ሐሙስ 2 ኦገስት 2018

ሠላም ለሃገራችን!



ባለፉት ዓመታት፣ ወራት፣ ሣምንታም ሆነ ቀናት የሆነውን ሁሉ ስናስበው በአስደሳችና በአስከፊ ነገሮች የተሞላ ጊዜ አሳልፈናል፡፡ 

በፍጥነት የሚለዋወጡ ክስተቶች ከመኖራቸው ባሻገር ስለነዚህ ክስተቶች በየሚዲያውም ሆነ ማህበራዊ ሚዲያው የሚደርሱን ትክክለኛም ሆኑ የተዛቡ ዘገባዎችና ትንታኔዎች የራሳቸው የሆነ ጫና ያሳድርብናል፡፡


በዚህ መሃል እኛ ምን አልን፣ ጻፍን ወይም አደረግን? የኛ ምላሽ ወደፊት የሚኖረውን ክስተት ሁሉ ስለሚፈጥር በጥንቃቄ እንድንንቀሳቀስና ለሠላም መኖር እንድንሰራ አደራ እንላለን፡፡ 

ማናቸውም ዓይነት ድንበር ሳይገድበን ለሰው ልጅ ሠላም እንስራ፡፡  
 መልካም ቀን ይሁንልን!
ሠላም ለሃገራችን!

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ብሔራዊ አገልግሎት ሲነሣ

 ብሔራዊ አገልግሎት ሲነሣ  ከ2008 ዓ.ም.  ትዝ ያለኝ በኢትዮጵያ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጊዜ የነበረው ብሔራዊ አገልግሎት በሚገባ የተጠና ነው። ከረጅም ዓመታት በፊት በጉዳዩ ላይ መጻሕፍትንና አጫጭር ጽሑፎችን ያነበብኩ ይ...