2023 ጁን 17, ቅዳሜ

ኢትዮጵያም እንደ ዩጋንዳ?

ኢትዮጵያም እንደ ዩጋንዳ? 

ከስር በሚጀምር እንቅስቃሴ መንግሥትን አስገድደን ሕግ እናስወጣው!


አነጋጋሪውን የዩጋንዳ ፀረ-ተመሳሳይ ፆታ ሕግ በጥብቅ እደግፈዋለሁ። ኢትዮጵያም ይህን መሰል ሕግ ማውጣት አለባት ብዬ አምናለሁ። ያው ሆዳም ባለሥልጣን ዶላሩ ያሳሳዋል እንጂ! ባህላችንን አደጋ ላይ ሳይጥል አንድ ሊባል ይገባል። ከፈረንጆች ሳይንስና ቴክኖሎጂን ለመማር የማይጨነቀው ዋልጌ ሁሉ ለዚህ ወደ ኋላ አላለም። ፈረንጆቹም ይህ ነገር መጤ እንዳልሆነ ለማስረዳት ብዙ ጽፈዋል። የሐሰት ጥርቅም! ለማናቸውም በሰፊው የሚደገፈው የባህል ወረራ አደገኛነቱ እያደር ይገባናል። እስካሁን የታዘብኳቸው፦ 

1. የአዲስ አበባ ጉዶች መጽሐፍ ላይ መሰለኝ በአዲስ አበባ ያለው አሳሳቢ ሁኔታ ተጽፏል።

2. ስብሐት ገብረእግዚአብሔር የተባለ በትግርኛ ሳይሆን በአማርኛ ብቻ ለመጻፍና ባህልን ለማጥፋት የተላከ ብዬ የማስበው ግለሰብም ተመሳሳይ ፆታን በረቂቅ ዘዴ ለማስተዋወቅ ሞክሯል። ተልዕኮውን ትውልድ ተመራምሮ ይድረስበት።

3. የልማት ድጋፍ ለማድረግም ሆነ ለማናቸውም ዓላማ የሚመጡ አሜሪካውያንን እስኪ ጠይቋቸው። እኤአ በ2014 ሦስት አሜሪካውያን ሴቶች በደብረብርሃን በአንድ ካፌ ስለ በጎፈቃድ ሥራ ስናወራ በምስጢር ቃላት "አዞዎች" እያሉ ስለ ጉዳዩ ሲያወሩ ምስጢሩ ምን እንደሆነ ጠይቄ ሳይወዱ በግድ አውጣጥቼ ነገሩኝ። ግልጽ ተቃውሞዬን ተናግሬ እዚህ ለማስፋፋት እንዳይሞክሩ አስጠነቀቅኋቸው። ከሐይቅ የመጣችው አሜሪካዊት አንዱን የተመሳሳይ ፆታ አራማጅ ከሐይቅ እስከ ደሴ በመኪና ጎተቱት አለች። በግልጽ ለመከራከር ሲፈሩኝ ሌላ አሜሪካዊ በፌስቡክ ሜሴጅ የጥናት ወረቀት ተብዬዎችን እንዲልክልኝ አደረጉ። ይህን መሐልሜዳ ይሰራ የነበረ ፈረንጅ ልክ ልኩን ነግሬ አሰናበትኩ። ሌላ ቀን አንደኛዋ አሜሪካዊት ከሌላ ወንድ አሜሪካዊ ጋር ስትዳር ለሰርግ አዲስ አበባ ተጠራሁ። በግብዣው መሐል ያንን የመሐል ሜዳ አሜሪካዊ አየሁት። ለምን እንደሆነ በማላውቀው ምክንያት ሰውነቴ ተቀያየረ፤ ተናደድኩ። ከዚያ ወደሱ እየሄድኩ "Never in this country!" ማለትም "በዚህች አገር ፈጽሞ አይሆንላችሁም!" እያልኩ ስጠጋው የቤቱ ማለትም የ"አዲስ ጉርሻ" ባለቤት የሆነው ጃማይካዊ "ሰክረሃል መሰለኝ" ብሎ አስቆመኝ። ባያስቆመኝ በቤቱ በብዛት ሐበሾች ስለነበሩ ግጭት ሊፈጠር እንደሚችል እገምታለሁ። አንዷ ጥቁር አሜሪካዊት ስለምትቆረቆርልን መሰለኝ "ነገሩ የለም ትላላችሁ እንጂ ወንዶቹ አሜሪካውያን እዚህ (ኢትዮጵያ) ብዙ ኢትዮጵያውያን ወንዶች የፍቅር ጓደኞች አሏቸው" ብላኛለች።

4. ውብሸት ወርቃለማሁ ከአሜሪካና ከዉጪ ዲፕሎማት ወንዶች ጋር ያለውን ምስጢር አላውቅም። ልጁ ግን በግልጽ የወጣ ግብረሰዶማዊ ነው። ይህን ላውቅ የቻልኩት ሙያዬ የእንግሊዝኛ ሥነጽሑፍ ስለሆነ የሱን ምርምሮች አግኝቼ ሳነብ ነው። ጉዳዩ አገርበቀል ነው ባይ ነው።

5. በቅርቡ ከአንዲት ሐኪም ጋር ሳወራ ብዙ ነገር ነገረችኝ። ወጣት ወንዶች በሚያጋጥማቸው ችግር እሷ ሐኪም ቤት እንደሚመጡ ነገረችኝ። ወንድአዳሪ እንደሆኑ ነግኛለች። ሌላ በሃያዎቹ አጋማሽ ያለች ወጣት ሴት ልጅ መውለድ እንደምትፈልግና ከዚህ ነገር እንዴት መውጣት እንደምትችል ለማማከር መምጣቷን ነግራኛለች።

5. አንድ ኢትዮጵያዊ ቤተሰብ አሜሪካ ሁለት ወንዶች ልጆች አሉት። አንዱ ገንዘብ ይልክላቸዋል። ሌላው አይልክም። "ትልቁ ሲረዳን አንተ ምነው ረሳኸን!" እያሉ ይጨቀጭቁታል። ተምሬ ሰርቼ እልክላችኋለሁ ቢል አስቸገሩት። ምስጢሩን ዘረገፈው። "እሱ እኮ ወንድ አዳሪ ሆኖ ከወንዶች ጋር ግንኑነት እየፈጸመ ከሚያገኘው ነው የሚልክላችሁ" ሲላቸው "ታዲያ አንተስ የለህም እንዴ!" አሉት። እሴት እየጠፋ ነው።

6. ትናይት ለአንዲት አዝማማያዋ ላላማረኝ ወጣት በፌስቡክ መልዕክት "ያልሆነ ነገር ውስጥ እንዳትገቢ። ህሊናሽን ንፁህ እንደሆነ አቆዪው" ብዬ መልዕክት ልኬላት "እሺ" ብላ መለሰችልኝ። ይሳካልኝ ይሆን? ሱፍ እየለበሰ በመዞር ኃይማኖት ከመስበክ እንደመለስኩት ወዳጄ በተሳካልኝ።

7. ባለፈው በሬዲዮ የሰማነውስ አንዲት ኢትዮጵያዊት ሴት ዉጪ አገር ከሴት ጋር ስትጋባ ሰርግ ላይ ወላጆቿን ጠርታ እናቷ ስትሄድ አባቷ የቀረው?

ወገኖቼ፣ ዝምታው ያብቃ! ልጅ ወልዶ ማዕረግ ማየት እንዳማራችሁ እንዳይቀር።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...