2023 ጁላይ 8, ቅዳሜ

ግለ ታሪክ 2

 በስድስት ዓመቴ ትምህርት ቤት ማለትም አንደኛ ክፍል ገባሁ፡፡ ትምህርት የሚባል አላውቅም፡፡ የአንደኛ ክፍል ስም ጠሪዬ ቲቸር ታደሰ መረብ ኳስ ሲጫወቱ በጓደኛቸው ‹‹እነ መዘምር እኮ ምንም አያውቁም፡፡ ዓመት ሙሉ ተመላልሰው እንዴት ልጣላቸው ብዬ ነው›› ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፡፡ ይህ ለምን ሆነ? አባቴ ዕድሜዬ ሳይደርስ አስገባኝ፡፡ እስከ አራተኛ ክፍል ምንም ሳላውቅ ቆየሁ፡፡ የየክፍሉ ትምህት ይደራረባል፡፡ እሱ ጥሩ ያደረገ መስሎት ወይም ዕድሎችን ሲሻማ እኔ በመሐል ቤት ተጎዳሁ፡፡ የአንድን ሰው ሕይወት ማበላሸቱን አስቡት፡፡ እኔ ያለዕድሜዬ ገብቼ ሦስት ዓመት የሚበልጠኝ ወንድሜ ማለትም እንጀራ ልጁ እኔ ሦስተኛ  ክፍል እስክደርስ በግ እረኛ ሆኖ ቀረ፡፡ ያ ክፋት በኔ ትምህርት አለመሳካት ተካካሰ፡፡ ያ ልጅ በአደጋ ሲሞት አባቴ ምን ተሰምቶት ይሆን? በክፋት ውስጥ አድጌ ይህን ለማጽዳት እየሰራሁ ነው፡፡   

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...