2018 ኦገስት 12, እሑድ

ጊዜን ፍለጋ! ጊዜ፣ የገባቸው የሚተጉለት፣ አብዛኞች የሚዘነጉት ሐብት … ካለፈው የቀጠለ


ደራሲ - ሊዮን ሆ

ተርጓሚ - መዘምር ግርማ



ክፍል 1፡ ተመራጭ የአሠራር መንገዶችና ጊዜ 

ግለሰቦች አመርቂ ውጤት ለማስመዝገብ ጊዜና ሐብታቸውን ምን ያህል በአግባቡ ይጠቀማሉ?  ቡድኖች ወይንም ድርጅቶችስ ትልልቅ ግቦችን ለመቀዳጀት የሚጠቅሟቸውን ጥሬ ዕቃ፣ የሰው ኃይል፣ ክህሎት፣ ገንዘብ ወይም የአስተዳደር አቅሞቻቸውን እንዴት ይፈጥራሉ ወይም ያሻሽላሉ? እንግዲህ አሁን እኔና እርስዎ የምርታማነት ጨዋታ አንዳንድ ማለት ጀምረናል፡፡ በዚህ ክፍል ብዙ ስራዎችን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት የሚጠቅሙዎትን ሁሉንም ጠቃሚ ብልሃቶች አቀርብልዎታለሁ፡፡   



ስለማለዳ ሥራ ልምድዎ ድብቅ ጉልበት ምን ያህል ያውቃሉ?

አስተማማኝ የማለዳ የሥራ ልምድ መኖር ምርታማነትዎን ለመጨመርና አጠቃላይ ሕይወትዎን ለማሻሻል ከሚጠቅሙዎት ሁነኛ መንገዶች አንዱ ነው፡፡

የኔን (የሊዎን ሆን) የማለዳ የሥራ ልማድ ያየን እንደሆነ ጠንካራ ማሻሻያ ማድረግ ግድ የሚለው ነበር፡፡ እንዴት መሰለዎ? ጠዋት ከእንቅልፌ እንደነቃሁ ዝም ብዬ እየተገላበጥኩ ስልኬን መጎርጎር ብቻ ነበር ስራዬ፡፡ ጥሎብኝ በቃ እንቅልፍ ወስዶኝ ሳለ እንዲያው  ምን አምልጦኝ ይሆን እያልኩ ስፈልግ አረፍድላችኋለሁ፡፡ የእርስዎም እኮ እንደኔ እንደዱሮው ይሆንና ያርፈዋል ማሬ፡፡  ብዙዎቻችን ቀኖቻችንን የምንጀምረው ኢሜልና ማሕበራዊ ሚዲያችንን በማየት ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ጥሩ ልማድ ላይሆን ይችላል፡፡



ባልተtገባ መንገድ ማለዳችንን መጀመር ምርታማነታችንን ሊያነጥፈው ይችላል፡፡ በአንድ ቀን የተለመደው የሥራ ቆይታችን ስምንት ሠዓት ነው፡፡ ይሁን እንጂ ኃይላችን ከሠዓት ሠዓት ከፍ ዝቅ ማለቱን ሁላችንም እናውቃለን፡፡ ቀንዎን ተፍለቅልቀውና በጥሩ አቅም ሊጀምሩ ይችላሉ፡፡ ሆኖም ቀኑ እየገፋ ሲሄድ ትንሽ እንቅልፍ ሊያሰኝዎት ይችላል፡፡ ደህና ጉልበት ባለዎት ሠዓት ውጤታማ ስራ መስራት ግድ ይልዎታል፡፡

አእምሮዎ ስል በሆነበት ጊዜ መስራትን ይልመዱ፡፡

‹‹የማለዳ ስራዎ በሳምንት ከሃያ በላይ ሰዓት ያተርፍልዎታል›› የሚለው የቤንጃሚን ሃርዲ መጽሐፍ ጊዜያችንን በአግባቡ ተጠቅመን ስለምናተርፍባቸው ሁነኛ ዘዴዎች ጠቃሚ ነጥቦችን ያቀርባል፡፡

 ዋነኛው ምክንያት በጠዋት ከምን ጊዜውም በላይ ንቁና ዝግጁ መሆንዎት ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ይህን የምርታማነት መስኮት በደንብ አልተጠቀሙበትም፡፡

ምን ያህል ስራ ሰሩ የሚለው በእርግጥ ምንም ዋጋ የለውም፡፡  የሰሩት ምንድነው የሚለው ነው ቁልፉ ጉዳይ፡፡

አነስተኛ ጥቅም ያላቸውን ጥቃቅን ስራዎች እየሰሩ እሰራዋለሁ ካሉት ዝርዝር ላይ እያንዳንዷን ዝርዝር ጫር እያደረጉ እያጠፉ ስራዎን መጀመር የሚፈታተንዎት ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ ችግሩ ግን ራስዎን ከተጫነብዎት የትንንሽ ስራዎች ተራራ ጥግ እንደምንም ብለው ቆፍረው ባወጡ ጊዜ ድክምክም ብለው ጉልበትዎን የጨረሱበት ጊዜ ይሆናል፡፡ ይህም ትልልቆቹንና በዝርዝርዎት ላይ የበለጠ ጠቀሜታ አላቸው ብለው ያስቀመጧቸውን ስራዎችዎን መስራትን የበለጠ አዳጋች ሊያደርግብዎት ይችላል፡፡

ለአብነት አንድ መቶ የኢሜል መልዕክቶችን ስላዩ ምርታማ የሆኑ ሊመስልዎት ይችላል፡፡ ግን አባተሉዎት ነው መባል ያለበት፡፡ በማለዳ መጀመሪያ አንድ ትልቅ ዋጋ ያለውን ስራ ለመስራት ይቁረጡና ኢሜሉን ለኋላ ያዘግዩት፡፡

ይቀጥላል፡፡

እስከዚያው የእርስዎን ልምድ ያጋሩን፡፡

2018 ኦገስት 11, ቅዳሜ

በኢትዮጵያ ክፉ ቀን ዳር ዳር ሲል


በህዝብ መካከል አላስፈላጊ ጥላቻ እንዳይፈጠር ለመከላከልና የተፈጠረውም ለወደፊቱ መማሪያ ይሆነን ዘንድ ገፃችን አንዳንድ ጉዳዮችን ያነሣል። ገጠመኛችሁን ዘርና ኃይማኖት ሳትጠቅሱ አጋሩን።
ምንጭ: ቃለመጠይቅ
The gathering storm in Ethiopia
Envisioning a scenario where there is no ethnic hatred and to learn from where there was any, we share with you some stories. Please share your stories without mentioning the group that targeted others or those who were targeted.
Source: Interview

"በዚያች አነስተኛ ከተማ ወጣቶች (ዱርዬዎች) በዘሩ ምክንያት ረብሻ በተነሳ ቁጥር ያሽቆጠቁጡት ጀመር። ወደ ትልቁ የክልሉ ከተማ ሸሽቶ ከርሞ ይመጣል። አሁን በግልጽ ባይሆንም ደበቅ እያለ በዚያች ከተማ በስጋት ይኖራል።"
"In that small town the youth target him whenever there was chaos. As a result, he moved to the nearby big town. He comes back when things calm down. At this time he is living by hiding himself."
"የክልሉ ሰዎች ሙሉ በሙሉ መጤ ጠልነት ስለሌለባቸው የአንዱ ከተማ የእግርኳስ ቡድን የከተማችንን ተጨዋቾች ሊደበድቡ ሲሉ የነሱው ቋንቋ ተናጋሪዎች የሌላው ከተማ ሰዎች አዳኗቸው። እነዚያንም ሰደቡ።"
"As it was not all the members of the ethnic group who are xenophobic, when members of one town's football club were about to attack our team, those from the other town but the same ethnic group defended us. They also insulted the attackers."
"ዱሮ ያክመን የነበረው የከተማችን ሥራ ፈጣሪ ሐኪም ንብረት የነበረው ሠው ሐኪም ቤት የፍየል መዋያ ሆኗል። አሣዘነኝ። በዘሩ ምክንያት አሳደውት ጠፍቶ ነው።"
"The clinic owned by the health practitioner who treated us has become a resting place for goats. He flew because they persecuted him for his ethnicity. I felt sorry."
"እናንተ እንደፈለጋችሁ አድርጉኝ እንጂ ከዚህ አልሄድም አለ። ተንበርክኮ ለመናቸው። ቤተክርስቲያን ረጂ ነኝ። ክፉ አላደረኩም አለ። በኋላ በህመም ሲሞት ካገሩ መጥተው አስከሬኑን ዘመዶቹ ሲወስዱት ለምን እንደዚህ አደረጉ ብዬ ገረመኝ።"
"Treat me as you like. I will not go anywhere," said the man and begged them kneeling down. He said he helped churches and did nothing to harm them. I felt confused when his relatives took his corpse to where he was born when he died of natural cause."

2018 ኦገስት 8, ረቡዕ

ሁሉ አማረሽን ‹ኢንተርኔት› አታውጧት፡፡

መዘምር ግርማ
የእንግሊዝኛ ሥነ-ጽሑፍ መምህር፣ ተርጓሚ፣ የራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት መስራችና ባለቤት፡፡
ይህ ጽሑፍ በአምስት መቶ ቃላት የተቀናበረና በሦስት ደቂቃ ውስጥ ተነቦ የሚያልቅ ነው፡፡

እንደ ሕዋ?
አሁን መንፈቀ ሌሊት ሲሆን፤ ደብረብርሃን በሚገኘው ቤቴ ሃሳቦቼን በጽሑፍ እያሰፈርኩ ነው፡፡ ከተወሰኑ ሠዓታት በፊት እንደ ኢትዮጵያ ሕዋ ሳይንስ ማህበር ከፋይ አባልነቴ የደብረብርሃኑ የቅርንጫፍ ማህበራችን ሊቀመንበር መምህር ግዛው ብርሃኑ የሰጠኝን ኮስሞስ የሚል ስለ አጽናፈ-ዓለም የሚያትት ዘጋቢ ፊልም እያያሁ ነበር፡፡ ከዚህ ፊልም ጋርም የሚያያዝ መልዕክት ላደርስዎ ግድ አለኝ፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ ኢንተርኔት ወይም በይነ-መረብ እንደ አጽናፈ-ዓለም ባይሆንም ለኛ ግንዛቤ አጽናፈ-ዓለም መሰል ሰው ሰራሽ ትስስር ነው፡፡ እኔና እናንተ ምንም ብንጥር ከአራት በመቶ በላይ የኢንተርኔትን ግዛት መዳሰስ አይቻለንም ይባላል፡፡ ከጥቁሩ (96 በመቶው) ክልል መግባት ፈጽሞ የተከለከለ ነው ይባላል፡፡ ያስቀስፋል፡፡
የሰው ልጅ መጻፍ ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ አንድ መቶ ሰላሳ ሚሊየን መጻሕፍትን ጽፏል፡፡ እኛም ይህንን ማንበብ የምንችል አይደለን፡፡ ከዚህም ውስጥ በዚህች ባለችን እውቀትና ችሎታ በየስድስት ወሩ በየቋንቋው በእጥፍ ከሚጨምረው የመረጃ ቋት ስንቱን ማየት ይቻለናል? የጽሑፍ ብቻ አይደለም፤ የምስል፣ የድምጽ፣ የቪዲዮና ከዚህም ውጪ ሠነዶች አሉ፡፡ ዓለም እንዴት አንደዋለች በቪዲዮ የሚቀጸውን ጉግል ኧርዝን እንኳን ስንት ሆነን እንበረብረው ይቻለናል?

ሁሉ አማረሽ?
በእርግጥ እትዬ ሁሉአማረሽ የሚሏት ቆንጆ ተወልጄ ባደኩባት ሳሲት ከተማ አልነበረችም፡፡ እኛ ሰፈር እትዬ ሁሉ ግርጌሽ ነበረች፡፡ ሌላዋ ደግሞ አገሬው ስሟን መጥራት ስለማይችል ‹ሁሉ አገርሽ› የሚላት በሠማይ የምታልፍና ባስፈለጋት ቦታ ማረፍ የምትችል ፍጥረት አለች - ሄሊኮፕተርን መሆኗ ነው፡፡ ሁሉ… ሁሉ… ሁሉ… እያልን ስንሄድ እናንተም አገር የማትጠፋው ሁሉ አማረሽ ነች፡፡  ገበያ ወጥታ ያገኘችውን ዕቃ ስትነካካና ዋጋውን ስትጠይቅ የምትውል ቅንጡ እመቤት! ሁሉም ስለሚያምራት አንዱም ለየት ብሎ አይታያትም፤ አያረካትምም፡፡ ብዙ ቀን ስትመርጥና ሰው ስታደርቅ ውላ ሳትገዛ ትገባለች፡፡ ከስንት አንዴ ገዛችም ከተባለ የረባ ነገር ገዝታ አታውቅም ይባላል፡፡ መጣች ከተባለ ነጋዴ ሁሉ ስራዋንና አድራጎቷን ስለሚያውቅ ይማረርባታል፡፡ ታዲያ አንድ ነጋዴ ለቤተሰቦቿ ‹‹ሁሉ አማረሽን ገበያ አታውጧት›› ብለው ነገሯቸው፡፡ ስሟም ሁሉ አማረሽ ሆኖ ቀረ፤ እሷም ገበያ መውጣት ተወች፤ ቤተሰቧም ይሆናታል ያሉትን እቃ በጥንቃቄ መርጠው ገዝተው ያመጡላት ጀመር፡፡ ከዚያ ወዲህ ከበፊቱ የተሻለ ምርጥ እቃ ትጠቀም ጀመር፡፡ እድሜ ለቤተሰቦቿ፡፡ ግን እስከመቼ በሰው ተመርጦላት ትገፋዋለች?

ሁሉአማረሽ ኢንተርኔት ትጠቀም ጀመር፡፡
ያቺ ሁሉአማረሽ ትምህርቷን ጨርሳ ኢንተርኔት ትጠቀም ጀመር፡፡ ታዲያ ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይተውም እንደሚባለው ሆነና ያ ችግር መልኩን ለውጦ መጣላት፡፡ እንደሚከተለው እንይላት
ሀ. አንዱን ለመምረጥ የመቸገር ነገር አልለቅ አላት፡፡ ስትነካካና ከስፍራ ስፍራ ስትዘዋወር ትውላለች፡፡ ከድረገጽ ድረገጽ ትሄዳለች፡፡ ለሳይንስ፣ ለቴክኖሎጂ፣ ለፍልስፍና፣ ለዕውቀት ምናምን ቦታ አትሰጥም፡፡ የተለያዩ ጆርናሎችንም ሆነ የምርምር ተቋማትን አትቃኝም፡፡ አንድ ገጽ ላይ ስትገባም በሚያረካ መልኩ አታየውም፡፡
ለ. እንደ ገበያው ይህ የቴክኖሎጂ ገበያ ለየት አድርጎ የሚያወጣላት የምትፈለገው ገጽ የለም፡፡ ዓይኗ ገብቶላት ጊዜ የምታሳልፍበት የለም፡፡ ለብ ለብ ስታደርግ ትውላለች፡፡ የአእምሮ ኳሸርኳር ይዞሻል የሚሏት አሉ፡፡ በልቅምቃሚ መረጃ ስለተሞላች ያወቀች የሚመስላት ጊዜ አለ፡፡
ሐ. ገበያ ላይ ሰው ማድረቋ እዚህም አልቀረም፡፡ በቻቱ በምኑ ሰውን ተደርቃለች፡፡ በመሆኑም ሰዉ ይማረርባታል፡፡ ጊዜ ሰጥታ ብትሰራና ስራዋን አንድ ቀን ቁጭ ብላ ብትገመግም በሙሉም ባይሆን በከፊል ባሻሻለች ነበር፡፡
መ. አንድ ቀን ገበያ መውጣት የምትተው ትመስላለች፡፡ ገዢ እንጂ ሻጭ እንዳልሆነች ይታወቃል፡፡ ገበያ የራሷን የምታወጣው የላትም፡፡ ሰው በጻፈው ላይ ሃሳብ ለመስጠተ ትጣጣር ይሆናል፡፡ አንብባ ትጨርሰውም አትጨርሰው የሆነ ነገር ትላለች፡፡ የራሷግን ምንም የላት፡፡
ሠ. ከእንግዲህ እሷ ይህን መድረክ ወይም ገበያ ስላልቻለችበት በልጅነቷ እንደነበሯት ወላጆች ሁሉ የሚያስፈልጋትን መርጠው የሚያመጡ ሰዎች ስለሚያስፈልጓት በራስሽ ኢንተርኔት ዘንዳ ድርሽ አትዪም ተብላለች እላችኋለሁ፡፡ ጊዜ፣ ገንዘብ፣ ብዙ ሃብት አባከነቻ፡፡ ከሁሉ አገርሽ የምንማረው ነገር ብዙ ስለሆነ ሁላችንም ሃላፊነት የተሞላበት ስራ እንስራ እላችኋለሁ፡፡



     



ጊዜን ፍለጋ ! ጊዜ፣ ብልሆች የሚተጉለት፣ ደካሞች የሚዘነጉት ሐብት


ደራሲ  - ሊዮን ሆ
ተርጓሚ - መዘምር ግርማ

ዕቃን ወይንስ ጊዜን እንግዛ?
በጣም የሚፈልጉትን ነገር ለመጨረሻ ጊዜ የገዙበትን ወቅት ያስታውሱ፡፡ ቆይቶ ምን ተሰማዎት? መቼም ተደስተዋል፡፡ አሁንስ ሌላ በእውነት የሚፈልጉት ነገር አለ? አዲስ ላፕቶፕ፣ ስማርት ስልክ ወይንም አዳዲስ የወጡ ምርጥ ምርጥ ልብሶች? የፈለጉት ዕቃ ምንም ይሁን ምንም እሱን መግዛት ደስታን ያጎናጽፍዎታል፡፡ በመጨረሻም እቃውን በእጅዎ ሲያስገቡ እስኪ ልሞክረው ወይም ልጠቀምበት ብለው በማሰብ ይደሰታሉ፡፡ ምናልባት ‹‹ገንዘብ ደስታን አይገዛም›› የሚለውን ብሒል ሰምተው ይሆናል፡፡  አዎ! ለጊዜው ያንን የምንፈልገውን ነገር ስንገዛ ደስተኞች ልንሆን እንችላለን፡፡ ይሁን እንጂ፡-

ይህ ደስታ የእውነት እንዳይመስልዎት
የሰው ልጆች ጊዜያዊ ደስታን መፈለጋቸው ተፈጥሯዊ ባህሪያቸው ነው፡፡ ‹ጊዜያዊ ደስታ› የሚለውን አገላለጽ ምናልባት ለመቶዎች ጊዜያት ሰምተውት ይሆናል፡፡ የምንፈልገውን ነገር በፈለግነው ቅጽበት ማግኘት ማለት ነው፡፡ ይህ የ‹ጊዜያዊ ደስታ› ፍላጎታችን የመጣው በምድር ላይ ራሳችንን ለማቆየት በምናደርገው ጥረት ምክንያት ነው፡፡ እዚህ ጋ ዓላማዬ ስለ ጊዜያዊ ደስታ በዝርዝር ለማውራት አይደለም፡፡

‹ጊዜያዊ ደስታ›ን ፍለጋ በሰዎች ልጆች ተፈጥሮ ያለ ቢሆንም እኛ የምንኖረው በ‹ዘገየ ደስታ› በሚመራ ማህበረሰብ ውስጥ ነው፡፡ የ‹ዘገየ ደስታ› የሚባለው አንድን ነገር ፈልገን በፈለግነው ሠዓት ማግኘት ሳንችል ስንቀር የሚከሰተው ነው፡፡ ደሞዛችን እስኪከፈለን፣ በምንወደው ምግብ ቤት ምግብ እስክንበላ፣ ወይም በትልቅ ሆቴል ቡና እስክንጠጣ በትዕግስት እንጠባበቃለን፡፡ የፈለግነው ነገር ሲደርስ ደግሞ በጣም እንደሰታለን፡፡

ይህንን ነገር ጥበቃ የናፈቅነው ናፍቆት፣ የነበረን ምኞት ወይንም ይህ የዘገየው ደስታ ራሱ ስናገኘው ከሚሰማን በላይ ስሜታችንን ይነካዋል፡፡ ይህን ስሜት የሚያመጣውም ‹ዶፓሚን› ነው፡፡ ዶፓሚን በአእምሯችን ውስጥ ያሉትን የደስታ ቀጣናዎች የሚቆጣጠር ቅመም ነው፡፡ አንድን ነገር በጣም ከፈለጉት፣ በአእምሮዎ ውስጥ በሚካሄደው የዶፓሚን መለቀቅ  ደስታ እየተሰማዎት ነው ማለት ነው፡፡ የሆነው ሆኖ ያ የሚፈልጉት ነገር ግን የአስፈላጊነቱ ደረጃ ወደ ሁለተኝነት ወረደ ማለት ነው፡፡ እስኪ እንዲያው ቆም ብለው ያስቡት፡፡ ለረጅም ጊዜ እገዛዋለሁ በማለት ሲመኙት የነበረውን ነገር ከገዙት ከተወሰኑ ሰዓታት በኋላ ምን ተሰማዎት? መቼም እቃው እጅዎ የገባ ጊዜ የተሰማዎትን ያህል አይደለም፡፡ ሲመኙት የነበረው ጊዜ የነበረዎትንም ደስታ ያህል አይደለም፡፡ ይህ ተፈጥሯዊ ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ሰው የመሆናችን ውጤት ነው፡፡
ይህ በዚህ መልኩ የሚሰማዎት ደስታ እውነተኛ ደስታ አይደለም፡፡ በእርግጥ ሰውነትዎ ውስጥ ከሚካሄደው ስነ-ሕይወታዊ እንቅስቃሴ አንጻር ስናየው የሚደሰቱት በዶፓሚን ርጭት ምክንያት ነው፡፡ ይህ የዶፓሚን ርጭት ሲያበቃ መልሰው ሌላ አዲስ ነገር የመፈለግ እድልዎ ሰፊ ነው፡፡ የዚህም ምስጢሩ የበለጠ ዶፓሚን ፍለጋ መሆኑ ነው፡፡ ‹‹ገንዘብ ደስታን አይገዛውም›› የሚለው ነባር አባባል ትክክለኛ ትርጉሙ እንግዲህ ይህ መሆኑ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ገንዘብ ደስታን የሚገዛልዎ መንገድም አለ፡፡ ችግሩ እርስዎ በሚያስቡት መንገድ አይደለም እንጂ፡፡


ደስታን ከፈለጉ ጊዜን ይግዙ

የአሜሪካ ብሔራዊ የሳይንስ አካዳሚ በቅርቡ ባሳተመው መጽሔቱ የአንድን ጥናቱን ውጤት አቅርቦ ነበር፡፡ ለጥናቱም በሁለት ቡድኖች የተከፈሉ ሰዎች እያንዳንዳቸው ለየግላቸው አርባ አርባ ዶላር ተሰጣቸው፡፡ የአንደኛው ቡድን አባላት በገንዘቡ ማናቸውንም የፈለጉትን እቃ እንዲገዙበት ተነገራቸው፡፡ የሁለተኛው ቡድን አባላት በአንጻሩ የበለጠ ነጻ ጊዜ እንዲኖራቸው የሚያስችላቸውን እድል እንዲፈጥሩበት ተነገራቸው፡፡ ለምሳሌ ምግብ ከሚያዘጋጁ ይልቅ ተሰርቶ እንዲመጣላቸው እንዲያስደርጉ፣ ወይንም ቤታቸውን ራሳቸው ከሚያጸዱ ይልቅ ሌላ ሰው እንዲያጸዳላቸው እንዲያስደርጉ ታዘዙ፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎች እያንዳንዳቸው ደስታቸውን ከዜሮ እስከ ዐሥር ባሉት ቁጥሮች ተጠቅመው እንዲመልሱ ሲደረግ  ገንዘቡን ተጨማሪ ነጻ ጊዜ በመግዛት ላይ ያዋሉት ሰዎች እቃ ከገዙቱ ይልቅ በአንድ ሙሉ ነጥብ ልቀው ተገኝተዋል፡፡     

የተደሰቱት እንግዲህ መስራት ከማይፈልጉት ነገር ራሳቸውን በማላቀቃቸው ነው፡፡  በረጅም ጊዜ ሲታይ ገንዘቡን ተጨማሪ ጊዜ ለመግዣ ያዋሉት ሰዎች የላቀ የህይወት እርካታ ሲያገኙ፤ ተጨማሪ ሸቀጥ መሸመቱ ግን በእነዚያኞቹ ደስታ ላይ ያመጣው ለውጥ አልነበረም፡፡  

ሰዎቹን ያስደሰታቸው ያገኙት ነጻ ጊዜ ነው፡፡
ያ ያገኙት የጊዜ ፋታ ነው ደስታቸውን ያመጣላቸው፡፡ ገንዘቡ በቃ ተጨማሪ ጊዜ ለማግኘት የተጠቀሙበት መሳሪያ ነው፡፡ ገንዘቡ በመሰረቱ አላስፈላጊ ነው፡፡ ዋናው ቁም ነገሩ ጊዜን የሚያዩበትን መንገድ ማስተካከሉ ላይ ነው፡፡

እያንዳንዳችን በቀን 24 ሰዓት አለን፡፡ [በበለጸገው ዓለም?] የሴቶች አማካይ የእድሜ ጣሪያ 81.2 ዓመት ሲሆን፤ የወንዶቹ ደግሞ 76.4 ነው፡፡ ከሞላ ጎደል አብዛኞቻችን እኩል ጊዜ አለን ለማለት ይቻላል፡፡ እያንዳንዷ ሰዓት ወይንም ደቂቃ በአስፈላጊው ነገር ማሳለፍ መቻል ደስተኛ ህይወትን የመፍጠሪያው ዓይነተኛ መንገድ ነው፡፡
እርስዎ ሁልጊዜ ብትለት ወይንም የስራ ጫና የሚሰማዎት ከሆነ፣ ለራስዎም በቂና የተስተካከለ ጊዜ ያለዎት ካልመሰለዎት ሁኔታውን ለማስተካከል ለውጥ ማምጣት ይኖርብዎታል፡፡     


ገንዘብ ይኑረኝ ወይንስ ጊዜ?
ጊዜ አላቂ ነው፡፡ እያንዳንዳችን በዚህ ዓለም ላይ ያለነው በጊዜያዊነት ነው፡፡ ጊዜን በብልሐት መጠቀም አስፈላጊ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ምንም የማይጠቅሙዎትን ነገሮች በመፈጸም ጊዜዎትን ሊያባክኑ መቻልዎት እሙን ነው፡፡  ብዙዎች ሰዎች ጊዜያቸውን የሚያሳልፉበት መንገድ ይህ ጊዜያቸው ምንም ገደብ የለውም አንዴ የሚያሰኝ ነው፡፡ ነገሩ ግን በተቃራኒው ነው፡፡
እስኪ በየቀኑ ዐሥር ዐሥር ብር ይቆጥባሉ ብለን እናስብ፡፡ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ 3650 ብር ይኖርዎታል፡፡ በተመሳሳይ መንገድ ከጊዜ በኋላ የሚጠቀሙበት ዐሥር ደቂቃ በየቀኑ ቢያስቀምጡ በዓመቱ መጨረሻ 60 ሠዓታት ይኖሩዎታል፡፡
የእርስዎ ምርጫ ታዲያ የቱ ነው?
አብዛኛው ሰው ገንዘቧን ይመርጣል፡፡ ይገባናል፡፡ ሰዎች ተጨባጭ ነገር ይፈልጋሉ፡፡ ገንዘብም በተፈጥሮው ልንቆጥበው የምንችለው ነው፡፡ ብናጣው ደግመን ሰርተን ልናገኘውም እንችላለን፡፡ የጊዜ ነገር ግን ወዲህ ነው፡፡ አንዲት ሠዓት ካለፈችን ለዘላለሙ አልፋ ትቀራለች፡፡ አብዛኞቹ ሰዎች ብዙውን ጊዜ የሚዘነጉት ነገር ቢኖር እነዚያ የተከማቹ 60 ሠዓታት ከ3650 ብሩ የበለጠ ዋጋ ሊኖራቸው መቻሉን ነው፡፡ ጊዜያችንን በትክክል ዋጋ እንሰጠው ዘንድ በአእምሯችን ውስጥ ተጨባጭ ወደሆነ ነገር ልንቀይረው ግድ ይለናል፡፡

ገንዘብ ተጨባጭ ሆኖ ጊዜ ተጨባጭ አይደለም?
ሕይወታችን የተለያዩ ክንውኖች ድምር ነው፡፡ እያንዳንዷን የምንለፋለትን ነገር የምናደርገው በመጨረሻ በጎ ዓላማ አስቀምጠን ነው፡፡  ማንኛችንም ብንሆን ከማያስደስቱ ይልቅ ብዙ አስደሳች ጊዜያት እንዲኖሩን እንፈልጋለን፡፡ ለምንወዳቸውም ይህንኑ እንመኛለን፡፡
እነዚህን ነገሮች ለማገኘት የሚከፍሉት ዋጋ ግን ምንድነው?
ያ ዋጋ ጊዜ ነው፡፡ እያንዳንዱ ነገር የሚደረገው መቼም ለዚህ ሲባል ነው፡፡ አንድን ነገር የምናደርግበት ጊዜ ከሌለን ያ ነገር ትርጉም አልባ ነው፡፡ ቢሊየነር ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ያንን ለማጣጣም ያለዎት ግን አንዲት ሠዓት ብቻ ከሆነች ቢሊየኑ የስሙን ያህል ዋጋ የለውም፡፡
ገንዘብን እንዴት እንደምናገኝና እንደምናጣ በይበልጥ ይገባናል፡፡  ለአብነት አንዲት መቶ ብር መሬት ላይ ብትጥሉ ወዲያውኑ ተመልሳችሁ እንደምታነሷት እርግጥ ነው፡፡ አንድ መቶ ደቂቃ ያለምንም ስራ ብታሳልፉ ግን መቼም ምንም አይመስላችሁም፡፡
የጊዜን ውሱንነት ብናውቅም ብዙውን ጊዜ ውሱን እንዳልሆነ ነው የምናስበው፡፡ አንድ መቶ ብር በጀት እያለዎት አንድ መቶ ሽህ ብር ወጪ ማውጣት እንደሚያከስርዎት እሙን ነው፡፡ ጊዜን እንዲህ ማድረግ ግን የበለጠ ይጎዳዎታል፡፡
‹‹ሌሎች ዕቅዶችን በማቀድ ላይ የምታጠፋው ጊዜ ሕይወት ይባላል፡፡›› ጆን ሌነን፡፡
ገንዘብ ይህን ያህል ተጨባጭ የሚመስለን እኮ በዙሪያችን ያሉት ነገሮች በሙሉ የገንዘብ ዋጋ ስለተተመነላቸው ነው፡፡ የነገሮችን አንጻራዊ ዋጋ ለመተመን ይጠቅመናል፡፡ ለጊዜም ግን ይህን ማድረግ እንችላለን፡፡


ጊዜን የመለኪያው ትክክለኛው መንገድ
አንድ ቀን 24 ሠዓታትን ይይዛል፡፡ ሁሌ በሠዓት ውስጥ ስድሳ ደቂቃ፣ በደቂቃም ውስጥ ስድሳ ሴኮንዶች አሉ፡፡ አንዳንድ ሕይወት ረጅም፣ አንዳንዱ ደግሞ አጭር ቢሆንም እርስዎ ግን ከ70 እስከ 80 ዓመት ዕድሜ ይኖራሉ ብለን እናስብ፡፡ ከዚህ ውስጥስ ምን ያህሉን በወጣትነትና በመልካም ጤንነት ያሳልፋሉ? ከነዚህ ዓመታት ውስጥ በሕይወትዎ ዋጋ ከሚሰጧቸው ሰዎች ጋር የሚያሳልፏቸውስ ስንቶቹን ነው?
ጊዜን በደቂቃዎች ወይንም በሰዓታት እንደሚለካ ነገር ከመቁጠር ይልቅ እንዴት እናሳልፈዋለን የሚለውን መመልከት ይጠቅማል፡፡ የሕይወትዎ ጥራት የሚለካው በጊዜዎ ጥራት ነው፡፡ እርስዎም በአንድ አቅጣጫ ከሚያዩት ይልቅ በበለጠ አተያይ ሊያዩት ይገባል፡፡
እስኪ ለምሳሌ ራስዎን የሚከተሉትን ጥያቄዎች ይጠይቁ፡-
በቀን ውስጥ ስንት ሠዓታትን ተናደው፣ ሰግተው፣ እርካታ አጥተው ወይንም ተበሳጭተው ያሳልፋሉ?
ከሚወዷቸው ጋር ዝም ብሎ እቤት ውስጥ አብረዋቸው በመቀመጥ ሳይሆን በጥሩ ግንኙነት ምን ያህል ጊዜ ይቆያሉ?
ራስዎን በማሻሻል ስራ ላይ በየቀኑ ወይንም በየሳምንቱ ምን ያህል ጊዜ ለማሳለፍ አስበዋል?
እንዲያው በማይረዷቸው ምክንያቶች የማያስደስቱዎትን ስራዎች በመስራት የሕይወትዎን ምን ያህል ሠዓታት ይፈጃሉ?
በአንድ ምሽት ከ6 እስከ 8 ሰዓታት ያህል በእንቅልፍ እናሳልፋለን፡፡ ግን ምን ያህል ሠዓታት ናቸው እውነተኛ ረፍት የሆኑት? ስለዚህ ምን ያህሉን እንዲያው አልጋችን ላይ ተጋድመን አሳለፍናቸው?

ለእነዚህና እነዚህን ለመሳሰሉ ጥያቄዎች መልስ የሚፈልጉና እርምጃ የሚወስዱ ከሆነ የራስዎን ሕይወት ጥራት ለመቆጣጠር በሚያስችልዎት መንገድ ላይ ሊገቡ ነው ማለት ነው፡፡  ካልሆነ ግን ለመጀመር ጊዜው አሁን ነው፡፡
ስራዎትን ትተው እያንዳንዱን ቀን እንደፈለጉ እንዲያሳልፉ እየመከረኩዎት አይደለም፡፡ ያ ምክንያት-አልባና የማይመስል ነገር ነው፡፡ ስለነገሮች እንዴት ማሰብ እንዳለብዎትና ምን ላይ ለማተኮር እንደሚወስኑ በየቀኑ ሊመርጧቸው የሚችሏቸው በርካታ ምርጫዎች አሉልዎት፡፡ እርስዎ ልብ አሉትም አላሉት እነዚህን ምርጫዎች ሁልጊዜ ይመርጣሉ፡፡ እነዚህን ምርጫዎች ልብ ብለው ሕይወትዎን የሚቆጣጠሩ ከሆነ ትርጉም ያለው ጊዜ የሚያሳልፉባቸውን በርካታ ሠዓታት፣ ቀናት እንዲሁም ዓመታትን ይቀዳጃሉ፡፡ እያንዳንዱ ሰው በየቀኑ ተመሳሳይ ሃያ አራት ሠዓት አለው፡፡ ቢሆንም እርስዎ ግን ከሚያስቡት በላይ ከዚህ ጊዜ አብዛኛውን በቁጥጥርዎ ስር ማዋል ይችላሉ፡፡
የመጀመሪያው እርምጃዎ መሆን ያለበት ጥራት ያለውን ሕይወት ዝም ብሎ ለንግግርዎ ማሳመሪያ ሳይሆን እውነተኛ እሴት ለማድረጊያ መጠቀም ይኖርብዎታል፡፡   
በመሰረቱ የሕይወትዎ ጥራት የሚበየነው በጊዜዎ ጥራት ነው፡፡
የእንቅልፍዎን ጥራት በእጅጉ የሚያሻሽሉ ትናንሽ ተግባራትን በቀኑ ውስጥ ቢወስዱ ምን ይመስልዎታል?
አለያም የሃያ ደቂቃ የቀን እንቅልፍ በመተኛት የዕለቱን ምርታማነትዎንና የሰውነትዎን አቅም ያሳድጉ፡፡
ከጓደኞችዎና ከሚወዷቸው ጋር በሚገናኙባት አጭር ጊዜ ጥልቅ ትስስር ያለው ቆይታ ቢያሳልፉስ?  
እነዚህ እንግዲህ ከላይፍ ሃክ ዋና እሴቶች አንዱ የሆነውን የጊዜዎን ጥራት መጨመርን አስመልክቶ ካከማቸናቸው በርካታ መንገዶች እጅግ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

በህይወታችን ካሉን ትልልቅ ቁጭቶች የተወሰኑት ጊዜያችንን ለማሳለፍ በወሰንባቸው መንገዶች ምክንያት ያጣናቸው ዋጋ ያላቸው ጊዜያት ናቸው፡፡ እነዚህን ጊዜያት መልሰን ለመኖር ወይንም የተለዩ ምርጫዎችን ለማድረግ እንችል ቢሆን ልንከፍል የምንችለውን በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ አስቡት፡፡ ስለዚህ ጊዜዎ በትክክል ዋጋ እንዲኖረው የማድረግ ምርጫን ያድርጉ፡፡ አሁን በሕይወት ሳሉና እየተነፈሱ ሳለ፤ አጅግ ዘገየሁ ብለው አያስቡ!  

በበርካታ ክፍሎች ይቀጥላል!









2018 ኦገስት 6, ሰኞ

የእንትን ብሔረሰብ አባላት እንደሚጠሉት በምን አወቀ?


ነሐሴ 1፣ 2010፡፡

ደብረ ብርሃን፡፡


የኦክስፎርድ የእንግሊዝኛ መዝገበ-ቃላት ለአንድ ነገር የሚኖረን ‹‹ጽኑ ምክንያት-የለሽ ፍራቻ›› ሲል ቃሉን ይበይነዋል፡፡ በስልኬ ያለኝ መዝገበ-ቃላት በበኩሉ ‹‹አመዛዛኝነት በዞረበት ያልዞረ በልክፍት ደረጃ ያለ ፍራቻ›› ሲል ይፈታዋል፡፡ ትርጉሙን እንደዚህ አውቀን ቃሉን ለማወቅ መቻኮላችን ያለና የነበረ ቢሆንም ቃሉን ለአፍታ እናቆየውና ርዕሰ-ጉዳያችንን እንመርምር፡፡ ‹‹ቃሉንማ አውቀዋለሁ! አንተ አሳስተህ ተረጎምከው! እኔ ባለሙያ ስለሆንኩ በተሻለ መጠን አስረዳለሁ!›› ለሚል ሰው የአስተያየት መስጫው ክፍት ነው፡፡



የአንድን የእንግሊዝኛ ቃል ፍቺ በማብራራት ጀመርኩ፡፡ የአማርኛ አቻ አለው ወይስ የለውም ብሎ ለሚጠይቀኝ ሰው መልሴ አይጠፋም ነው፡፡ ቃሏን ዛሬ ከአንድ ቪዲዮ ስሰማት ‹‹ምነው በፖለቲከኞቻችን ዘንድ ተዘወተረች!›› ብዬ ለመምዘዝ በቃሁ፡፡  

‹‹የእንትን ህዝብ ለምንትስ ህዝብ ፎቢያ አለው›› በማለት ንግግራቸውን፣ ሃሳባቸውንና ድርጊታቸውን ምክንያታዊ የሚያስመስሉ ፖለቲከኛን ስሰማ ደነገጥኩ፡፡ ህዝቡ የሰዎች ድምር በመሆኑ ጉዳዩን ወደ ሰዎች ደረጃ አውርደን እንነጋገር፡፡

ፎቢያ ያላቸው ሰዎች እንዴት ልጆቻቸውን ለሚጠሉት ይድራሉ?

ጽኑ ምክንያት-የለሽ ፍራቻ ካለው እንዲጋባ ማን ያስገድደዋል?

የፖለቲካ ጋብቻ መሰላቸው እንዴ!



ጥያቄ ሳላበዛ ወደመሰለኝ መልስና ማብራሪያ ልሂድ፡፡

በመደበኛው የማህበረሰቡ ኑሮ ልጅን ለመዳርም ሆነ ለራስ የትዳር አጋር ለመፈለግ  ሁኔታው በዘላቂነት ተጽዕኖ ያለው በመሆኑ የትዳር አጋር ምርጫው በጥንቃቄ ይፈጸማል፡፡ ይህም በአብዛኛው በቋንቋ፣ በኃይማኖት፣ በትውልድ ስፍራ፣ በኑሮ ደረጃ ወዘተ ተመሳሳይነት ያለው ሰው ፍለጋን ያመጣል፡፡ ከህዝብ እንቅስቃሴ፣ ከዓለም ስልጣኔ፣ ከተግባቦት መጨመር፣ ከአገር ምስረታ ጋር የሚያያዙ ምክንያቶች ከማህበረሰብ ውጪ ማግባትን ግድ ይሉታል፡፡ ከዘመናዊነት ጋር የሚመጣ ከአንድ ማህበረሰብ ውጪ ካለ ሰው ጋር የሚፈጸም ጋብቻ በአገራት ደረጃ ይቅርና በዓለም አቀፍ ደረጃ እየጨመረ ነው፡፡ የአንድ አገር ሰው የሌላን አገር ሰው አግብቶ በሰላም እንደሚኖር ይታወቃል፡፡ እኛ አገር በተቃራኒው ከስልጣኔ መንበር በየጊዜው እየራቅን ቁልቁል እየወረድን ስለሆነ በማህበረሰባችን ውስጥ ብቻ እየተጋባን እንገኛለን፡፡ ከውጪ አናስገባም ብለናል፡፡ ይህም የሚያሳየው ትናንት የሰለጠንን ዛሬ በአንጻሩ ያቆለቆልን መሆናችንን ነው፡፡ በሃገራችን አንዱ ማህበረሰብ ከሌላው ሲጋባ የኖረው ተዋዶ እንጂ የፖለቲካ ዓላማ ኖሮት አይደለም፡፡ ነገሥታት አድረገውት ሊሆን ቢችልም ግለሰቦች ግን ሊያስቡት አይቻላቸውም፡፡



ጋብቻ ከትስስሮች ሁሉ የላቀው ስለሆነና ፍሬውም ለዘመናት የሚቆይ ስለሆነ መነሻ ምሳሌ አደረግነው፡፡ይሁን እንጂ በሌላ ዘርፍም ቢሄዱ ጉዳዩ ያው ነው፡፡ ጋብቻ ለመፈጸም ድፍረት ያለው የእውነት ይወዳል ማለትም ስለሚቻል ነው፡፡    



አባቶቻችን ያልተማሩ ሞኞች ስለነበሩ ባህላቸውን፣ ቋንቋቸውን፣ ኃይማኖታቸውን፣ ማንነታቸውን አደጋ ላይ የሚጥል ውሳኔ ስላደረጉ ብቻ እኔ አላደርገውም የሚሉም አይጠፉም፡፡ ለሰው ልጅ ተፋቅሮ መኖርና ለዓለም ሰላም ካልጠቀመ የኔ ቋንቋ ምንድነው! ማንነቴስ! ኃይማኖቴስ! ተደፍጥጠዋል የሚልም ይኖራል፡፡ ታዲያ አዲስ ማንነት ቢያዝስ ምን ይኮናል?

ህብረተሰቡ ይጠሉኛል ባላለበት ሁኔታ፣ ጠላ የተባለውም እጠላቸዋለሁ ባላለበት ሁኔታ ይጠሉናል ማለት ምንድነው? ለራስ የፖለቲካ ትርፍ ሲባል ህዝብን የሚያጣላ ነገር ከመደርደር የሚያፋቅር ነገር ማምጣት አይቻልም ወይ?

ለፖለቲከኛው መጠየቅ የሚፈልጋቸው ጥያቄዎች አሉኝ፡-

ሀ. በጽኑ እንደሚጠሉ በምን አወቅህ?

ለ. ህብረተሰቡ በየትኛውም ዓለም እንዳለው አንዱ ላንዱ ከሚሰጣቸው ባህሪያትና ቀልዶች በዘለለ የከረረ ነገር አይተሃል?

ሐ. ምክንያት-የለሽ ፍራቻ እንዴት ይኖራል?

መ. አመዛዛኝነት የሌለው ፍራቻ እውነት እኛ አገር በህዝብ ዘንድ አለ?

ሠ. በልክፍት ደረጃ ያለ ፍራቻስ?



አሁን እዚህ እቤቴ በምሽት እየጻፍኩ (ሐምሌ 30፣ 2010፣ ከምሽቱ 7፡17 ላይ) ሳለሁ አንድን ህዝብ ፈርቻለሁ? አልፈራሁም፡፡ ለምን ብዬ? በወገን መሃል ነኝ ብዬ አምናለሁ፡፡

በእንትናችን ምክንያት ይሰድቡናል ሲባል የከረመውን ነገር አንድ ወቅት ከሰው ጋር ባደረኩት ወግ እንደተረዳሁት የሚገርም ግንዛቤ ጨብጫለሁ፡፡ ሰዳቢ የተባለው ህዝብ አንድ አባል የነገሩኝ ነገር ቢኖር ‹‹እነሱ እኮ በእንትናቸው ይኮሩብናል›› የሚል ነው፡፡ ‹‹እኛ እንደነሱ አንትን ባይኖረንም ሰርተን እናገኛለን›› ዓይነት ነገር መሰለኝ ያሉኝ፡፡ ይንቁናል የተባለው ነገር የሚያስከብራችሁ ሆኖ ተገኘ፡፡ ‹‹ጎረቤቴ ይህን ያወራ ይሆናል›› ብሎ ከማሰብ የራስን ሃሳብ መኖር የሚሻል ይመስለኛል፡፡ ያኔ ከተጋነነ ፍራቻ ራሳችን ነጻ እንወጣለን፡፡ ምናልባት እኛው ከሆንንስ የተጋነነ ፍራቻ ያለብን! ራሳችንን እንመርምር፡፡



ከጽሑፉ በኋላ የመጡልኝ ሃሳቦች፡-



ወደ ሌሎች ስንጠቁም አራቱ ጣቶቻችን ወደራሳችን ይጠቁማሉ የሚለው አባባል ለአሁኑ ጉዳያችን ትክክለኛ ማስረጃ ነው፡፡

ይፈሩኛል ብሎ መኖር ምን ጥቅም አለው? እፈራቸዋለሁ ቢሆን የራስን ስሜት ስለሆነ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡

ምን አልባት ፈርተው ከሆነም መፍራታቸው ይጠየቅ፡፡

እውነት ከፈሩ አይዟችሁ በላቸው፡፡

በፍርሃት እንዲሞቱ ብትፈቅድ ግን ዋጋ የለውም፡፡

እኛና አነሱ እያልክ ከምትከፋፍል አርፈህ ስራህን ብትሰራ ምን አለበት

እሱና እኔ ከምትል እኛ ብትል አስደናቂ ጥምረት ይፈጠርና በጋራ ታድጋላችሁ፡፡

የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል፡፡

የጥርጣሬ ቤት ከንቱ አደጋ ይጠብቀዋል፡፡

የበለጠ የፍራቻ ቤት የፈሪ ዱላና ያልተጠበቀ ውድመት ያስከትላል፡፡


የተማረው ወደ ትውልድ ቀዬው ያለመመለሱ ሲፈተሽ


የራስ አበበ አረጋይ ቤተመጻሕፍት የዕለቱ መልዕክት


ነሐሴ 1፣ 2010፡፡

ደብረ ብርሃን፡፡

የጽሑፉ ዓላማ፡- ሁላችንም ‹‹እሱ እኮ የዚህ አገር ልጅ ነው!›› የሚለንን መጥቀምና ማገዝ እንዳለብን ለማስታወስ ነው፡፡   

‹‹በየትኛው የአገራችን ክፍል የተማረው ሰው ወደ ቀዬው ተመልሶ ለውጥ ለማምጣት ቻለ?›› ብለን አእምሯችንን ለመፈተሽ እንሞክር፡፡

ይህን አረፍተነገር ቃል በቃል እንመንዝር ብንል  እንኳን ብዙ ቁም ነገሮችን ማውጣት እንችላለን፡፡ 

ሀ. በየትኛው የአገራችን ክፍል?

ይህን ሃሳብ ስንመነዝረው ከመቀሌ እስከ ሞያሌ፣ ከጎሬ እስከ ጎዴ፤

ከገጠር እስከ ከተማ፤

ከለማ እስካልለማ፤

ለመድረስ ከሚያዳግት እስከ ምቹ፤

የተለያዩ ኃይማኖቶች፣ የሥልጣኔ ደረጃዎች፣ ቋንቋዎች፣ ባህሎችና አመለካከቶች ያሏቸውን

የትኛውንም ዓይነት ክፍል ማለታችን ነው፡፡

ለ. የተማረው ሰው?

በህብረተሰቡ ‹‹የተማሩት ምን አመጡ?›› የምንባለውን፤

በአካባቢያችን ያለውን የትምህርት ደረጃ አልፈን ለትምህርት ሲባል የወጣነውን፤

ሰርተፊኬት፣ ሌቭል 1፣2፣3፣ ወዘተ፣ ዲፕሎማ፣ ዲግሪ፣ ማስተርስ፣ ፒኤች ዲ፣ አጫጭር ስልጠና ወዘተ ያለንን

በትምህርት እንጀራ የወጣልንን፤

የሚያውቀን ታዳጊ እንደሱ/ሷ ተምሬ ትልቅ ደረጃ እደርሳለሁ የሚለንን፤

ማለታችን ይሆን?

 ሐ. ወደ ቀዬው?

ዘር ማንዘራችን ከተወለድንበት ሥፍራ የሚመዘዘውን፤

ወላጆቻችን በአካባቢው የተወለዱትን፤

ወላጆቻችን ለሥራ ጉዳይ በሄዱበት የተወለድነውን፤

አካባቢውን አድገንበት ትዝታውና ውለታው ያለብንን፤

ዘለግ ላለ ጊዜ የሰራንበትን፤

ውኃውን የጠጣነውን፤

በንገዱ ያለፍን ያገደምንበትን፤

ትዝታው ውል የሚልብንን፤

እልቆ መሳፍርት ነገር ልናነሳለት የምንችለውን ማለት እችል ይሆን?

መ. ተመልሶ?

ቋሚ መኖሪያውን ወደዚያች ስፍራ ቀይሮ፤

በልቦናው ወይም በእግረ-ህሊናው ሄዶ፤

ረዘም ላለ ጊዜ ሄዶ ቆይቶ፤

ለአጭር ጊዜ ሄዶ ሰርቶ፤

ለአንዲት ቀን ሄዶ፤

ሠ. ለውጥ ለማምጣት ቻለ?

ጫማ እያላችሁ ያለማድረግ ልማዳችሁን ተዉ ካለ፤

ሃሳቡን ካጋራ፤

ካወያየ፤

ግጭት ከፈታ፤

ትምህርት ቤቱን ተመልሶ ካየ፤

የእምነት ተቋሙን ካሰራ፤

ዛፍ ከተከለ፤

ችግረኛን ከረዳ፤

የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ካስተዋወቀ፤

ሌላው ቢቀር በመንደሩ ሄዶ ከተንጎራደደ (እንደሱ እሆናለሁ የሚሉ ልጆች ሊወጡ ስለሚችሉ)፤

ምርጫ ከተወዳደረ፤

ቆቅና ጅግራ ካደነ፤

ግብረ ሰናይ ድርጅት ካመጣ፤

ስልጠና ከሰጠ፣ ካሰጠ፤

በገቢ ማመንጫ ቡድን ካደራጀ፤

ዝርዝሩ አያልቅ ብሎን እንቸገር ይሆን?



ወገኖቼ፣

ወገኖቼ ማለቴ ላቀርባችሁ ስለምችል፣ ስለምወድ፣ ስለሚገደኝ፣ ስለማይቆጨኝ፣ መልካም የሆነው ሁሉ ወዘተ ነው፡፡

ቀስ ብለው ራስዎን ይዘው ይከተሉኝ፡፡

በምናብ፡፡

አንድ አፍታ፡፡

ከተቻለ በዚያች ቀዬ አብሮዎት ላደገ ሁነኛ ወዳጅዎ ይህን ጽሑፍ ይላኩለት፤ አንብቦም ተወያዩበት፡፡ አንድም ነገር አድርጉ፡፡



በዚያች ቀዬ አካላዊ ትዝታ፡-

አፈሩን ሲፈጩ የነበረው፤

በባዶ እግርዎት ሲሄዱ የነበረው፤

ፀሐይ ላይ ሲቀመጡ የነበረው፤

ሲያምዎት የነበረው፤

ሲርብዎት የነበረው፤

ሲጠግቡ የነበረው፤

ቀን የሚውሉባቸው ስፍራዎች፣ አመሻሽ የሚያሳልፉባቸው የተለመዱ ቦታዎች፣ ሌሊት የሚያድሩበት ቦታ (አልጋ፣ ድብዳብ፣ መደብ፣ መሬት፣ ሳጥን ላይ፣ ምድጃ ….)

መጸዳጃ ቤት ነበር ወይስ አልነበረም?

ወሳኝ የህይወትዎ ጊዜያትስ - ልደት፣ ግርዘት፣ ክርስትና፣ ሰርግ፤



በዚያች ቀዬ መንፈሳዊ ትዝታ፡-

ቤተክርስቲያናችሁ፣ መስጊዳችሁ፣ የአምልኮ ዛፋችሁ፤

መንፈሳዊ አባቶቻችሁ፤

የበዓላት ቀናት፤

ስታዝኑ፤ ስትደሰቱ፤

ጾምና ጸሎቱ፤

የቡድን አምልኮው፤

ለተቸገረ ያበላችሁበት፤

የተጣላ ያስታረቃችሁበት/የታረቃችሁበት፤

አምላክ ተቀይሞኛል የምትሉበት፤

አምላክን የተቀየማችሁበት፤



በየዘርፉ በርካታ ትዝታ ያላችሁ ያች ቀዬ አሁን በምን ዓይነት መልኩ ተለውጣለች? ‹‹እኔ አካባቢዬን መለወጥ እችላለሁ›› ብለን ማመን አለብን ይህን ጉዳይ ከዳር ለማድረስ፡፡ ተስማማን መሰለኝ፡፡ እንቀጥል፡፡ የተወሰኑ ዘርፎችን ለይተው እርስዎ ሲያድጉ ከነበረው የተሻለ ለማድረግ የድርሻዎትን ይወጡ፡፡

ምን ምን ሊያሻሽሉ እንደሚችሉ እንነጋገር፡፡

ሀ. ሰፈራችሁ

ለ. ትምህርት ቤታችሁ

ሐ. የእምነት ተቋማችሁ

መ. ማህበራዊ ግንኙነታችሁ

በእነዚህ ዘርፎች አንድ አንድ ነገር ለመስራት ከተነሱ ሌላውም እየተሰካካ ይፈታል፡፡ ጓደኞችዎ ደግሞ ከእርስዎ የበለጠ የጋለ ስሜት ስላላቸው በአራት ዘርፈፎ እንዲሁ መስራት ይቻላቸዋል፡፡



ያኔ

የሥልጣኔ ጮራ እናንተ ቀዬ ሰተት ብላ ትገባለች፡፡

የሰራችሁትን ስለምትጽፉት ሌሎችም ይከተሏችኋል፡፡

ጸጸት አይኖርብዎትም፡፡

በሌሎች የህይወትዎ ዘርፎች ስኬቶችን ይቀዳጃሉ፡፡

ውለታ ቢስነት አይሰማዎትም፡፡



ለተግባር ስለተነሳሱ አመሰግናለሁ፡፡



ከጽሑፍ በኋላ የመጡ ሃሳቦች፡-

ሀ. በኢትዮጵያ ሬዲዮ በአንድ ወቅት የሰማሁት ሰው ሃገር ውስጥ ቀርቶ ለመስራትና ለእረፍት ሲል ጥሎት ወደመጣው ውጪ አገር ላለመሄድ የወሰነው ከሃያ ዓመታት በፊት ቁጭ ብሎ ጫማ የሚያስጠርግበት ድንጋይ በመጣም ጊዜ እዚያ ስፍራ መኖሩ አሳዝኖትና የቀዬውን ያለመለወጥ አይቶ ነው፡፡

ለ. የህይወት መንገዱ የጠፋቸውና እኛ አንድ አፍታ ችግራቸውን አይተን ብንመክራቸው ሊለወጡ የሚችሉ የልጅነት ጓደኞችና የምናውቃቸው ሰዎች አሉ፡፡ የባንግላዴሹ ማህሙድ የኑስ የሚሊዮኖችን ህይወት እንዴት እንደለወጡ አንብቡ፡፡

ሐ. እኛን ያዋለዱን እናቶች የት ይሆኑ? እንደኛ ልጅ አላቸውን?

መ. ለትምህርት ቤታችን ለዓመት ማስታወቂያ መጻፊያ የሚበቃ ማርከር ከ100 ብር የሚበልጥ አይመስለኝም፡፡
 


2018 ኦገስት 3, ዓርብ

Four Generations of English Majors in Ethiopia


Mezemir Ethiopia
August 3, 2018

The idea of writing on this topic has been kept on my table for a long while. However, since I’m getting increasingly disorganized and leave such important issues unfinished, the commencement of the project stayed until this day. Since, on this day, I found some time for this activity, the scribbling has started. As to the means by which I get the input for the writing endeavor, I had planned to distribute questionnaires, conduct focus group discussions and interviews. These, as time permits, shall be done in the future. Let me, for the time being, share with you the ideas I gathered through the informal talks and conversations I made.  

Introducing myself is vital at this level. I am a lecturer of English who is placed in the third generation in the category below. Currently, I teach English and literature courses at Debre Birhan University. I have been trying to learn English until this time. All in all, I find it hard to comfortably express myself in the language. 

The First Generation:

The First generation is what came after the second Italo-Ethiopian war, 1936 - 1941. The education system, which was modeled after the British one had a keen concern in the quality of English language teaching.  The pupils schooled at that time were native-like as they were trained in modern boarding schools which had quality  teaching materials, expatriate teachers, testing systems and so on. Above all, they were able to pursue higher learning abroad with ease. The books these students authored, both literary and non-literary, the intellectual movements they started and their overall personality puts them above the other categories of English majors. World-class authors including Tsegaye, Daniachew and Solomon are from the Imperial years. 

The Second Generation: The generation in this category comes next to the ones whose story is narrated above. The students who completed school in the old curriculum were selected to join higher education on strict criteria. They had a sound knowledge of grammar and reading. As they joined universities and colleges that demanded rigorous study and hard work, they maintained the love for education particularly English. At the time being they are found at schools, civil service and universities among others. The current state of the English language in Ethiopia, even if it is grammar-centered relies on them. Whether my generation achieved greater goals or not, it is the fruit of their mentorship and effort. At this point, we should mention those educated at Kotebe and Addis Ababa Univeristy. They relate about their schooling with passion and eagerness. Novels including Animal Farm, Gulliver's Travels and Great Expectations are very familiar with these guys.

The Third Generation: Those of us who joined universities in the first rounds of the new curriculum fall under this category. Among us, there are students who had interest in learning in general and the English department in particular. There is also a significant number of English majors who didn’t choose or like English. For the sake of their survival, which is to acquire a job, they are there. However, one cannot confidently say they hate learning. I can mention some reasons why the weakness started. The declining quality of English language teaching in the lower grades and high schools made the students relatively weaker than the previous ones. The lecturers at the English departments also played their own strong and weak roles. In big universities, they prefer to work part-time outside the universities and, as a result, give a lesser attention to their students at public universities. Even the bright students at the English departments get weaker and weaker throughout their stay at universities. If one witnesses how departments like Political Science handle their students, it is easy to learn that even slow learners improve their skills dramatically.        

The Fourth Generation: The generation that is at universities at this time has been categorized under this category. From the point of view of the teachers and the community, this time is when the teaching and learning of English is in the brink of failure. Among a class of 30 students, if you find five who chose English as their major, you are very lucky. Some students who perform well in English and who would otherwise intend to join the English department are assigned at other departments because of the rules of the ministry. The burden the nation experienced because of the previous failures is being observed now. Something should be done to keep the relative quality of English language teaching intact. There should be a love of such key areas as literature, writing and speaking to achieve bigger goals in the area of English language teaching in this country.

Thank you for reading. I look forward to hearing from you!

2018 ኦገስት 2, ሐሙስ

ሠላም ለሃገራችን!



ባለፉት ዓመታት፣ ወራት፣ ሣምንታም ሆነ ቀናት የሆነውን ሁሉ ስናስበው በአስደሳችና በአስከፊ ነገሮች የተሞላ ጊዜ አሳልፈናል፡፡ 

በፍጥነት የሚለዋወጡ ክስተቶች ከመኖራቸው ባሻገር ስለነዚህ ክስተቶች በየሚዲያውም ሆነ ማህበራዊ ሚዲያው የሚደርሱን ትክክለኛም ሆኑ የተዛቡ ዘገባዎችና ትንታኔዎች የራሳቸው የሆነ ጫና ያሳድርብናል፡፡


በዚህ መሃል እኛ ምን አልን፣ ጻፍን ወይም አደረግን? የኛ ምላሽ ወደፊት የሚኖረውን ክስተት ሁሉ ስለሚፈጥር በጥንቃቄ እንድንንቀሳቀስና ለሠላም መኖር እንድንሰራ አደራ እንላለን፡፡ 

ማናቸውም ዓይነት ድንበር ሳይገድበን ለሰው ልጅ ሠላም እንስራ፡፡  
 መልካም ቀን ይሁንልን!
ሠላም ለሃገራችን!

2018 ጁላይ 31, ማክሰኞ

The Benefits of My Problems

Wednesday, August 1, 2018
Debre Birhan
Mezemir Girma

The best-selling author of the motivational book, “You Can Win”, Shiv Khera teaches us that problems or attitudes that seem to harm us also can have some benefits. There are causes to the consequences.
Some of the problems I have are listed below:
A.      Wandering around the whole day
B.      Not giving time to myself
C.      Forgetting my physical self
D.      Always eating out
Let me search deep in my mind the possible benefits I got from these distractive behaviors.

A.      About My Wanderer Self
As if I get my income from a certain job like one that requires wandering, I spend my days moving here and there. If it is in campus, I go to the lounge, to my colleagues’ offices, the department head’s office and so and so forth. This has a significant negative impact on my job. It could just be one or two classes that I have on a particular day. It is those classes that I consider my job. The day would be covered by my fruitless walking and so on. Outside the campus, though, I would go to hotels and restaurants that serve me for a price I afford. The benefit? Yes. I am now aware that this has to change. The fact that I am fade up with this has brought about a change in my current awareness and status. I have realized that time is a resource whose ownership we have to cherish.    

B.      Not Giving Time to Myself
Did I give time to myself? No. I should quote an experienced Oromo scholar from the university I work in. This acquaintance of mine says that he heard something from a friend in Adama. That friend would worry whether the generation of this Information Technology Era gets time to think. There are TV, FM, Internet, Smartphone, etc that steal the time the youth has. The same is true with me. Due to this and other factors, I am robbed of my time and resources. I cannot think of my life or the progress or failure I am making and. I am not listening to myself.  The benefit of this one? As I can see, this helped me look into myself at this time. Whether I am late or not is up to time, friends and my improved self to judge.

C.      Forgetting My Physical Self
The benefit of this one would be its contribution in helping me now revert to my physical being. What am I for after all? What about this body that serves me? These legs that carry me along. All should be given time and attention. What you, my reader, should know is that our life should be a balanced one. Really! The physical being alone can take us nowhere. To the achievement I wish to reach at, first acknowledging the fact that I forgot my physical self if one step. In an article written yesterday, I mentioned that how my legs rot because I didn’t wear sandals. The other parts of my body also suffered as a result of the attention I failed to give them. Medical checkup? Yearly? No! It was in 2012 that I last had. How funny is our life? Rather miserable!


D.      Eating Out
If there is any grave error I made in my carrier, it is the attention I didn’t give to cooking at home. Cooking has no harm. It is rewarding. When you cook, you have time to look into your life. You have time to clean your house, wash your clothes, bathe and after all do other quadrant two activities. You spend time at home and you give yourself a respect. On the contrary, I forgot myself and ate out. This takes more than fifty percent of my income. The quality of life I lead goes down as a result of this. The benefit of this is still the lesson I took from my own laziness and stupidity. The amount of money I am paid covers the food-related expenses I incur. I think that caused my problem in this regard. If I had a meal planner, that would teach me how to get programmed. I had one. I didn’t stick to it. I tasted the consequence!

I hope I made my point. Just the negative aspects of your life also have positive ones. Every cloud had a silver lining. 

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...