2018 ሴፕቴምበር 9, እሑድ

በተጋባዥ ፀሐፊ

ደጅ አስጠኒ
(ሳሙኤል በለጤ የፍሬ)
ታሪክ ነክ ወግ
ደጃች እምሩ ቦጋለ ጃንሆይ በትረ-ስልጣን ከጨበጡ(1923ዓ.ም) አንስቶ እስከ ስልጣናቸው ማክተሚያ ድረስ በታማኝነት፣በቅንነት ታትረው ሲያገለግሉ ቆይተዋል። በጃንሆይ ዘመነ መንግስት ብዙ ህጎች ነበሩ ለምሳሌ ንጉሱን ለማግኘት ደጅ መጥናት ካገኙም ብኻላ የራሱ የሆነ የእጅ አነሳስ ስርአት አለው ከሁሉም አስቸጋሪው ነገር ግን ለንጉስ ጀርባ አይሰጥም ተብሎ ወደ ኻላ የመሄድ ስርአት ይተገበር ነበር
*እግሬ የኻሊት መንገዱን ቀጠለ
ማጅራቴም እያደር ዓይን አበቀለ
*ከእራሴ* ብሎ የገጠመም ነበር(ተመላላሽ ባለጉዳይ መሆን አለበት.....!!!) ታዲያ ተለታት አንድ ቀን ጃንሆይ ትልቅ ስብሰባ እንዲደረግ አዘዙ በስብሰባውም ላይ ከፍተኛ ባለስልጣናት እድምተኛ ነበሩ የፅሕፈት ሚኒስተሩ የኪነ ጥበብ ሚኒስተሩን ጨምሮ ተሳታፊዎች ነበሩ የስብሰባው አጀንዳ እንዴት??? <<ኢትዬጵያ ወደ 20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንቀላቅላት የሚል ነበር>> ታዲያ  ደጃች እምሩ በስብሰባው <<የፊውዳል>> ስርአቱን የሚቃወም ነገር ካንደበታቸው አፈትኮ አመለጣቸው። (ካመለጠ .....አመለጠ! የምላስ መለምታ በባሊዚ አይታሽም ወገሻዎች እንዳሉት) ጃንሆይ በጣም ተናደዱ ቁጣቸው ግንባራቸው ላይ ተፅፎ ይነበባል። ደጃች ግምባር ላይ ዓይናቸውን ተክለው ጉሮሮዋቸውን ሞርደው
<<ሰማ እምሩ አየህ......!!! ጃፓን ወደ 21ኛውሺ ስልጣኔያዊ ግስጋሴ ያረገችው ከነ ፊውዳል ስርአቷ ነው።>>
ለማንኛውም እምሩ ከዛሬ ብሀላ <<ደጅ አስጠኒ>> ሆነሀል ሲባሉ ደጃች መብረቅ የወረደባቸው እስኪመስል ድረስ ክው ብለው ደርቀው ቀሩ (ደረቁ......ደረቁ ..አልጠበቁትማ)
ደጅ አስጠኒ ማለት ደሞዝ ወይም ምንም አይነት ጥቅማ ጥቅም የማያገኝ(ስራ እስካል ጀመረ ወይም ወደ ስልጣኑ እስካል ተመለሰ ድረስ) የእለት ተእለት ተግባሩ ተደጃፍ ሆኖ ለንጉሰ ነገስቱ እጅ ነስቶ ማገልገል ለቀለብ የቅርብ ሩቅ ዘመዶቹ የሚሰጡት ማለት ነው። በየለቱ በደጅ ጥናቱ መገኘቱን ማሳውቅ ይኖርበታል። ሆኖም ደጅ አስጠኒው አንዳንዴ <<የተስፋ ጭላንጭል>> ሲኖረው አንዳንዴ ደግሞ ተስፋው ይሟጠጥበታል ታዲያ ይሄ አያደርቅም ያደርቃል...!!! ደጃች እምሩ <<በደጀ አስጠኚነት>>መስራት ጀመሩ ንጉስ ሲያልፋ እሳቸው ለጥ ብለው እጅ ሲነሱ ግርማይነቶ <<1000 ዓመት ይንገሱ>> ንጉስም ዜሮ መርቅ የሚሉ ይመስላሉ(....ካስተያየታቸው) አንዳንድ ቀን እንዳላየ እያለፉ ደጃች ሲሰግዱ ቀናት፣ሳምንታት፣ወራት፣አመታት አለፉ ንጉሰ ነገስቱ ሲያልፉ ደጃች ከጠዋት እስከ ማታ ለጥብለው ሲሰግዱ እንሜያቸው ገፋ ከዛ <<እያጎበደዱ......! እያጎበደዱ.....! እያያያጎጎጎጎጎነበሱ ሄዱዱዱዱዱ>>
አከተመ
ስላነበባችሁልኝ ክበሩልኝ
ነሐሴ 2010

1 አስተያየት:

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...