2023 ጁላይ 3, ሰኞ

ግለ-ታሪክ

የሁለተኛ ክፍል ተማሪ ሆኜ መዝሙር በመዘመር ሰኔ 30 ተሸልሜ ነበር። ከሁሉም ልጅ በላይ ጮክ ብሎ መዘመርን ማን መክሮኝ እንዳደረኩት አላስታውስም። እንግዲህ አንዱ ሲዘመር ጮክ ተብሎ ነው ብሎኝ እውነት አድርጌው ይሆናል። ብቻ አላውቅም። 8 ክፍሎች በእኔ ምክንያት ብዙ ቀን ተገርፈዋል። "ጉርምስና ነው የማትዘምሩት! ይህ ትንሽ ልጅ ሲዘምር!" እየተባሉ። ከሁሉም ትንሹ ሳልሆን አልቀርም። ሁሉም ሰው ተረት ንገረን እያለ ይይዘኛል። ያን ሳስታውሰው አሁን ሥነጽሑፍ ማጥናቴ ይገርመኛል። አንድ ቀን ማለዳ እናቴ ክፉኛ ደበደበችኝ። በፍልጥ ሳይሆን አይቀርም። ስጋዬ ሳይቦጫጨቅ አንቀርም። ጎረቤታችን ጋሽ ሞገስ ነው ሮጦ መጥቶ የገላገለኝ። እንደምንም ደብተሮቼን ይዤ ወደ /ቤት እያለቀስኩ አመለጥኩ። ያስደበደበኝ ቁርስ መጠየቄ ነው። ቸግሯት አይደለም። ሙሉ ተመን ያላት ገበሬ ነች። ምግብ ያለመስራት ስንፍና ነው። ትምህርት ቤት ገብቼም ለቅሶዬ አላቆመም። ስዘምርም ጮክ ብዬ እያለቀስኩ። ቲቸር በመዝሙር መሐል ቀጥ ብለው ከቆሙበት መጥተው "መዘምር ተወው" አሉኝ። ጎረቤታችን የነበረን ልጅ /ብርሃን አግኝቼው "አቤት እናታችሁን ስትፈሯት!" አለኝ። ወንድሜ በዓመቱ በአደጋ ሞተ። ልጄን ቀጥቅጬ ገደልኩ አለች። አደራ በትዳራችሁ ስትናደዱ በልጆች ላይ እንዳትበቀሉ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት

  በመንግሥት ወደ ወለጋ ከተወሰዱ በኋላ ዛሬ በግላቸው ደብረብርሃን የገቡት አዛውንት የዓይን ምስክርነት ረቡዕ፣ የካቲት 20፣ 2016 ዓ.ም. መዘምር ግርማ ደብረብርሃን   ዛሬ ረፋድ አዲስ አበባ ላምበረ...