2018 ጁላይ 28, ቅዳሜ

ለመደሰት ስለማንበብ


ራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት

የዕለቱ መልዕክታችን 21.11.2010


የንባብ ዓላማዎች ብዙ ናቸው፡፡ አንደኛው ለመደሰት ማንበብ ይባላል፡፡ ለመደሰት ማንበብ በብዛት የልቦለድ፣ የግጥምና የተውኔት ንባብን የሚመለከት ነው፡፡ መዳረሻው መደሰት ሲሆን እግረመንገዱን የሚያሳካቸው ንዑሳን ዓላማዎችም ይኖሩታል፡፡ ለመደሰት የማንበብ ዓላማችን ሌላ ንባብን ሲገታብን ግን ለምን ብለን መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ በወሳኝ ሃገራዊ ክስተቶች ወቅት የማይናወጥ ምክንያታዊ አቋም አይኖረንም፡፡  ዕውቀታችን ጎልብቶ በምንማረው የትምህርት ዘርፍ የተሳካልን ሰዎች ልንሆን አይቻለንም፡፡ በሳይንሣዊ መንገድ የተፈተሹ ምርምሮችን ማድረግም ሆነ የተዘጋጁትን በጥሩ መንገድ መረዳት ያዳግተናል፡፡ ምሁርነት፣ አርቆ አሳቢነት፣ አመዛዛኝነትም ሆነ ለወገንና ለራስ ጠቃሚነት የሚመጣው ጠጣሩን ንባብ ስናነብና በዚያም መንገድ እስከሚያስፈልገው የትግበራና የማሰላሰል ጎዳና ስንጓዝ ነው፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...