤታቸው ለመታሰቢያ በአቅራቢያው የተመሰረተውን የግራር አምባ ትምህርት ቤትንም ያግዛሉ፡፡ አዲሱ ሊቀመንበራቸው ልጅ ዳንኤል መስፍን ስለሺም ትምህርት ቤቱ የሚያስፈልጉትን ቁሳቁሶች በራሳቸው ወጭ በከፊል አሟልተዋል፡፡ እንግዲህ በዚህ ስፍራ የምናስባቸውን አርበኞች ተግባር ምንነት ለመረዳት አንድ ስማቸውን ለመጥቀስ ያልፈለጉ መምህርን አርበኛ ማለት ምን ማለት ነው? ብዬ ጠይቄያቸው ‹‹አርበኛ ማለት ትልቅ ጥልቅ የሃገር እና የወገን ፍቅር ያለው፣ የሃገሩን እና የወገኑን ጉዳት ማየት የማይሻ እና ለዚህም ማሳያ የሚሆን ውድ የሆነውን የህይወት መስዋዕትነት እስከመስጠት ድረስ ወደኋላ የማይል ነው፡፡›› ብለውኛል፡፡ ለእርስዎስ አርበኛ ምንድነው? የአርበኞች ቀንን እንዴት ያከብሩታል ብዬ ላቀረብኩት ጥያቄ እኝሁ መምህር ሲመልሱልኝ ‹‹በውስጤ ነው የማከብረው፤ አከባበራችን ይለያያል፡፡ የማስበው ያን ያክል መስዋዕትነት ለማድረግ የነበራቸው የህዝብና የሃገር ፍቅር ስሜት ምናልባትም አሁን ካለው ትውልድ ጋር በማወዳደደር ዛሬስ ያለው ትውልድ ይሄን ትልቅ የህዝብ እና የሃገር ፍቅር ስሜት ይኖረዋል ወይስ ጠፍቷል የሚል አከባበር ነው፤ ስለሚያሳስበኝ ነው፡፡›› እኝህ መምህር ወደ ስፍራው ሳንሄድ ከሰጡኝ ከዚህ ምላሽ እንደምንረዳው በህሊናው አርበኞችን የሚያስብ እንዳለ ነው፡፡ በዓሉን በመሰባሰብ የሚያከብሩት ሰዎችስ እንዴት ያከብራሉ የሚለውን እስኪ እንይ! ግራሯ በስፍራው ወድቃ ማንም ሳይነካት እንዳለች ይሄው አምስተኛ አመቷን ልጽደፍን ነው፡፡ ግራሯ ወድቃ ባችበት ስፍራ ስንደርስ ህዝቡ ተሰባስቦ ይፎክርና ይሸልል ነበር፡፡ በስፍራ የተገኙት ተማሪዎች፣ ወላጆች እና ተጋባዥ የአካባቢው ነዋሪዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ነበሩ፡፡ እኔና ጓደኛዬ መምህር ሳለአምላክም የተሰማንን ስሜትና ህዝቡ ስላዘጋጀው ዝግጅት ያለንን አክብሮት ገለጽን፡፡ አንዲት ሰላድንጋይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የምትማር ወጣት የላከችው ግጥም በመምህር ሻውል ማሞ ሲነበብ ስሰማ የወጣቱን ተሳትፎና ፍላጎት አደነቅሁ፡፡ ከግጥሟ ሁለት መስመር ብንወስድ ‹‹ኑ ታምሯን እዩ የሸዋን አፈር አብቅላለችና አንዲቷን ግራር፡፡›› ይላል፡፡ ድንቅ እይታ! ለግራር አምባ ትምህርት ቤት በስጦታነት ይዤ የሄድኩትን አጀንዳ መያዣ መዝገብ በስነ ስርዓቱ ላይ ሳበረክት አንድ ሽማግሌ የሚከተለውን መልዕክት ጽፈው ሰጡኝ፡፡ ‹‹ለመምህር መዘምር ግርማ፣ በረከቱ በአርበኛው ሰብሳቢ በኩል ለተረካቢው ቢሰጥ›› ይል ነበር፡፡ ለአርበኞና ለማህበራቸው ስጦታ ይዤ ባለመሄዴ ተጸጸትኩ፡፡ በሌላ ቀንም ለመውሰድ ቃል ገባሁ፡፡ በወረዳው 602 አባላት ያሉት የአርበኞች ማህበር ነው ያለው፡፡ ከስጦታ ወሬ ሳንወጣ ባለፈው ዓመት ለግራር አምባ ትምህርት ቤት ያሰባሰብንውን መጽሃፍ ስንለግስ የሌሎቹ ትምህርት ቤቶች ወላጆች ‹‹ሁሉንም ለግራር አምባ መስጠታችሁ ምነው?›› ብለውኝ ስለነበር መጽሐፍ ለሌሎቹም ወደፊት የማሰባሰብ የቤት ስራ አለብኝ፡፡ ሌላ የደረሰኝ ማስታወሻ የሚከተለው ነው፡፡ ‹‹ማሳሰቢያ ሰጭ አቶ አወቀ አክሊሉ ስሆን በዚች አንዲት ግራር እንድትተካ አንድ እግር ወርካ ተክዬ እየተንከባከብኩ ስገኝ አጽድቄ እያለሁ ሰዎች ነቅለውብኝ ሞራኔ ከስሮ እገኛለሁ፡፡›› ይላል፡፡ ባለፈው ዓመት አሁን ወድቃ በምትገኘው ግራር ምትክ እንዲተክሉ የቤት ስራ የወሰዱት አባት ነበሩ ይህን መልዕክት የላኩልኝ፡፡ ጥረታቸው አለመሳካቱ ያሳዝናል፡፡ አርበኞቹ የሚታወሱበት እንደ ህዝቡ ጥያቄ አንድ ሐኪም ቤት ወይንም ሌላ ለሕዝቡ የሚጠቅም ተቋም ቢቋቋም ግን ከዛፍ የበለጠ ማስታወሻ ይሆናል እለላሁ፡፡ አርበኞች በስፍራው በ1931 ዓ.ም. በጦርነት ወቅት ሆነው መደራጀታቸውን ሁሌም አደንቃለሁ፡፡ ያልተደራጀ ሕዝብ ምንም የረባ ነገር ላይሰራ ይችላል ብዬ ስለማስብ፡፡ አባቶች በበዓሉ እለት ስለአርበኞች ማህበር አመሰራረት የሚያውቁትን ነግረውናል፡፡ ሰነዳቸውን ካጸደቁ በኋላ 200 ዓመት ያህል ዕድሜ ባላትና ሰዎች ሲጣሉ በሚታረቁባት በዚህች ታሪካዊ ግራር ላይ ያረዷቸውን በጎች ስጋ ሰቅለው እየቆረጡ እየበሉ ተማማሉ ይሉናል፡፡ የአርበቻችን የትግል ህይወት ምን ይመስል እንደነበርና በስፍራው ተሰባስበው በሚመክሩበት ሰሞን ዋና ዋናዎቹ አርበኞች እነማን ቤት እንዳረፉ ጭምር ተነግሮናል፡፡ ቄስ ለማ ገብረመስቀል ባቀረቡት ግጥምና መልዕክት ማጠቃለያ ላይ የሚከተለውን ብለው ነበር፡፡ ‹‹ክቡራን እንግዶች፣ ትውልድ ያልፋል፤ ስም ግን ከመቃብር በላይ ስለሚቆይ ጊዜውን ጠብቆ በኢትዮጵያ ላይ ፈተና የሚገጥም በመሆኑ ወደፊትም በትጋትና በወኔ መቋቋም እንዲቻል የአርበኞቹን ተተኪዎች ልጆች እንድታስቡን አሳስባችኋለሁ፡፡›› የተዘጋጀውን ዳቦና ጠላ ከተጋበዝን በኋላ እና እየፈረሰች ባለችው ሐውልት አጠገብ ፎቶ ከተነሳን በኋላ ቸኩለን ስለነበር እና ዝናብም ስለጀመረ ወደ ሳሲት የመልስ ጉዞ ጀመርን፡፡ በዚህን ጊዜ አንድ አባት አርበኛ እየሮጡ መኪናችንን ሲከተሉ አይተን አቁመን አሳፍረናቸው ይዘናቸው ስንሄድ የሃምሳ አለቃ በላቸው እንደሚባሉና የሞጃ አርበኞች ሊቀመንበር አንደሆኑ ነገሩን፡፡ ለበዓሉ ሲሉ ይህን ሁሉ መንገድ በእግራቸው ሳይሆን አይቀርም የወረዱት! በበዓሉ ላይ ብዙ የማይረሳ ትዝታ ቢኖረኝም አሁን ስለበዓሉ ያናገርኳቸው ሰዎች ወደሰጡኝ ምላሽ እንሄዳለን፡፡ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን የሆኑት አቶ አክሊሉ ይርጉ ‹‹አንዲት ግራርን ካሁን በፊትም አውቃታለሁ፡፡ ስፍራው ጀግኖች አርበኞቻችን ማህበራቸውን ያቋቋሙበት እንደሆነም አውቃለሁ፡፡ የሰሜን ሸዋው የአርበኞች ማህበርም ለማስተዋወቅ ጥረት እያደረገ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ማስተዋወቁ ደግሞ ታሪኩ ለወደፊቱ ትውልድ እንዲተዋወቅና እንዲቀጥል እንዲሁም ስለስፍራው ዕውቀት እንዲኖረን ያግዛል፡፡ ፋሺስት ኢጣሊያንን በመዋጋት አባት አርበኞቻችን ያደረጉትን ተጋድሎ በተገቢው መንገድ ለመዘከር ያስችለናል፡፡ ቦታውን የቱሪስት መስህብ ለማድረግና ለማስተዋወቅ ኮሌጃችንም ሆነ ዩኒቨርሲቲያችን የጋራ ሃላፊነት አለባቸው፡፡›› እሙዬ አረጋ (ጊፍቲ) ስለ በዓሉ አከባበር በሰጠችኝ አስተያየት ‹‹የአምናው አከባበር አሪፍ ነበር - አስበውበት ነበር፡፡ ዘንድሮ ግን የአርበኞች ሽለላ እንኳን አነስተኛ ነው፡፡ የዘንድሮው ምንም አልታሰበበትም፡፡ ወይ ከምርጫው ወይ ከዋንጫው ሊሆን ይችላል፡፡ አምና በዛ ብለን ነበር የመጣንው፡፡ በእርግጥ ዘንድሮም ትምህርት ቤት አዘጋጅተው ሊሆን ይችላል እኛ ቸኩለን ዝናብም ሆኖ ነው እንጅ፡፡ አምና የልጁ መወለድ ነው ያስመሸን፡፡ የቀይት ጤና ጣቢያን አለፍ ብለን ሲወለድ ደብረ ብርሃን ከምንሄድ ተብሎ ነው የተመለስንው እና ልጁን ሃኪሞች መኪና አዋለዱ፡፡ የልጁ ስም ግን ማን ሆኖ ይሆን? አምና አብረውን በዓሉን ግራሯ ጋ ያከበሩት አራት አባቶች መሞታቸው አሳዝኖኛል፡፡ እኛ ፎካሪው ሰውዬ ሞተው እንዳይሆን …›› ብላኛለች፡፡ እኝህ ፎካሪ ባለፈው ዓመት ‹‹ራያው ከፌ አዳባይ ገባ እንደ ወለፌ ቦንብ አይሮፕላን ቲጥል በተራ መትረየስ ቲጮህ መድፍ ቲያጓራ የጎበራ ልጅ ይደባለቃል ተነጭ ጋራ!›› ብለው ጎራዴ ይዘው ሲፎክሩ የገባኝን ያህል ተረድቼ ግማሹ አማርኛቸው ስለከበደኝ ራሴን ከባህሌና ቋንቋዬ ምን ያህል እንደራቅሁ እንድታዘብ የረዱኝ ናቸው፡፡ እኝህ የኋላሸት የተባሉ ሽማግሌ አሁንም በህይወት እንዳሉ ከመርሃ ግብሩ መጠናቀቅ በኋላ በሌላ ቀን ሰው ጠይቄ አረጋግጫለሁ፡፡ የፖለቲካል ሳይንስና የፍልስፍና መምህሩን ለማ ሚዴቅሳንም በጉዳዩ ላይ አነጋግሬያቸው ነበር፡፡ ለእርሳቸው ‹‹ጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን የእነርሱ የሆነ አንድ ገናና አስተሳሰብ ብቻ ሃገሪቱ የምትመራበት ይሁን ብሎ ማሰብ በጣም ትልቅ ስህተት ነው፡፡ ምንጫቸው ከምንም ይሁን ከምን የተለያዩ አስተሳሰቦችን ማስተናገድ የሚችል፣ የሚጠይቅ፣ በህግ የተሰጠውንም ነጻ አስተሳሰቦችን የመሰንዘር መብቱን የሚጠቀም ትውልድ ሊፈጠር ይገባል፡፡ የራስን ቁሳዊ፣ መንፈሳዊና ታሪካዊ እሴቶች የማያከብር፣ የማይንከባከብ እና የማያሳድግ ትውልድ ብዙም አያድግም፡፡ ‹‹ይሄ ታሪክ የመላው ኢትዮጵያውያን ታሪክ ነው፡፡ እንደዚህ አይነት የጋራ በሆኑ ታሪካዊ ቅርሶቻችን ላይ ሁላችንም ልንሰራ ይገባል፡፡ ያከባበር ስራዓቱ ሰፋ ባለና በደመቀ ሁኔታ ቢከበር ወጣቱ ኢትዮጵያዊነቱን እንዲያስብ እና ሃላፊነቱን እንዲወጣ ያግዝ ነበር፡፡ ነገር ግን ያ አለመሆኑ ነገሮች የበለጠ የከፉ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡ ምክንያቱም አሁን ያለን አዲስ ፌደራል ስርዓት ነው፡፡ ሰዎች በፊት ሲሰማቸው የነበረው ብሔራዊ ስሜት እየተሸረሸረ ክልላዊነት እያየለ መጥቷል፡፡ እና ይህን ባላንስ ያደርግ (ያመጣጥን) ነበር፡፡ ምን ያህል የሚያምር ታሪክ እንደነበረን፣ ከኛም አልፎ ለጥቁሮች አርዓያ የሆነ ታሪክ እንደነበረን ያስታውስ ነበር፤ ሊሰራበት ይገባ ነበር፡፡ ‹‹ትውልድ ያልፋል ሃገር ግን ቋሚ ነው፤ ጠንካራና ያደገች አገር ለመመስረት የአንድነት ጠንካራ መሰረት ሊኖር ይገባል፡፡ አሁን ያለው አገር ያለመስዋዕትነት ያገኘነው አይደለም፡፡ ዋጋ ተከፍሎበታል፡፡ ወደፊትም ቢሆን አንድ ሃገር ከውስጥም ሆነ ከውጭ አደጋ አይገጥማትም ማለት አይደለም፡፡ ይችን አገር በነበረችበት የጥንካሬ መሰረት ላይ ለማስቀመጥና እየጠነከረች እንድትሄድ ለማድረግ እንዲህ አይነት በዓላት ቦታ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ ፖለቲካዊ ይዘት ብቻ ሳይሆን ታሪካዊ ይዘትም አላቸው፡፡ በተጨማሪም ብዙ ፋይዳ አላቸው፡፡ የታሪካ አጋጣሚ ሆኖ በወቅቱ የነበሩት የፖለቲካ ልሂቃን ከሰሜን ሸዋ የወጡ ስለነበሩ ይህ የታሪክ መታሰቢያ እዚህ መደረጉ የሚከፋ አይደለም፡፡ ነገር ግን በሌሎች ቦታዎችም ያሉ ወጣቶችም የጋራ የሚያደርጋቸው በዓል ስለሆነ በዓሉ ሁሉም ቦታ ላይ ሊከበር ይገባዋል፡፡›› የአርበኞች መሪዎች በአሁኑ ወቅት የአሁኑ ትውልድ ድህነትን መዋጋት ነው ያለበት ሌላ ወራሪ የለብንም በሚሉት ላይ ለጠየቅኋቸው ጥያቄ ሲመልሱ መምህር ለማ የሚከተለውን ብለዋል፡፡ ‹‹ለአንድ ሃገር ጠላቱ ድህነት ብቻ ነው ብዬ አላምንም፡፡ ችግሩ ፈርጀ ብዙ ነው፡፡ ሁሉንም ችግሮች በጋራ ለመቋቋም የሚያስችለን ስነ ልቦና መፍጠር አለብን፡፡ እንደዚህ ዓይነት ታሪካዊ ክስተቶችን ማውሳት ደግሞ ለዚያ አንዱ መንገድ ነው፡፡ ›› ሌላው ወደስፍራው አብሮኝ የተጓዘው መምህር ሳለአምላክ ደግሞ ‹‹በቦታው የተገኘነው የአርበኞች አባቶቻችንን በዓል ለማክበር ነው፡፡ አርበኞች አባቶቻችን አገራችንን ባህሏን፣ እምነቷን ሃብቷን ጠብቀውልናል፡፡ ሌሎች የአፍሪካ አገሮች ግን ያነበራቸውን ብዙ ነገር አጥተዋል፡፡ የነርሱን ውለታ መክፈል የምንችለው በዓሉን በየዓመቱ በማክበር ነው፡፡ በበዓሉ ላይ ተማሪዎችም አባቶችም ነበሩ፤ የመንግስት ተወካዮች ግን አልነበሩም፤ በዚህ ትንሽ ቅር ተሰኝቻለሁ፡፡ ለበዓሉ ትኩረት እንዳላደረጉ ነው፡፡ እንዲያውም ታስታውስ እንደሆነ ሰላድንጋይ እንደደረስን ከተማዋ በጣም አሸብርቃ ነበር በባንዲራ፡፡ እና እኛ ያሰብነው ምንድነው በዓሉ እየተከበረ ነው በሚል ነበር፡፡ ነገር ግን በኋላ የተረዳነው ነገር የአባይን ዋንጫ ለመቀበል እየተዘጋጁ መሆኑንና ስለበዓሉ ምንም መረጃ እንደሌላቸው ጠይቀናቸው ስለበዓሉ ምንም ዓይነት ነገር አልሰጡንም፡፡ በቦታውም ስንደርስ የመንግስት ተወካይ አልነበረም፡፡ ይህ የሚሳየው በመንግስት ትኩረት እንዳልተሰጠው ነው፡፡ ለወደፊቱ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡ ይሄ በዓል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ተምሳሌት ስለሆነ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡ አካባቢው የመሰረተ ልማት ችግር አለበት፡፡ ትምህርት ቤት ይከፈት ብዬ ስጠይቅ አርበኞች ምንድነው ያሉ ሆስፒታል ቢሆንልን ነው፡፡ እና የጤናም ችግር እንዳለ ያሳያል፡፡ እንደሚታወቀው እድሜህ በገፋ ቁጥር በሽተኛ ትሆናለህ፡፡ እንክብካቤ ያስፈልግሃል፤ ርቀት ሄደህ መታከም አትችልም፡፡ ገቢም ላይኖርህ ይችላል፡፡ እና በዚያ አካባቢ ለአርበኞች ሆስፒታል እንዲቋቋምላቸው ለመጠየቅ እንደተዘጋጀን አስታውሳለሁ፡፡ ሳሲትን ከጠበቅኋት በታች ነው ያገኘኋት፡፡ ምን አልባትም የኪስ ከተማ ስለሆነች ይሆናል ብዬ አሰብኩ፡፡ መንገዱ አስፋልት አልሆነም ከዋናው መንገድ ገባ ስትል፡፡ ምንም እንኳን ምቹ ቢሆንም አስፋልት ቢሆን ጥሩ ነው፡፡ በክረምት ግን ጭቃ ሊሆን ይችላል ብዬ አስባለሁ፡፡ እና በጣም ግሎባላይዜሽን (ሉላዊነት) የገባባት ከተማ አትመስልም፤ በጣም ትንሽዬ ከተማ ናት፤ ደህና ካፌ እንኳን የለባትም፤ ገብተን ቡና ልንጠጣ ሻይ አዝዤ ቡና ብቻ ነው ያለው አለችኝ፡፡ ህዝቡም ቢሆን ምን ያህል በድህነት አረንቋ ውስጥ ያለ ህዝብ መሆኑ ያስታውቃል፡፡ እኔ ስፍራው ላይ ተገኝቼ በዓሉን በማበሬ ኩራት ተሰምቶኛል፡፡ ለወደፊቱም ሌሎችንም አሳምነን መንግስትም ያመነበት አይመስልም መንግስትም ህብረተሰቡን ቀስቅሶ እንድናከብር እመኛለሁ፡፡ ይህ በዓል እንደሚታቀው ትልቅ በዓል ነው፡፡ እዚያ ግራር አለች አባቶቻችን ጣሊያንን ለመዋጋት መጀመሪያ የተደራጁባት፤ ይሄ ነው የምትለው እንኳን ሐውልት አልቆመለትም፤ ይሄ በጣም የሚያሳዝን ነገር ነው፡፡ይሄ የውጭ ወራሪን ያሸነፍንበት በዓል ነው፡፡ እና በግሌ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡ ወደፊትም ህጻናቱ እንዳቀረቡልን ስነጽሑፍ አዘጋጅተን ሰዎችንም ይዘን ተደራጅተን እናከብረዋለን ብዬ አስባለሁ፡፡ ›› መንግስት ለአርበኞች ማህበር መጠናከሪያ ገንዘብ እና ሌላም ድጋፍ በማድረግ እንደሚያግዛቸው ሁሉ ይህን በዓል በድምቀት በማክበር፣ የቀድሞው የመቶ ብር ኖት ላይ የነበረውን የአርበኛ ምስል መልሶ በማተም እና በሌሎችም አርበኞችን በሚያስታውሱ ተግባራት እንዲሳተፍ አሳስባለሁ፡፡ አስተያየትዎንም ይጻፉልኝ፡፡ እስኪ በነዚህ ፉካሮዎች እንሰናበት፡፡ ግን ለመጭው ዓመት ክብረ በዓል እንዳትቀሩ! አደራ በምድር አደራ በሰማይ!!! እንበለውና ጉልበት ጉልበቱን እያነከሰ ጨካኙ ጣሊያን ይውጣ ዳገቱን፡፡ የኢትዮጵያ ጀግኖች እኛው መጡ አይናቸው ይመስላል መዳኒት የጠጡ እንደ ሰደድ እሳት እየገላመጡ ለጎጃም ንገሩ ለወሎ ንገሩ ያ ጨካኙ ጣሊያን ተመልሶ ሄደ በመጣበት እግሩ፡፡ ራያ ከፈለው አይምጣ ይቅር ጣሊያንን ገደለው አቤት አቤት ሲል፡፡ ዋቢ ጽሑፎች እና ቃለ ምልልሶች ‹‹ሪፖርተር›› Adwa victory by gallant Ethiopian warriors. 05/03/2014 Robert Wren’s article on www.adefris.info (this site is currentlu suspended) ተድላ ዘዮሐንስ፣ የኢትዮጵያ ታሪክ - ኢጣሊያ በኢትዮጵያ፣ አዲስ አበባ፣ ማንኩሳ አሳታሚ፣ 2004 ዓ.ም. ‹‹አውራምባ ታይምስ››፣ 3ኛ አመት ቁ 113፣ ሚያዝያ 23/2002 ጥላሁን ጣሰው፣ አዳባይ፣ አዲስ አበባ፣ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት፣ 1975 ዓ.ም. ከባላምባራስ በየነ አደለኝ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ፣ ሚያዝያ 10፣ 2006 ዓ.ም መጽሐፈ ትዝታ ዘአለቃ ለማ ሐይሉ ወልደታሪክ፣ መንግስቱ ለማ፣ አ.አ.ዩ. ፕሬስ፣ 2003 ዓ.ም. ፣ አ.አ - ኢትዮጵያ ከመምህራኑ ለማ ሚደቅሳ፣ ሳለአምላክ ጥላሁን፣ አክሊሉ ይርጉ እና ከወይዘሮ እሙዬ አረጋ ጋር በግንቦት 2007 የተደረጉ ቃለ ምልልሶች፡፡

2015 ጁን 22, ሰኞ

Read, Write, Apply and Transform Community!

The Road to Literacy On the afternoon of Friday, 19 June 2015, the head of the Department of English Language and Literature of Debre Birhan University informed me that I was one of the people invited to attend an NGO- meeting the following day. I was surprised to hear that because these days meetings and such educational opportunities have become the gathering places of the officials and their friends. I am a friend of none. The right person on the right occasion! I was told that I would brief the participants about the book club I co - founded and run and the benefit we got from the books Code Ethiopia, the organizer of the event, donated to the university. The department head, as he promised, phoned me in the evening and told me the place and time of the speaking event - Hiwot Hotel, at 8:30 AM, on Saturday. I went there the next morning just in time and found the place ready. “Punctuality is not always the pride of the princes if the world has to drag this country called Ethiopia along,” I thought at the meeting place just a few yards from the former Debre Birhan Palace, where the royal family stayed at when they visited Tegulet. The participants of the day’s event were late to arrive at this place. This is very Ethiopian as some three generations of guests were arriving late. Canadian Organization for Development through Education (CODE Ethiopia) Anyhow, outside a small hall on the fourth floor, posters describing Code Ethiopia’s activities and their outcomes were posted for early comers to devour till the other participants come. “Who we are CODE Ethiopia (CE) is a non-governmental and non-profit making organization working on the establishment of a ‘Literate Environment’ in Ethiopia through development of reading culture. Since its inception in 1994 it has established 97 community libraries in rural districts and trained librarians, library management committee members, supplementary book writers in local languages [and English],editors and local educational newsletter producers.” This NGO that supplied close to three million books to schools in this country for free believes, “If you can learn to read and write, you can learn to do, and be anything. That is the idea behind CODE.” http://www.codecan.org When the program started at 9:30 AM, 30 minutes after the actual schedule, it was Mr. Nema who opened the day’s speaking event by stating its objectives. He said that the generous Canadian philanthropist, Mr. William Bill Burt, visited Ethiopia in 2007 and promised to sponsor an award for a literary contest in Africa. He was motivated to start this after he noticed high school students spoke or understood no English. As a result, through CE he sponsors novels in English written by Ethiopians about Ethiopian life. Mr. Nema stated that CODE had to organize such speaking events in Debre Markos and Debre Birhan towns of the Amhara Regional State to get new writers as there were none involved in the contest from this vast region so far. I say to you, please let us publish Amhara Region! After him, an official from the North Shewa Zone gave a key note address, and afterwards two community librarians from the Oromia Regional State shared their rich experiences about their libraries supported by CE. In Sheno and Fiche towns they have reading weeks, girls’ clubs, paying readers and much more that promote reading and literacy. I wished this was realized at all corners of the nation. The Burt Award for African Literature (BAAL) Next was the time for the Burt Award Winning writers to share their experiences with reading, writing and publishing. In each round CE has been awarding winners and runners-up with modest prizes. The 6th round will be launched in September 2015 and any Ethiopian can involve. The novels that you write should target Ethiopian young adult readers in the age group 12 – 18. Daniel G, one of the winners and a lecturer in Electrical Engineering at Wollo University, had the following to say: Readers are benevolent. People become cruel because they don’t read. Today’s youth has no good understanding. They just discuss European football. This is because they don’t read. Regarding my writing experience, I used to hide, tear or burn what I wrote fearing that people find it. Now I have published thanks to the award. I include in my writing the stories I heard from people in my locality including the story of the shepherd who plays the flute and towards whom a leopard comes to enjoy the music. I had a shortage of books as a child. Kibrom the author of The Revelatoin and a PR practitioner said this: A generation that doesn’t read is a lost one. Reading shaped me. In lower grades, my father pledged to buy me a bike and I stood first. However, when he failed to fulfill that, I stood last. After that, I forgot learning and it was at another time I started to read. Knowledge and wisdom are found in books. WE PRAY TO GOD TO GIVE US FOOD. WE SHOULD ALSO PRAY TO HIM TO LET US READ. I have published 27 children’s books most of which are translations from Amharic into Tigrinya. Code opened my eyes to reading. It has brought readers and writers together. Both authors were asked questions including one that says what they would do with the manuscripts if they were not selected for the prize. They had a very good discussion with us. THE DIAMOND TEACHER When I checked the schedule for the day I found this: Orientation to students and teachers on inspiring students to read literature, 12:00 – 1:10 PM, Ato Messeret. I suspected that the presenter probably must be my former African Literature instructor at Addis Ababa University (AAU). Mr. Nema invited whom he called a diamond teacher at AAU to the stage. Mr. Messeret deserrves this as he inspired thousands of his students and members of the public to read and live a literate life. He never harasses you as most of the others there do. Many an AAU instructor wasted our golden time and planted a hatered towards knowledge and research in most of us. Messeret, on the contrary, is always interesting to be with. He started by telling the audience about his upbringing. He told us that he was a ‘lazy’ student and his lower grade teachers learned to play soccer with his ass. Reading motivations including his non-literate mother who counted the right marks he scored in his notebook were mentioned and acnowledged. Later, she would send him to a local gas seller as an apprentice witnessing that he was weak at numerical skills. I think Messeret has always been the teacher I wanted to come to the class. He said that avid readers from our country contributed to the world through their reading experiences. For instance, demining or mine clearance, according to him, is Haddis Alemayehu’s idea. This renowned author didn’t attend above fourth grade. This sociable lecturer added this: Reading is a university by itself, so everyone should keep reading. We should not beg people to read in a country that has more than 2000 years of writing history. It is a paradox when we hear the other world call us uneducated taking part of their knowledge from our Geez books they looted. We should not be ridiculed as people from whom money should be hid in a book. When we move elsewhere in the world, space exploration is a French writer’s idea. This man of letters wrote that man could move to the moon using a machine he would build. Science has been taking such ideas from literature in this interdisciplinary world. Our mind can process 500 words per minute, so we should give it that much while we read. If we do not give it, it would wander here and there as we are reading. There should be a flow in your reading - you start an idea and shouldn’t move out of it. Then, you will be taken by the idea. True reading is like meditation. Feel the feelings of the characters, and move across the other world through reading. Don’t measure a book in its volume; rather worry how much it appeals to your mind. Teaching English skills would be sentences, yet literature, which promotes critical thinking, is language in context, and it helps you be aware of the culture and language in a wider context. Concerning his reading experience, Messeret says he understood English well after he read fiction at university. They were difficult to him at the beginning. He taught at AAU for 26 years. He told us that literature, which is a liberal subject, is fun to teach and learn. He doesn’t agree on blaming the youth which is taken as a trend from Socrates’ time on. Blaming and denouncing is simple, but building is difficult. I met Mr. Messeret during the tea- break and he shared his various ideas with me and my former classmate, Gebresillase. Our teacher said, “I make myself happy through teaching”. What shocked me is what he said on his suspension from his teaching position. He said he was asked to sign that the department of literature at AAU gets closed. “No I struggled throughout my life for its opening and wouldn’t sign for the closure. The other lecturers as well opposed the query and the administration said I was behind this” he narrates sadly. Let us try for the realization of what Mr Nema said, “We are trying to create the Ethiopian Bill Burt. In additon, our universities should criticize the books we published.” I expressed my gratitude to CODE for the English novels donated to our university. They have been very helpful in our literature class for their familiarity and simplicity. I also suggested that English novels written by Ethiopians including Ashenafi Kebede, Abe Gubegna, Sahlesilase Berhane Mariam and Daniachew worku be published since it is hard to find them in the market nowadays.

2015 ጁን 12, ዓርብ

Rediscover our cave

We have written the itinerary to the cave near Debre Birhan. Please read it and send us your feedback. I hope you and your friends will find it interesting. Thanks! You may share it. DEBRE BIRHAN AREA ITINERARY SITE NAME: Engidwasha TYPE: Natural and historical attraction LOCATION: 90 kilometers north of Debre Birhan. 40 kilometer of it is all weather gravel road which is on a good condition. It is past Tarmaber and Seladingay (Tsadkane). Only 20 kilometres from Seladingay! ABOUT THE SITE: The discovered part of this cave would be the size of a school compound. You should crawl and walk carefully to move from one part of the cave to the other. The hike to the cave takes some 30 minutes down a little steep hill. It is very quiet, tranquil, cold and interesting to be in the cave. Our local delicacies, music, dance and above all the stories the old people narrate about the cave are lively and they make your stay unforgettable. The cave served as a shelter for the whole local community when Fascist Italy invaded the area. There is an emerging story of a massacre on 400 partiots in the cave. The area was the center of the patriotic struggle in the 1930s. Traces of the ancient man, stone tools, are also discovered by an archaeologist researching the cave. Such new bits give a variety to the known sites in the northern route. WHAT YOU NEED: You should come with good shoes that can be used for steep slopes, flashlights, walking sticks and other equipments that you may need to visit this cave. Promoter: Mezemir Girma fb S
egent Ethiopia

The Moja Man’s Friday

In the afternon of Friday, June the 5th 2015, I headed to Adarash Arake, a famous liquor house, in Kebele two of Debre Birhan. Two liters of strong arake, a liquor from Ethiopia, I bought there and headed to the capital, Addis Ababa. On my way, I remembered my grandparents who walked for days all the way from Tegulet to Addis to attend the weddings of their land owner's children. These landowners included Leul Ras Imru and his sisters. After I finished the 130 kilometer journey, I went to Addis Gursha, a restaurant located next to Harmony hotel. The city I knew for the last 12 or so years looks different. I was just unable to find the places I had know easily. Most of the marks I knew were not there, so I had to ask the passers-by for help. Since I was an hour early, I had to wait for the guests and the couple to be wed there at the restaurant drinking soft drink. I had to pay 17 Birr for what cost me 1.50 in 2005 in the same town. In the mean time, guests started to come and chat about the wedding and personal business. As we were sitting in the veranda of Addis Gursha, both Amharic and English music kept flowing to our ears alternately. From PSI Ethiopia’s office located opposite where we were, in wedding dress emerge Erica and Shrunas with their bridesmaids and best men. It was me who saw them first and told the crowd with me about their coming. Soon, we started singing Amharic wedding songs. We got together with them at the main room and then headed to the veranda. The Rasta Addis Gursha owner congratulated the couple and welcomed us all. Erica’s and Shrunas’s coworkers, peace corps volunteers and other invited guests were there at the wedding. In my culture, Friday and June are not believed to be good for weddings to take place. That was why some of my friends did not believe me when I told them that I was going to a wedding. It is believed that the couple would not enjoy a happy life. However, I wish that these two enjoy life to the brim and accomplish their hearts’ wishes. The people drank what was provided and even some of them tasted my Debre Birhan liqor. I didn’t reserve a room, so I had to leave early. I left after a few hours to look for a room. A young man I met on the road showed me where to find and I found one. Again, I wish Erica and Shrunas a happy time together!

2015 ሜይ 14, ሐሙስ

ጥቁር እንዴት አገሬ ብሎ ይዋጋል?

አርብ ሚያዝያ 30፣ 2007 ዓ.ም. በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ቆይታዬ እጅግ ድንቅ ትምህርት ከወሰድኩባቸው መድረኮች አንዱ የነበረው በታሪክና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል ፊትአውራሪነት የተዘጋጀው ትምህርታዊ መድረክ የተካሄደበት ነበር፡፡ ሰዉ ሁሉ ‹‹እንዲህ ነው ምሁራን ማለት!›› ብሎ ያደነቃቸውና እንኳን መመራመርና ማወቅ ለሚፈልግ ቀርቶ ስለ ዕውቀትና ምርምር መስማት እና ማድነቅ ለሚፈልግ ሰው አርዓያ የሆኑ ተመራማሪዎች ጥልቅ ትምህርት የሰጡበት ቀን ነበር፡፡ የዚህ መድረክ ስያሜ ‹‹የአርበኞች ቀን መታሰቢያ አውደ ጥናት›› ሲሆን ሶስት ጥናቶች ቀርበውበታል፡፡ በጥናቱ የተገኙት 90 በመቶ የሚሆኑት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ሲሆኑ የተቀሩት ከባህል ጽ/ቤቶች የመጡ እንግዶች፣ የሰሜን ሸዋ አርበኞች ተወካዮች እና የዩኒቨርሲቲው መምህራንና ሰራተኞች ነበሩ፡፡ በየማስታወቂያ ሰሌዳው ላይ የማስተዋወቅ ስራ ቢሰራም ይህ በየትምህርታዊ መድረኩ የሰው መታጣት ችግር ሊለቀን እንዳልቻለ ግልጽ ነው፡፡ መፍትሔ ማፈላለግ ግድ ይለናል፡፡ የመጀመሪያው አቅራቢ የነበሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ ሲሆኑ የእርሳቸው ገለጻም ለጥቀው ለሚያቀርቡት ለኢያን ካምቤል ጥሩ ዳራ አስቀምጦላቸዋል፡፡ Mapping Collaboration and Resistance in Africa Orientale Italiana 1935-1941 የሚለውን ወረቀት ፕሮፌሰሩ ከማቅረባቸው በፊት ለአካዳሚክ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ከህዝቡም ጋር ለመነጋገር ዕድል የሚከፍት በመሆኑ ደስ እንዳላቸው በመናገር ነበር የጀመሩት፡፡ ከዚህ ቀጥሎ ከአውደ ጥናቱ የወሰድኩትን ማስታሻ በቅድሚያም የፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለን በአጭሩ አቀርባለሁ፡፡ አርበኝነትን ያለ ባንድነት ወይንም ለጣሊያን ከተደረገው መተባበር ውጭ ሙሉ ለሙሉ ልንረዳው አንችልም ያሉት ምሁሩ በ1928 ዓ.ም ጣሊያን ከኢትዮጵያ እጅግ ያየለ ዝግጅት እንዳደረገችና ኢትዮጵያም በነበራት አቅም ወረራውን እንዴት ለመቋቋም እንደቻለች በማስረዳት የወረራውን መልክ አሳይተዋል፡፡ ከ300 000 በላይ ጦር ወደ አፍሪካ ከጣሊያን ጊዜ ወዲህ ተልኮ የማያውቅ ሲሆን ጣሊያንም ይህንን ሁሉ ወታደር የላከችው አንድም የአድዋው ሽንፈት እንዳይደገም በመፍራትና ሁለትም የቀዳማዊ ኃይለስላሴን ዘመናዊነትና ዝና በመገንዘብ ነበር፡፡ እንደተገመተው የኢትዮጵያም ጦር በቀላሉ አልተሸነፈም፤ ጦርነቱም በአጭር ጊዜ ውስጥ አላለቀ፡፡ 400 ታንክና 300 የጦር ጀቶች የዘመናዊው የጣሊያን ትጥቅ ማሳያዎች ነበሩ፡፡በሰሜን ለመሸነፍ ሰባት ወር፣ በምስራቅ ስምንት ወር ሲፈጅብን፣ በነገሌ ደግሞ አመት ከስድስት ወር ሳንሸነፍ ቆይተናል፡፡ ጣሊያን ደብረብርሃን ሚያዝያ 25፣ ቱሎፋ በተባለች ኮረማሽ አጠገብ ባለች ስፍራ ደግሞ በ26 ገብቶ ሚያዚያ 27 በ10 ሰዓት አዲስ አበባን ይቆጣጠራል፡፡ ይህም በጦርነቱ ተፈጥሮ ላይ የራሱ ተጽዕኖ ነበረው፡፡ የጣሊያን መንግስት በኢትዮጵያ ተብሎ መታወጁ የብዙውን ሞራል ሰብሯል፡፡ ከዚህ ጊዜ በኋላ ከደብረሲና እስከ አዲስ አበባ ባለው መንገድ ላይ መንገዱን የማወክ የአርበኝነት ተግባር ተጀመረ፤ ከዋና ከተማዋ ወደ አዋሽ የሚሄደውን የባቡር መስመርና የፍቼንም መንገድ የመዝጋት ስራ ተጧጧፈ፡፡ በመልሱም መስመሮቹን የማስከፈትና አርበኛውን የማባረር ስራ በጣሊያኖች ተጀመረ፡፡ አርበኝነቱ ቤተክርስቲያን የነበረችበትና ሰፊ መሰረት የነበረው ነበር፡፡ እንደማሳያም አቡነ ጴጥሮስ የነበራቸው አስተዋጽኦ ይገለጻል፡፡ እኝህ መንፈሳዊ ሰው ከደብረ ሊባኖስ ጋር በእጅጉ የተቆራኙ ነበሩ፤ እዚያም ይኖሩ ነበር፡፡ አዲስ አበባን ለመቆጣጠር የተጠራውንም ስብሰባ በገዳሙ መርተው ነበር፡፡ በ1928 ሃምሌ ላይ አርበኞቹ አዲስ አበባን ነጻ ለማውጣት ሞከረው የነበረ ሲሆን አቡነ ጴጥሮስም ይህ ሙከራ ከሽፎ ይገደላሉ፡፡ ምዕራብ ኢትዮጵያ ላይ የራስ እምሩ የጎሬው መንግስታቸው ፍልሚያውን ሲያካሂድ ቆይቶ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ራሳቸው ራስ እምሩ ተማርከው ወደ ጣሊያን ይወሰዳሉ፡፡ የጣሊያን ጦር ዋነኛ ተግባራትም የሸዋን መስመሮች ማስለቀቅ፣ የራስ ደስታን ጦር ማጥፋትና የጣሊያንን መንግስት የሚደግፉትን ማፈላለግና ግንኙነት መፍጠር ይሆናል፡፡ የራስ እምሩና የጥቁር አንበሶች መያዝ አንድ ጉልህ ሂደት ነው፡፡ በየካቲትም ወር ግራትሲያኒ መስመሮቹን ስላስለቀቀ አሸንፈናል የሚል ስሜት መጣበት፡፡ ለወራሪው የነጭ ጦር የሚደረገው ትብብር ሁለት መልክ ነበረው፡፡ ይኸውም አንድም ግለሰቦች እንደራስ ሃይሉ ራሳቸው የሚያደርጉት ትብብር ሲሆን ሌላውና ብዙ ሰዎችን የሚካትተው ግለሰቦች ማህበረሰባቸውን ይዘው የሚገቡበት ሂደት ነበር፡፡ በሁለተኛው መንገድ የሚገቡት ባላባቶች በአፋርና በሰሜን ነበሩ፡፡ ለወራሪዎቹ መተባበሩ በነዚህ ስፍራዎች ብቻ ሳይወሰን ድፍን ሸዋ፣ ጎንደር፣ ላስታ፣ ጎጃም ባንዳ ነበር አሉ፡፡ ለአገሩ የሚዋጋ በየስፍራው መኖሩ ግን መዘንጋት የለበትም፡፡ ሰፊ የማግባባት ስራ ከተሰራ በኋላ የወላይታ፣ ጅማ፣ ከምባታ እና ሃድያ ባላባቶች ለጣሊያን ሊተባበሩ ቻሉ፡፡ ለዚህም ትብብር የዳረጋቸው የጣሊያን ፖሊሲና ውትወታ ነው፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ ማለት አማራ የሚገዛት የአማራ አገር ናት›› እያሉ ጣሊያኖቹ ከወለጋ፣ ከኢሊባቡር እና ከፋ ደጋፊዎችን ማግኘት ችለው ነበር፡፡ ኦርቶዶክስ ነው የሚገዛችሁ በማለትም ይህንን ያገኙትን ድጋፍ አጠናክረውታል፡፡ ከሸዋ ውጭ የነበረውን አማራ ደግሞ ሸዋ ነው የሚገዛችሁ እያሉ ለመከፋፈል ቢሞክሩም አልተቻላቸውም፡፡ የሆነው ሆኖ ከየካቲት 1929 እስከ 1933 ጣሊያኖች በአንጻራዊነት በሰላም የሚያስተዳድሩባቸው ጊዜያት ነበሩ፡፡ ለኘጮቹ የተደረገውን ተብብር ስናይ ባንዳዎች የራሳቸውን ታሪክ ስላልጻፉና ባንዳነታቸውንም ከነጭራሹ ደብቀው ስለተቀመጡ የእነርሱ ታሪክ ያልተሟላ ነው፡፡ በጣሊያኖች በኩል ለተባበሯቸው ኢትዮጵያውያን በሮማ ያደረጓቸውን አቀባበሎችና በቤተመንግስት ያደረጓቸውን መስተንግዶዎች ጨምሮ በርካታ ፎቶዎችን እና ካርታዎችን ከአርኪ ገለጻ ጋር ያቀረቡት ፕሮፌሰሩ ያለምንም የጽሑፍ ማስታወሻ ንባብ የሚሰጡት ማብራሪያ አብዛኛውን እስካሁን የማውቀውን ምሁር የሚያስከነዳ ነበር፡፡ በሞሶሎኒ ቤተመንግሰት ፊት ለፊት ለጅማው ገዥ ለሱልጣን አባ ጆቢር ክብር የተደረገውን ደማቅ ሰልፍ አሳይተውናል፡፡ የአፋርና የቆላው ኢትዮጵያ ሰዎች የተደረገላቸውን አቀባበል በክብር ልብስ ሆነው በፊተኛው ረድፍ ቆመው ሲታደሙ አይተናል፡፡ የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ የነበሩት አቡነ ዮሐንስም ተባባሪ ሆነው ሄደው ነበር፡፡ እንደምገምተው አቅራቢው ምሁር ያላቸው የጣሊያንኛ፣ የአረብኛና የግዕዝ ችሎታ ከተለያዩ መዛግብት ያልተዳሰሱትን እውነታዎች ለመፈልፈል ረድቷቸዋል፡፡ የአርበኝነትን እንቅስቃሴ በተመለከተ ግራትሲያኒ አጠፋዋለሁ ሲል አልሆነለትም፡፡ በውጭው ዓለም ጥቁርና ኋላ ቀር ህዝብ እንዴት ለአገሩ ይዋጋል የሚል አስተሳሰብ ነበር፡፡ አገሬ ኢትዮጵያ የሚለው ግንዛቤ ግን ለብዙ ዘመን ለሺዎች አመታት የቆየ ሲሆን ንጉስ ኢዛና ነበር ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያ የሚለውን በደብደቤው ውስጥ የተጠቀመው፡፡ መጀመሪያ መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ግዕዝ ሲተረጎምም ኢትዮጵያ የሚል ቃል ተጠቅመዋል፡፡ ከአረብኛ ወደ ግዕዝ የተተረጎመ ገድል ላይም ኢትዮጵያ አለች፡፡ ከዚያ ዘመን ወዲህም በ13ኛው ክፍለ ዘመን ላይ ይህንኑ ቃል ተጠቅመውት እናገኘዋለን፡፡ በአረብኛ አበሻ የሚለውን ወደ ግዕዝ ሲተረጉሙ ኢትዮጵያ እያሉ ነው፡፡ በግዕዝ ትርጉሙ ላይ አበሻ የሚል የለም፡፡ ስለዚህ ለመንደራቸው፣ ለቀያቸው አለያም ለዘመዶቻቸው ብቻ ሳይሆን ለሃገራቸው የሚቆሙ አርበኞች መኖራቸው ለወራሪዎች እውነታውን ከጠበቁት በላይ አድርጎባቸዋል፡፡ አርበኞችንም አግባብቶ ወደ ጣሊያን ለማስገባት እልህ አስጨራሽ ጥረቶች ይካሄዱ ነበር፡፡ እንደ ምሳሌም በሞሶሎኒ ጥያቄ አበበ አረጋይ ከኢጣሊያ መንግስት ጋር እደራደራለሁ ይላሉ፤ ይህን የሚያደርጉትም ጊዜ ለመግዛት ነው፡፡ የትምህርት ደረጃቸው ስምንተኛ ክፍል ስለደረሰ የውጭ ቋንቋና ጂኦግራፊም ጭምር ስለሚያውቁ የሁለተኛውን የዓለም ጦርነት መከሰትን ይገምቱ እና ይጠባበቁ ነበር፡፡ ሞሶሎኒም ለእንደራሴዎቹ ወይ ተዋግታችሁ አሸንፉ ወይንም ለቃችሁ ውጡ ይላቸዋል፡፡ ከራስ አበበ ወገን ፊታውራሪ ወንድምነህም ለድርድር መጥተው ፎቷቸው ይታያል ፕሮፌሰሩ ባቀረቡልን ትዕይንት ላይ፡፡ ከዚህ ቀጥሎ በዓለም ሁኔታም መቀያየርና በነበረውም የሃይል አሰላለፍ መሰረት ሁኔታዎች ሁሉ ለጣሊያኖች ይገለባበጡባቸዋል፤ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ባዳ የነበረውንም ጨምሮ የመቀመጫ መርፌ ይሆኑባቸዋል፡፡ የእንግሊዞች መምጣት አስተዋጽኦ ማድረጉ አይናቅም፡፡ በእንግሊዞች እገዛ ያደረግነው የ1933ቱ ጦርነት የነጻነት ጦርነት ሳይሆን የመጫረሻው ጦርነት መባል አለበት፡፡ ምክንያቱም ከዚያም በፊት በርካታ ጦርነቶች በየጠቅላይ ግዛቱ ስለነበሩ ነው፡፡ ከጥር እስከ ሚያዚያ 1933 ጣሊያን አለቀለት፡፡ ይህም የሆነው ህዝቡና አርበኞች እንደገና ስለተነሱ ነው፡፡ ባላባቱ ሁሉ ወደ አርበኝነት ይገባ ያዘ-- በደቡብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን በሁሉም ቦታ፡፡ ቀጥሎ ምርምራቸውን ያቀረቡት ኢያን ካምቤል ሲሆኑ ምርምራቸውም የሚያጠነጥነው በደብረሊባኖስ ግድያ ላይ ነበር፡፡ በዛሬው ዕለት ታሪክ እየሰራን ነው ብለው ነበር የጀመሩት፡፡ ይህ የአሁኑ መድረክ የደብረ ሊባኖሱ ታሪክ ለህዝብ ይፋ የሆነበት የመጀመሪያው ነው፡፡ ጣሊያን ግዛት ያስፈልጋታል፤ ኢትዮጵያም መሰልጠን አለባት የሚል ነበር ጣሊያኖች እዚህ ለመግባታቸው ያቀረቡት ምክንያት፡፡ ስለዚህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ ስለተፈጸመው ትልቁ ግድያ ብዙም የሰማነው ነገር አለመኖሩ የሚገርም ነው፡፡ ግራትሲያኒ የአዲስ አበባን ከተቆጣጠረ ከሶስት ሳምንት በኋላ የኢትዮጵያ ገዥ ተብሎ ተሾመ፡፡ ግራትሲያኒ በአንደኛው የዓለም ጦርነትና በሊቢያም ተሳትፎ የነበረውና መጥፎ ታሪክ ያለው ሰው ነው፡፡ በአንድ ጊዜ ስምንት ሰው የሚሰቅሉ ተንቀሳቃሽ የሰው መስቀያዎች ኢትዮጵያን በሚያስተዳድርበት ወቅት በየስፍራው ነበሩት፡፡ ግራዚያኒ ደብረሊባኖስ እና ሌሎች የኦርቶዶክስ አብያተክርስቱያናት የችግሩ ምንጭ እንደሆኑ ያምን ነበር፡፡ ስምኦን አደፍርስ፣ ሞገስ አስገዶምና አብርሃ ደቦጭ ያቀነባበሩት የግራትሲያኒ የግድያ ሙከራ ሳይሳካ ቀርቶ ህዝቡን ለማስጨፍጨፍ በቃ፡፡ የሞቱትን ከአዲስ አበባ ለማውጣት በ100 የጭነት መኪናዎች አራት ቀን ወስዶባቸዋል፡፡ ግራዚያኒ የግድያ ሙከራ ከተሞከረበት ጊዜ ትንሽ ቀደም ብሎ በዕለቱ በሚያዘጋጀው ዝግጅት ላይ አቡነ ቄርሎስ ቀርተውበት ሲጠባበቅ የሚያሳይ ፎቶ አይተናል፡፡ እርሳቸውም አሞኛል አልመጣም ብለው ሀኪም ልኮ ጤንነታውን አረጋግጦ በግዴታ አምጥቷቸዋል፡፡ ችግር ሊኖር እንደሚችል ሰው ነግሯቸው ነበር ማለት ነው፡፡ የችግሬ ምንጭ ነው የሚለውን ገዳም የደብረሊባኖስን ለማውደም የሚያዝ ሰነድ አዘጋጅቶ የነበረው ግራትሲያኒ በገዳሙ ያሉትን ካህናትና ምዕመናን ለመግደል ዕቅድ ሲወጣ ከረመ፡፡ ግንቦት 12 ቀንም የአቡነ ተክነሃይማኖት ንግስና የሚካኤልም በዓል ቀን ስለነበር ተመረጠ፡፡ ለንግስ የመጣውንና ሁሉንም ህዝብ ቤተክርስቲያኑ ግቢ ውስጥ አስገብተው ደብቀው ባስቀጧቸው መኪኖች እየጫኑ ወስደው ገደሏቸው፡፡ ግራዚየኒ 452 ሞተ ብሎም ይፋ ቢያደርግ እንኳን ከ1800- 2200 ሰው ተገድሏል፡፡ ከደብረ ሊባኖስ የተረፉትን ወደ ስምንት መቶ የሚጠጉ ሰዎችም ደብረ ብርሃን ያመጧቸዋል፡፡ ከዚያም ወደ አንኮበር መስመር እንግጫ የሚባል ስፍራ ላይ ወስደው በምስጢር ጉድጓድ አስቆፍረው ገድለው እንደቀበሯቸው የሚያስረዱ የአይን ምስክሮችን ጭምር አነጋግረዋል ተመራማሪው፡፡ ከዚያም የተረፉት እዚህ ደብረ ብርሃን ከተማ ጮሌ አካባቢ እንደተገደሉና እንደተቀበሩ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህራን የሆኑት አለባቸው በላይና ቴዎድሮስ ስዩም በዕለቱ ባቀረቡት ምርምራቸው አረጋግጠዋል፡፡ ይህን ቦታም ለመንከባከብ እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል፡፡ በደብረ ሊባኖስ የሞቱ ሰዎች ዘመዶችና እነዚያን ሰዎች የሚያውቁ ሰዎች ተጠንተው ከሰሜን ሸዋ ተሰብስበው ሶማሊያ ውስጥ ወደሚገኘው ደናኔ እስር ቤት ተወስደው የታሰሩ ሲሆን ብዙዎቹም ሞተዋል፡፡ እነዚህ በሺዎች የሚቆጠሩት ኢትዮጵያውያን የሞቱበትና የታሰሩበት ደናኔ ታሪካዊ ነው፡፡ የደናኔ የማጎሪያ ካምፕ ከ75 ዓመታት በፊት ነበር የተከፈተው እዚያ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ተገድለዋል፡፡ ግራትሲያኒ የሰራው ግፍና በደል ተደብቆ ቆይቶ አሁን ድረስ ተመራማሪዎችም ሳይገነዘቡት መቆየታቸው ምክንያቱ አንድም እርሱ ራሱ ነገሮቹን ሁሉ እንደዚህ በድብቅ መስራቱ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ሰዎች ምንድነው እንደዚህ ክፉ የሚያደርጋቸው ከተባለ በማህበረሰብ ያለውን ሁሉንም ነገር ማላመድ ይቻላል፤ ሰውን መግደልንም ማለማመድ ይቻላል፡፡ ጀግናን ማወደስን ተምረንዋል፡፡ ዶሮ እንደመግደል ነው ብሎ ማስተማር፤ ልጆች የአርበኞችን የተቆረጠ ራስ እንዲይዙ ማድረግ መጥፎ ነገር ሰርተው ምንም እንደማመጣባቸውና ተጠያቂነት እንደማይኖር መንገር ነው መላው ብለዋል ኢያን ካምቤል፡፡ የእንግሊዝ መንግስት ኢትዮጵያ ጣሊያንን ወደ ፍርድ አደባባይ እንዳታወጣ ያደረገው ታሪካዊ ውሳኔ ዘርፈ ብዙ መንስኤዎች ነበሩት፡፡ በመጀመሪያም ሃገሪቱ እንድትወረር እጃቸው ስለነበረበትና በሌሎችም ስሌቶቻቸው ኢጣሊያን ማገዙን ወደውታል፡፡ በእኛ ሀገር በኩል የንጉሰ ነገስቱ መንግስት መጠነኛ እገዛ ቢደረግለትም ያ በቂ አይደለም የሚሉ እየመጡ ነው፡፡ በእንግጫ ሟቾቹን ለማስታወስ ምንም የተደረገ ነገር የለም፡፡ በደብረ ሊባኖስ ግን የሞቱትን ለማሰብ የተጻፈ የጽሑፍ መግለጫ አለ፡፡ የሚታወሱበትን አይነተኛ ነገር መፈለግ ግድ ይለናል፡፡ አሁን በሰሜን ሸዋ አርበኞችና በዩኒቨርሲቲያችን የታሪክ ምሁራን እየተሰራበት ያለው የደብረ ብርሃኑ መታሰቢያ ከዳር ቢደርስ ቀጣይ የሸዋ አርበኞችን ማፍራት እንደሚቻል እምነቴ ነው፡፡ በአውደ ጥናቱ ዕለት ከሸዋ አርበኞች ማህበር የመጡት አራት ሃላፊዎች በመርሃ ግብሩ የታደሙ ሲሆን ገና ወደ አዳራሹ ሲገቡ ተማሪውና ታዳሚው ተነስቶ በጭብጨባ እና በደስታ ነበር የተቀበላቸው፡፡ ባላምባራስ በየነ አደለኝም በወታደራዊ ሰላምታ ህዝቡን አመሰገኑ፡፡ የዚህ ዘመን ወጣቶች ታሪካቸውን ለማጥናት ባላቸው ትጋት እጅግ እንደተደሰቱ ተናግረው በ93 ዓመታቸው ይህን በማየታቸው ደስታቸው እጥፍ ድርብ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም የታሪክ ትምህርት በየመድረኩ የሚሰጥበት ዕድል ቢመቻች ሁላችንም ስለማንነታችን እንድናውቅና የአሁኑንም ሆነ የወደፊቱን ህይወታችንን በተሻለ ሁኔታ እንድንመራ ስለሚያስችለን እንደዚህ ዓይነት መድረኮች ቢጠናከሩ ጥሩ ይሆናል በሚል እርስዎንም ስለሰጡኝ ጊዜ እያመሰገንኩ ልሰናበት፡፡

2015 ሜይ 10, እሑድ

SIX HOURS AT MENDIDA

IRRESISTIBLE INCONVENIENCES In this country where life is totally unpredictable, by the time I arrived at the taxi stop in Tebase, the neighborhood I live in, there were no Bajajs, small three-wheel Indian made vehicles, with vacant seats on the road to take me to the bus station. As I was standing waiting for a Bajaj, I saw three young men who were turning their backs time and again, and that made me suspect that something was going wrong in that direction. It was roughly 6:30 AM. A moment later, I discovered that DeShantell (D.) Singleton of Georgetown, SC, was standing at the roadside behind the young men. I went there and met this straightforward woman in her early thirties. She carried a bag on her back and put a rather huge one on the ground. I could see that she was quite disturbed when she told me that a middle-aged mentally retarded man I saw earlier pass by me was annoying her by his stream of gibberish. She told me that she saw him wandering on the road before that day. I also knew that he was physically very weak and incapable of harming a fly. I told her that I was sorry about what had happened, yet she looked inconsolable. “D. it is like you are going back home to the USA with this big bag here,” I said trying to avert her attention. Unfortunately, that failed me as she responded, “I wish I were!” Why wouldn’t the people around her tell that man to go away! How could they be so indifferent? When I said that I felt sorry about the problem my countryman inflicted on her, she told me that she was rather the problem and would be back home in no time. (I met some locals who believe that PCVs are here only for their country’s benefits, so they might feel that D.’s response here was right. As to me, she is an asset for the school and community here in Tebase.) A woman of no worlds! Back home, America is also full of troublemakers when it comes to African-Americans’ rights. What a nuisance! “They know that I am a black American, so why won’t they help me?” she complained to the three of her fellow compatriots-cum-colleagues who came walking from the main Bajaj stop. Gebrielle Gueye of Cleaveland, OH, came from her site in Sendafa, 40 kilometers from the capital, spent the night here in Debre Birhan and was to go that morning to Mendida with us. This African- American girl was smoking cigarettes that D. whished had in order that she chases her anger away. I felt a little astounded as it was my first time to see her smoke. Meanwhile, the three kept walking to the bus station, yet we kept scanning the road for the Bajajs. Afterwards, I discovered the reason why there was a scarcity of Bajajs. St. George’s ‘yearly’ celebration was taking place in the other corner of our six centuries old town located 130 kilometers north east of the capital. Management majoring girls whom I am teaching writing this semester were coming from the church in that wee hour of the day. They must be coming from that church spending the entire night attending mass there as it would be impossible to go to the three kilometers distant church that morning. How people are becoming relatively active in their respective religions this decade! On the other hand, I wondered what was going on with party going students at our university. Debre Birhan University (DBU) banned them from going to their favorite night clubs for discipline or cultural reasons. When a Bajaj suddenly turned at the zebra crossing near us, D. jumped into it, put her bag at the back of the seat and murmured “I was here before anyone else.” The driver asked, “How much will you pay for the bag?” and another girl who came running to get into the vehicle complained, “It was me who told him to reserve me a seat!” While I was following D. by another Bajaj after a few minutes, I saw the three PCVs walk. They joined us in an old locally patched up bus at the station. How these buses make me feel sub-human! Living hells! I hate traveling because of you! Drivers in my country have a habit of coming to stations after they are told by their assistants that the buses are full – I think that was why the driver came late that morning. A moment later, we started our trip after waiting for a considerable time. My dear reader, I am going to use a conjunction Americans here say is misused. BY THE WAY, the place we started from is made into a bus station only a few years ago, yet formerly it was a police station. In most of the towns I know in this country, different institutions are swapping their places. How this disturbs me! DUSTY, BUMPY, BUT SCENIC At 7:10 in the morning, on the first day of May, 2015, we set off for Mendida town to attend the storybook festival at the elementary school there. The festival was planned and organized by Benjamin Rearick, an American Peace Corps Volunteer (PCV) who has been serving at the school for two years now. He comes from Kirksville. “What is the festival all about?” you may ask. Find out below! The driver showed his license to go to our destination to an indifferent looking traffic policeman who stopped the bus at Tebase. We went in a detour past the new defense forces vehicle assembly site. This was a navy’s training camp when our country had one. Women embracing children and wearing scarves were in the bus. A young man who spoke Amharic in a Tigrinya accent was sitting beside me. When he stared at Gebrielle, who was sitting opposite him, she felt angry with him and told me to tell him stop it and I followed suit. He told me that he knew many of the districts of North Shewa and he had been to Mendida over the last six months. His job was carrying merchandize around and distributing to shops. For the PCVs, the plastic bag that he carried contained litter. He lived in Addis with two others and moved to North Shewa a few months ago. On an iron box at the back of the driver’s seat sat a young girl, and it was like the driver was carrying her on his back. She was wearing a headscarf and another around her neck. The driver was wearing a light blue shirt and had hair that was not well taken care of. On the front seat sat D. listening to music in a headset that was orange, my favorite color that I began to loathe after ISIS killings of Christians cladding them orange. Next to her sat Dara Weiser of Philadelphia, PA, a PCV at Sheno. Jeff of Los Angeles, CA, was also listening to Gabby's complains about this young man. He wore a surgical mask. Sorry my brother for suffering as such to lift Ethiopia high up! “Tell him that I am not paying extra” shouted D. when the drivers’ assistant carried her bag out to the back box of the bus. Behind us are locals who I can’t tell much about as they are almost the same. It was me who taught DeShantell much Amharic for two months. The only benefit the teaching brought was that the money she paid me, 1640 ETB, was spent on charity at the school she works in. I think I am a bad teacher and the one to blame. Do you remember that a London police officer held the English teacher, Mr. Brown, accountable for what the latter’s English as a Foreign Language (EFL) student, Jemila, did? In the old London Weekend Television (LWT) comedy series, this Asian woman took many items home from a supermarket after she read ‘free’ written on them to indicate that they were free offer. Likewise, D. doesn’t understand any Amharic even if she has been living here for two years. I taught her say the name of her school – Med-Hane- Alem using two English words – mud and honey. Except for the language, she is more of an Ethiopian than an American. A Radio announcer was informing listeners the rights of people organized as it was May Day. That reminded me of what a young daily laborer in my locality said months back: “Couldn’t we work if we were not organized?” The tone this woman-announcer reads is of convincing people. Always she propagates that we do something or not do another. I don’t like such FM radio stations in this country except Sheger FM. After we passed Angolela, the birthplace of Emperor Minellik II, half of the people got off, so some standing travelers got respite. Young school children waved hands to us. They must be going to schools as some rural schools don’t recognize and close schools during public holidays. A few years ago, a Moslem English teacher in my area complained to me how the director of the school he works in pushed him off the veranda of his office as the former was absent on Romedan day! The 27 kilometers gravel bumpy road is not a dead way. I knew the town when I went past it to the Debre Libanos Monastery with my paternal uncle in May 2003 for a week long ‘prayers’. In the town though, there is a three kilometer asphalted road built to prevent trachoma infections. The sight on our way was of meadows, farmlands and eucalyptus trees. The cactus around houses makes the places look green. Cattle and pack animals were grazing. Around newly built and developed springs gather people with their donkeys and jerry cans to fetch water home. Iron-roof and grass huts are where these people live in. The driver’s assistant charged the people who he let into the bus after we travelled more than ten kilometers the same 12 Birr as we did. They are mostly illiterate farmers who can’t argue. I can say he scooped their money out of their pockets. They didn’t regret and it seems that this is the normal condition. Women walking wearing the local dress and carrying long black umbrellas with them bring the daily life of the people into your eyes. Men carrying sticks as is usual in the country on the other hand walk in the narrow winding paths. A man from Angolela got into the bus and he responded to my query on where he was taking the little girl with him. He said he was taking her to a medical place at Mendida. Debre Birhan was rather near to him, but he said Mendida was better in its service. The clinic built in memory of Menelik II at his birth place is no more functional. This man did not visit Fitawrary Gebeyehu’s remains at the church that is in his congregation either. How some people felt indifferent to the hero who died fighting at Adwa in 1986! I know how he is revered by many a local resident. In our conversation, this man told me that under age children work for the flower farm investment there for 20 Birr a day. It is a public property that the investor is given. Ah! Authorities! Off your hands from this densely populated area! Away with such an investment! Where should the cattle graze if investors go there? The acacia on the spurs were like jewels. I wished the meadows people ride horses across a good future. May you get saved from evil eyes! When we arrived at Mendida, four men sitting at the doorstep of a small house were sort of reconciling each other. One of them who seemed to be a high class was wearing a very neat gabbi, while the others were clad with gray ones darkened out of the dusty roads they walk across. THE STORYBOOK FESTIVAL Brittany Sharpless of Kentucky came to the bus station and took us to the school. She came from her site in Wolisso, past Addis, to take part in this event at the school. The school has a big playing ground in front of it. We saw young people playing football and running in the lane. May we see some of these runners in the international arena! Mendida Elementary School has what makes it Oromo. Some of the pictures on the walls are of Aba Gadas and other Oromo icons. Having met some of the teachers and the PCVs who came to attend the festivity, I started to chat with some students by a side of a classroom. To a question I asked her regarding which language was difficult among Amharic and Oromo, an English loving fourth grader whose name was Meron told me that both are simple based on one’s knowledge of the two. When I asked them what they would do if they got 1 million Birr, two students responded me that they would create job opportunities or save it and help their families with it. Meron said that she would open a hospital. The first grader Betty, who I asked about the importance of education, quickly responded that one can’t be a doctor without learning. Asked what their main threats are for the future, the kids responded me that they feared if they would face a shortage of time, fail to study and finally fail pass to the next grade level. The festival kicked off moments after we arrived at the school. The PCVs including Benjamin were busy working. For example, Sarah Brandwood, who comes from New Jersey and who works at Enewary School was writing an illustrated post in both Amharic and English. Lauren Lapointe, Sarah’s site mate, comes from Florida. I feel emotionally attached to her because of all these PCVs she is the only classroom teacher I know. She handles two sections of students at Enewary high school. How lucky would her students be to be educated by this native English speaking girl! A young man who was wearing a nice jacket opened the festival by listing the advantages of reading to the school community in Oromo. I thought that he was a teacher there. Later, I learned that Dinkisisa Temesgen was from Nekemte and at this time he works as an LCF (Language and culture facilitator) for Peace Corps Ethiopia in Addis. At first, I asked myself why this young man who spoke good English had to teach at that elementary school. In the meantime, I knew that I was mistaken. My belief is that any grade level deserves the best teachers, yet the reality is that the smart ones often go high up. I delivered Dinkisisa’s message in Amharic for those who didn’t understand Oromo. After my speech a young man read a children story in Oromo. However, since some teachers suggested that the nice story should also be shared with Amharic speaking students, who according to one teacher constitute more than half the school’s students, the young student re-read the story and Dinkisisa beautifully translated it into Amharic. Messages and announcements were delivered to the students in both Amharic and Oromo, and in my view the school is truly a bilingual environment. A fifth grader girl read the story of the hare and the tortoise in Amharic. This girl uses four legged walking sticks which her mother told me were brought as a gift to her by a German man who lived in the town. Now, though, the sticks are getting shorter as the girl is growing up. I saw another boy walking using crutches. I think his legs were injured by polio. The next activity was in the classrooms and we let the students write stories. I was assigned to grade seven. Both Oromo and Amahric medium students were mixed and I managed to tell them about a story structure and they had about an hour and a half to write and illustrate their stories. They wrote on AIDS, discipline and other areas. Some students who wrote stories they heard before were disqualified. I formed a jury among the students and they selected the five best stories. One problem I faced was the shortage of pens. Most of the students went home to bring pens and didn’t come back. Telling them the previous day to bring pens would work. The school community gave us participants from other places gifts of nice traditional scarves which I am very thankful for! I met a four or fifth grader girl mistaking a picture of an Oromo Abab geda with Aba Dula Gemeda, the current speaker of the Ethiopian House of People’s representative and the former president of the Oromia region. This Oromia is not into the blood of the students yet. I found them more of Ethiopians than Oromos. THE DIVERSE YET ALIENATED PEOPLE Oromo First? This town located in the Abuchuna Nya’a District of the North Shewa Zone of the Oromia Regional State is 180 far away from the center of the zone, Fiche town. The poorly built road makes travelling hard for the people who go there to access services. If it were Debre Birhan, 27 kilometers away, the residents of the district would have a great access to administrative facilities. Ethnic federalism is doing its job there. Interestingly, it is common to see the photos of the legendary bare-foot first African Olympic gold medalist, Abebe Bikila, at the gates of the public offices there. Even if he was not an Oromo by blood, based on what I heard on Sheger FM a few years ago, he is the fruit of Oromia. In addition to this, there is an effort to make the town look Oromo – writing the names of businesses in posters first in Oromo and then in Amharic. How many fought and died for this right? Religious and ethnic diversity is seen at this one kebele small town. Italians were the first foreigners to start working at the town in the missionary they set up during the Italian occupation of the town in 1940s. Some people told me that Mendida is dubbed the nearest town in Ethiopia to Italy since many a Mendida resident went there by the support of the Catholics there. The Orthodox Church at Mendida has been working hard to fundraise for the building of the new St. Mary’s Cathedral. The National Synod via the Fiche Diocese gave the go ahead, breweries sponsor the event and the bazaar, the first of its kind as far as my knowledge is concerned, starts the job. We had a lunch at the bazaar and I met the organizers of the fundraising to have some discussion. Orthodox Christians, Catholics and Protestants have churches in this small town of 5 ooo people. As we started the back trip at 2:45 PM, I asked two of the PCVs about the program before they stuck their ear phones into their ears. Dara told me, “For the children this is an opportunity to do a creative, fun, and interactive activity than just the lesson plans.” She set up a Book Club and a Geography Club at her school. She also brought US Embassy girl scouts and held a community gender discussion at her site. D. who says that she was nervous was the photographer- cum- facilitator for the session. She told me about the festival saying that through story writing they learn how to integrate more than a single piece of art. They also learn how to use their imaginations. They knew not this before. It is a good start. She is also doing a great job at her school and I am a witness of her great job as I sometimes assist her. I arrived at Tebase and had some compiling work on this travel account. When I was walking home afterwards in the evening I heard an old woman say for her mooing cow “You have eaten what you have for today; the remaining hay is for tomorrow.” I learned that not only people but also cattle get famished in this country. I hope that the pictures I took at the school will give you some highlight on the event. I also invite you to read what Benjamin posted today.

2015 ኤፕሪል 20, ሰኞ

For the Ethiopian Christians Murdered in Libya

I have really been saddened to hear what happened to our fellow country men. We have not yet recovered from the pains the South African murderers inflicted upon us; nonetheless, this inhumane deed of the ISIS terrorists has left a big wound in the hearts of many of us. Sooner or later, death comes to everyone of us including these brutal murderers. When death takes your life with a an unbearable pain as to be burnt alive or slaughtered, your death is indescribable! In a situation where you are not attended to by your loved ones, given water to quench your thirst or bread to satisfy your hunger, and even more than that where you are attacked like a wild animal and when no one is able to avenge your death, there crawls sorrow in the correct sense of the word towards your loved ones! May we never hear such sad stories again! Please stop posting the ISIS photos and videos and show your sympathy to the dead and their family!

2015 ኤፕሪል 16, ሐሙስ

በዓል ባይኖር ኖሮ

የበዓል ሰሞን የሚገርም ግርግር ትታዘባለችሁ፡፡ በብዛት ሰዎች የመጎብኘት ልማድ ባይኖራቸውም በዚህ ወቅት ግን ተጓዡ ይበዛል፡፡ በሚገርም ሁኔታ የምግብ ዝግጅት፣ ሽያጭና ፍጆታ ደግሞ ይጧጧፋል፡፡ ራድዮ ጣቢያዎች የማስታወቂያ ውርጅብኝ፣ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፣ የሙዚቃ ግብዣ ብሎም የበዓል ዝግጅቶች ያበዛሉ፡፡ ቴሌቪዥን ጣቢዎችም ልክ ሰሞኑን ኢቢኤስ ከቴዲ አፍሮ ቤት የበዓል ዝግጅት እንደጋበዘን ሁሉ ቀደም ብለው የተቀረጹ ዝግጅቶችን እንካችሁ ተቃመሱ ይሏችኋል፡፡ የበዓል ሰሞን መቼም በአቅም ማነስ፣ ከቤተሰብ በመራቅ፣ በህመም፣ በምግብ አለመመቸትና ሌሎችም ምክንያቶች የሚከፋውም አይጠፋም፡፡ የመገናኛ ብዙሃኑ ደግሞ እነ እከሌ ቤት ይሄ ተበላ ይሄ ተጠጣ የሚለው ማሳበቅ ይረብሽም ይሆናል በተለይ እንዲህ የህዝቡ የኑሮ ደረጃ በተለያየበት ወቅት፡፡ ምንም ቢሆን ግን ስንትና ስንት በዓል ሲያሳልፉ የታዘቡት ብዙ ለውጥና ሁኔታ ይኖራል፡፡ ምንም እንኳን ማስታወሻ የመያዝ ልማዳችን ደከም ቢልም የማይረሱ ገጠመኞችና ትዝብቶች ስለሚኖሩ አንዳንዶቹን እያነሳን ብናወጋ ለሁላችንም ያስተምርና ያዝናና ይሆናል፡፡ ታዲያ ወረድ ብሎ ባለው የአስተያየት መስጫ ላይ እንድተጽፈልኝ ነው ይህን ማለቴ፡፡ በመጨረሻም የሚከተሉትን የውይይት ሃሳቦች እነሆ ልበላችሁ! 1. በጃንሆይ ጊዜ ትምህርት 15 ቀን ለፋሲካ ይዘጋ ነበር ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ ከሞላ ጎደል አሁንም እየተዘጋ ስለሆነ ለምን መንግስት እውቅና አይሰጠውም የሚል ሃሳቤን በትህትና አቀርባለሁ፡፡ 2. የህዝቡ ኑሮ ይሻሻል ዘንድ የሚታትሩ ሰዎች ዓላማቸው ይሳከላቸው ስትሉ ጸልዩ፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለበዓል በግ ቢያርድ ደስ ይላል! 3. የሌላ ሃይማኖት ተከታይ የሆነ ሰው እንኳን አደረሳችሁ ሲላችሁ ምላሹ ምንድነው? 4. እርጥብ ስጋ መብላት ሳይንስና ባህል ከሚጋጩባቸው ተግባራት አንዱ ነው፤ እርስዎ ከሳይንስ ወይስ ከባህልዎ ጋር ተባበሩ? 5.
ብለው አስበው ያውቃሉ? 6. የሌላ ሃይማኖት ተከታዮች በዓላቸውን ሲያከብሩ እርስዎ ምን ይሰማዎታል? 7. በዓል ሲከበር በሰው አገር ሆነው ያውቃሉ? 8. በ2050 የሚከበረውን አንድ ሃይማታዊ በዓል ስታስቡት ምን ገጽታዎች የሚኖሩት ይመስላችኋል? 9. ዘፈን ለራስዎ ወይንም ለሌላ ሰው ለበዓሉ ጋብዙ ቢባሉ የማንን ዘፈን ይጋብዛሉ? ለምን? 10. መጭውን በዓል በተሻለ ሁኔታ ለማክበር ምን ቢደረግ ጥሩ ነው ይላሉ? በመጨረሻም መልካም የበዓል ሳምንት እመኝልዎታለሁ!!!

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...